2015 ኦክቶበር 19, ሰኞ

34ኛው አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ መደበኛ ስብሰባ ተጀመረ


አትም ኢሜይል
01sebeka 34
ጥቅምት 8 ቀን 2008 ዓ.ም
በእንዳለ ደምስስ
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን 34ኛው አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ መደበኛ ስብሰባ ጥቅምት 8 ቀን 2008 ዓ.ም በጠቅላይ ቤተ ክህነት ስብከተ ወንጌል አዳራሽ ቅዱስ ፓትርያርኩ፣ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ የየአህጉረ ስብከቱ ሓላፊዎችና የጠቅላይ ቤተ ክህነት ልዩ ልዩ መምሪያ ሓላፊዎች በተገኙበት ተጀምሯል፡፡

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የመክፈቻ ቃለ በረከት በማስተላለፍ ቀጥሏል፡፡

03sebaka3402sebeka34ቅዱስነታቸው ባስተላለፉት ቃለ በረከት ትናንት ቤተ ክርስቲያን ሀብተ ወልድ እና ስመ ክርስትና ሰጥታ በአባልነት የተቀበለቻቸው ልጆቿ ዛሬ እናት ቤተ ክርስቲናቸውን እየካዱ ወደሌላ ጎራ የመቀላቀሉ ጉዳይ እጅግ እየናረና የምእመናን ፍልሰት በየጊዜው እየጨመረ መሔዱ አሳሳቢ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡

06sebeka34የምእመናን ፍልሰት በተመለከትም መንስኤው ምንድነው ሲሉ ጠይቀዋል፡፡ ምእመናን ከቤተ ክርስቲያናችን እየወጡ ወደ ሌላ ካምፕ ለመግባት ለምን መረጡ? የሚያስተምራቸው ካህን አጥተው ነው? የቤተ ክርስቲያንናችን ትምህርት ሃይማኖት ክፍተት ኖሮት ነው? የቤተ ክርስቲያናችን አስተዳደር የማያረካ ሆኖ ነው? የካህን እጥረት ስላለ ነው? ወይስ ሌሎች ከእኛ ተሽለው ስለተገኙ ነው? አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤው ትኩረት ሰጥቶ ሊነጋገርበት ይገባል ብለዋል፡፡

ቅዱስነታቸው ወደፊት ትኩረት ሊሰጣቸው የሚገቡ ናቸው ያሏቸውንም እንደመፍትሔ ጠቁመዋል፡፡ ምእመናንን የመጠበቅ ተልእኮ በሚገባ እየተወጣን አይደለምና ባዶአችንን ከመቅረታችን በፊት ለተደራጀና ለድንበር የለሽ ትምህርተ ወንጌል ብንነሣ፤ የአስተዳደር ሥራችን ለምእመናን ሕሊና እንቅፋት እየሆነ ነውና የሃይማኖቱን መርህ ጠብቀን አስተዳደራችን የሕግ የበላይነት ያረጋገጠ፣ ግልጽ፣ ተአማኒና ተጠያቂነትን ያሰፈነ፣ የምእመናን ልብ የሚያረካ ተጨባጭ ለውጥ ማስመዝገብ ያስፈልጋል ሲሉ አሳስበዋል፡፡

04sebeka34ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የወላይታ ኮንታና ዳውሮ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ባስተላለፉት መልእክትም በዚህ ባለንበት ዘመን ሰበካ ጉባኤን የማጠናከር እንዲሁም የቤተ ክርስቲያናችንን ሁለንተናዊ ተልእኮ በመወጣት እድገቷንና ልማቷን በማፋጠን ተገቢ ሥራ በተገቢው ሥፍራ ሠርተን የጥንታዊትና የታሪካዊቷን ቤተ ክርስቲያናችን ሕልውና በመጠበቅ ዛሬም ለሀገርና ለወገን የምትሰጠውን አገልግሎት ማጠናከር ይገባል ብለዋል፡፡


በ2007 ዓ.ም የተከናወኑ ዓበይት ተግባራትንም በተመለከተ አባ ኃ/ማርያም መለሰ /ዶ/ር/ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ ቤት ምክትል ሥራ አስኪያጅ ዝርዝር ሪፖርት አቅርበዋል፡፡ ባቀረቡት ሪፖርትም በ2007 በጀት ዓመት በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት፣ የሊቃውንት ጉባኤን፣ የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ መምሪያን፣ የትና ሒሳብ መምሪያን፣ የገማት መምሪያን፤ የቅርስ ጥበቃና ተ መጻሕፍት ወመዘክርን፣ የሰብከተ ወንጌልና የሐዋርያዊ ተልእኮ መምሪያን፣ የቤቶችና ሕንፃዎች አስተዳደርና የልማት ድርጅትን፣ የማኅበረ ቅዱሳንን፣ . . . ወዘተ ሪፖርት አቅርበዋል፡፡05sebaka34
ከሰዓት በኋላ ጠቅላላ የሰበካ ጉባኤው ከየአህጉረ ስብከት የቀረቡ ሪፖርቶችን በማድመጥ ላይ ይገኛል፡፡

የአጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤው እስከ ጥቅምት 14 ቀን 2008 ዓ.ም ይቀጥላል፡፡

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

                                   በአውሮጳ   የካህናት አንድነት ማኅበር ሊቋቋም መሆኑ ታወቀ በ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከመላዋ አውሮጳ   የተውጣጡ ካህናት፡” የ...