2013 ኦክቶበር 10, ሐሙስ

ሰንበት ት/ቤቱ የካህናት  ሥልጠና አዘጋጀ
   በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በደብረ ከዋክብት አቡነ አረጋዊና ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ  ደብር የካህናት ሥልጠና ተዘጋጀ
የደብሩ ሰንበት ት/ቤት ያዘጋጀው ይህ ሥልጠና ከመስከረም 20-28  /2006  ዓ.ም ነው ፡፡ በሥልጠናውም ትምህርተ  ኖሎት ፤ ሥርዓተ ቤተክረስቲያን 
  ክርሥቲያናዊ ሥነ ምግባር ፤ የግጭት አፈታት ዘዴ እና ወቅታዊ የቤተ ክርስቲያን ጉዳይች  በሥልጠናው ተካተዋል  የደብሩ ሰንበት ት/ቤት  በተለይ ለካህናቱ ስልጠና ማዘጋጀቱ የቤተክርስቲያንን አገልግሎት በተቀላጠፈ መልኩ ለመፈጸም ይረዳናል ያሉት ሠልጣኞች ካህናት ሥልጠናው ወደፊትም መቀጠል እንዳለበት ተቁመዋል፡፡ በተለይ አሁን ያለውን ትውልድ በሚገባ ለማገልገልና ዘመኑን የዋጀ አገልግሎት ለሕዝበ ክርስቲያኑ ለማድረስ ይቻል ዘንደ የካህናት ሥልጠና በተጠናከረ መልኩ መቀጠል እንደሚያስፈልግ የደብሩ ሰንበት ት/ቤት ጠቁሞአል ፤በየደብሩ ይህ ተሞክሮ መቀጠል እንዳለበትም  የተጠቆመ ሲሆን ሌሎችም ባለድርሻ አካላት በሚችሉት ሁሉ ተሳታፊ እንዲሆኑ  ሰንበት ት/ቤቱ ጥሪ አቅርቧል፡፡  በሰንበት ት/ቤቱ  የሚያገለግሉ ወጣቶች በየመሥሪያ ቤቱ የሚሰሩ ዲያቆናት ሌሎቹንም በማስተባበር ሥልጠናው የተዘጋጀ መሆኑ ታውቋአል፡፡   

ሰንበት ት/ቤቱ የካህናት  ሥልጠና አዘጋጀ
   በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በደብረ ከዋክብት አቡነ አረጋዊና ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ  ደብር የካህናት ሥልጠና ተዘጋጀ
የደብሩ ሰንበት ት/ቤት ያዘጋጀው ይህ ሥልጠና ከመስከረም 20-28  /2006  ዓ.ም ነው ፡፡ በሥልጠናውም ትምህርተ  ኖሎት ፤ ሥርዓተ ቤተክረስቲያን 
  ክርሥቲያናዊ ሥነ ምግባር ፤ የግጭት አፈታት ዘዴ እና ወቅታዊ የቤተ ክርስቲያን ጉዳይች  በሥልጠናው ተካተዋል  የደብሩ ሰንበት ት/ቤት  በተለይ ለካህናቱ ስልጠና ማዘጋጀቱ የቤተክርስቲያንን አገልግሎት በተቀላጠፈ መልኩ ለመፈጸም ይረዳናል ያሉት ሠልጣኞች ካህናት ሥልጠናው ወደፊትም መቀጠል እንዳለበት ተቁመዋል፡፡ በተለይ አሁን ያለውን ትውልድ በሚገባ ለማገልገልና ዘመኑን የዋጀ አገልግሎት ለሕዝበ ክርስቲያኑ ለማድረስ ይቻል ዘንደ የካህናት ሥልጠና በተጠናከረ መልኩ መቀጠል እንደሚያስፈልግ የደብሩ ሰንበት ት/ቤት ጠቁሞአል ፤በየደብሩ ይህ ተሞክሮ መቀጠል እንዳለበትም  የተጠቆመ ሲሆን ሌሎችም ባለድርሻ አካላት በሚችሉት ሁሉ ተሳታፊ እንዲሆኑ  ሰንበት ት/ቤቱ ጥሪ አቅርቧል፡፡  በሰንበት ት/ቤቱ  የሚያገለግሉ ወጣቶች በየመሥሪያ ቤቱ የሚሰሩ ዲያቆናት ሌሎቹንም በማስተባበር ሥልጠናው የተዘጋጀ መሆኑ ታውቋአል፡፡   

ሰንበት ት/ቤቱ የካህናት  ሥልጠና አዘጋጀ
   በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በደብረ ከዋክብት አቡነ አረጋዊና ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ  ደብር የካህናት ሥልጠና ተዘጋጀ
የደብሩ ሰንበት ት/ቤት ያዘጋጀው ይህ ሥልጠና ከመስከረም 20-28  /2006  ዓ.ም ነው ፡፡ በሥልጠናውም ትምህርተ  ኖሎት ፤ ሥርዓተ ቤተክረስቲያን 
  ክርሥቲያናዊ ሥነ ምግባር ፤ የግጭት አፈታት ዘዴ እና ወቅታዊ የቤተ ክርስቲያን ጉዳይች  በሥልጠናው ተካተዋል  የደብሩ ሰንበት ት/ቤት  በተለይ ለካህናቱ ስልጠና ማዘጋጀቱ የቤተክርስቲያንን አገልግሎት በተቀላጠፈ መልኩ ለመፈጸም ይረዳናል ያሉት ሠልጣኞች ካህናት ሥልጠናው ወደፊትም መቀጠል እንዳለበት ተቁመዋል፡፡ በተለይ አሁን ያለውን ትውልድ በሚገባ ለማገልገልና ዘመኑን የዋጀ አገልግሎት ለሕዝበ ክርስቲያኑ ለማድረስ ይቻል ዘንደ የካህናት ሥልጠና በተጠናከረ መልኩ መቀጠል እንደሚያስፈልግ የደብሩ ሰንበት ት/ቤት ጠቁሞአል ፤በየደብሩ ይህ ተሞክሮ መቀጠል እንዳለበትም  የተጠቆመ ሲሆን ሌሎችም ባለድርሻ አካላት በሚችሉት ሁሉ ተሳታፊ እንዲሆኑ  ሰንበት ት/ቤቱ ጥሪ አቅርቧል፡፡  በሰንበት ት/ቤቱ  የሚያገለግሉ ወጣቶች በየመሥሪያ ቤቱ የሚሰሩ ዲያቆናት ሌሎቹንም በማስተባበር ሥልጠናው የተዘጋጀ መሆኑ ታውቋአል፡፡   



          ሰንበት ት/ቤቱ የካህናት  ሥልጠና አዘጋጀ
   በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በደብረ ከዋክብት አቡነ አረጋዊና ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ  ደብር የካህናት ሥልጠና ተዘጋጀ
የደብሩ ሰንበት ት/ቤት ያዘጋጀው ይህ ሥልጠና ከመስከረም 20-28  /2006  ዓ.ም ነው ፡፡ በሥልጠናውም ትምህርተ  ኖሎት ፤ ሥርዓተ ቤተክረስቲያን 
  ክርሥቲያናዊ ሥነ ምግባር ፤ የግጭት አፈታት ዘዴ እና ወቅታዊ የቤተ ክርስቲያን ጉዳይች  በሥልጠናው ተካተዋል  የደብሩ ሰንበት ት/ቤት  በተለይ ለካህናቱ ስልጠና ማዘጋጀቱ የቤተክርስቲያንን አገልግሎት በተቀላጠፈ መልኩ ለመፈጸም ይረዳናል ያሉት ሠልጣኞች ካህናት ሥልጠናው ወደፊትም መቀጠል እንዳለበት ተቁመዋል፡፡ በተለይ አሁን ያለውን ትውልድ በሚገባ ለማገልገልና ዘመኑን የዋጀ አገልግሎት ለሕዝበ ክርስቲያኑ ለማድረስ ይቻል ዘንደ የካህናት ሥልጠና በተጠናከረ መልኩ መቀጠል እንደሚያስፈልግ የደብሩ ሰንበት ት/ቤት ጠቁሞአል ፤በየደብሩ ይህ ተሞክሮ መቀጠል እንዳለበትም  የተጠቆመ ሲሆን ሌሎችም ባለድርሻ አካላት በሚችሉት ሁሉ ተሳታፊ እንዲሆኑ  ሰንበት ት/ቤቱ ጥሪ አቅርቧል፡፡  በሰንበት ት/ቤቱ  የሚያገለግሉ ወጣቶች በየመሥሪያ ቤቱ የሚሰሩ ዲያቆናት ሌሎቹንም በማስተባበር ሥልጠናው የተዘጋጀ መሆኑ ታውቋአል፡፡   

2013 ኦክቶበር 5, ቅዳሜ


ቀጣዩ የኢሕአዴግ ዒላማ ማኅበረ ቅዱሳን ይኾን?

FACT Weekily Magazine cover story
(ፋክት መጽሔት፤ ቁጥር 14 መስከረም ፳፻፮ ዓ.ም.)
ተመስገን ደሳለኝ
የኢሕአዴግ ታጋዮች የመንግሥት ‹‹ጠንካራ ይዞታ›› የሚባሉ ከተሞችን ሳይቀር መቆጣጠር ችለዋል፤ ወደ አዲስ አበባም የሚያደርጉት ግሥጋሴም ፕሬዝዳንት መንግሥቱ ኃይለ ማርያምን ሳይቀር ዕንቅልፍ ነስቷል፡፡ በአንዳች ተኣምር ግሥጋሴውን መግታት ካልቻሉ በጥቂት ወራት ውስጥ ሁሉም ነገር ታሪክ እንደሚኾን በማወቃቸው መላ በማፈላለጉ ላይ ተጠምደዋል፡፡ በዚህን ጊዜ ነበር(የሐሳቡ አመንጪ ተለይቶ ባይታወቅም)፣ ‹‹ለዩኒቨርስቲ ተማሪዎች አጭር ሥልጠና ሰጥቶ ከሀገሪቱ ሠራዊት ጎን ማሰለፍና የ‹ወንበዴውን ጦር› ማድረሻ ማሳጣት›› የሚለው ሐሳብ እንደ መፍትሔ የተወሰደው፡፡
እናም መንግሥቱ ራሳቸው ተማሪዎቹን በዩኒቨርስቲ አዳራሽ ሰብስበው እንዲህ ሲሉ አፋጠጧቸው፡- ‹‹እነርሱ (ኢሕአዴግና ሻዕቢያን ማለታቸው ነው) ለእኵይ ዓላማቸው ከእረኛ እስከ ምሁር ሲያሰልፉ እናንተ ምንድን ነው የምትሠሩት? በሰላማዊ ሰልፍና በስብሰባ ብቻ መቃወም ወይስ ወንበዴዎቹ እንዳደረጉት ከአብዮታዊ ሠራዊታችነ ጎን ቆማችኹ የአገሪቱን ህልውና ታስከብራላችኹ?››
ይህን ጊዜም አስቀድሞ በተሰጣቸው መመሪያ ከተማሪው ጋራ ተመሳስለው በአዳራሹ የተገኙት የደኅንነት ሠራተኞችና የኢሠፓ ካድሬዎች ‹‹ዘምተን ከጠላት ጋራ መፋለም እንፈልጋለን›› ብለው በስሜትና በወኔ እየተናገሩ በሠሩት ‹ድራማ› ተማሪው ትምህርት አቋርጦ እንዲዘምት ተወሰነ፤ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲም ተዘጋ፤ ተማሪዎቹም ለወታደራዊ ሥልጠና ደቡብ ኢትዮጵያ ወደሚገኘው ብላቴ የአየር ወለድ ማሠልጠኛ ከተቱ፡፡
ከመላው ዘማቾች ዐሥራ ሁለት የሚኾኑ ተማሪዎች ተሰባስበው ሲያበቁ በየቀኑ ካምፓቸው አቅራቢያ ወደሚገኘው ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን በመሄድ ከመዐቱ ይታደጋቸው ዘንድ ፈጣሪያቸውን በጸሎት መማጠን የሕይወታቸው አካል አደረጉት፤ ከቀናት በኋላም በአንዱ ዕለት አንድም ለመታሰቢያና ለበረከት. ሁለትም ስብስቡ ሳይበተን ወደፊት እንዲቀጥል በሚል ዕሳቤ ‹‹ማኅበረ ሚካኤል›› ብለው የሠየሙትን የጽዋ ማኅበር መሠረቱ፡፡ . . . ይኹንና ከመካከላቸው አንዳቸውም እንኳ በ፲፱፻፸፯ ዓ.ም በፓዌ መተከል ዞን የተደረገውን የመልሶ ማቋቋም ሠፈራ ፕሮግራም እንዲያመቻቹ በዘመቱ ተማሪዎች ከተመሠረተውና ከተለያዩ የጽዋ ማኅበራት ጋራ በመዋሐድ የዛሬውን ‹‹ማኅበረ ቅዱሳን›› እንደሚፈጥሩ መገመት የሚችሉበት የነቢይነት ጸጋ አልነበራቸውም፤ የኾነው ግን እንዲያ ነበር፡፡

ማኅበረ ቅዱሳን
የ‹‹ማኅበረ ሚካኤል›› መሥራቾች ከተማሪ ጓደኞቻቸው ጋራ ‹‹ይለያል ዘንድሮ የወንበዴ ኑሮ››ን እየዘመሩ የገቡበት ወታደራዊ ሥልጠና ተጠናቅቆ ወደ ጦር ሜዳ ከመግባታቸው በፊት ዐማፅያኑ አሸንፈው የመንግሥት ለውጥ በመደረጉ ሥልጠናቸውን ሳይጨርሱ ወደየመጡበት ተመለሱ፡፡ ኾኖም ለውጡ በተካሄደ በዓመቱ እነርሱን ጨምሮ በአምላካቸው፣ በጻድቃን፣ በሰማዕታትና በመላእክታት ስም የተመሠረቱ[ከአቡነ ጎርጎርዮስ ዘንድ ሲማሩ የቆዩ] የተለያዩ ማኅበራት ተሰባስበው ወደ አንድ እንዲመጡ መደረጉ ሊጠቀስ የሚገባ ልዩነት ባይፈጥርም ስያሜው ግን ብርቱ ክርክር አሥነሳ፤ አቡነ ገብርኤልም ‹‹ማኅበረ ቅዱሳን ብዬዋለኹ›› ብለው ውጥረቱን አረገቡት፡፡ ዕለቱም[ልደቱን የሚቆጥርበት] ግንቦት ፪ ቀን ፲፱፻፹፬ ዓ.ም. እንደነበር ተጽፏል፡፡
ዓላማው ምንድን ነው?
ማኅበረ ቅዱሳን ሲመሠረት ዓላማዬ ብሎ የተነሣበት መሠረታዊ ጉዳይ በተለያየ ጊዜ ለኅትመት ባበቃቸው ድርሳናቱ ተገልጧል፡፡ እርሱም፡- ትምህርተ ሃይማኖት፣ ሥርዐተ እምነት፣ ክርስቲያናዊ ትውፊትና ታሪክ ተጠብቀው ለትውልድ እንዲተላለፉ ማስቻል ነው፡፡
ማኅበሩ ከመሰሎቹ የተለየ ጥንካሬ እንዲኖረው ያስቻለው ዓላማውን ከግብ ለማድረስ በዋናነት በሀገሪቱ የተለያዩ ዩኒቨርስቲዎችና ኮሌጆች የሚማሩ ተማሪዎችን አባል ማድረጉ ላይ ተግቶ መሥራቱ ነው፡፡ ዛሬም ድረስ መስፈርቱ እያገለገለ እንደኾነ ይታወቃል፤ ይህ ኹኔታም ይመስለኛል አንዳንድ ጸሐፍት ማኅበሩን ‹‹ቤተ ክርስቲያኗ በዩኒቨርስቲዎች ያላት እጅ›› እንዲሉት ያስገደዳቸው፡፡
የኾነው ኾኖ ማኅበሩ በምሥረታው ማግሥት በሃይማኖቱ የመጨረሻውን ሥልጣን በያዘው ቅዱስ ሲኖዶስ ዕውቅና ተሰጥቶት በጠቅላይ ቤተ ክህነት የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ ሥር እንዲኾን ተደረገ፡፡ በ፲፱፻፹፭ ዓ.ም. ደግሞ መተዳደርያ ደንቡን አጸደቀ፡፡
የግጭት ጅማሬ
. . . አንዳንድ የኢሕአዴግ አመራሮች በብላቴ ከተመሠረተው ‹‹ማኅበረ ሚካኤል›› ጋራ በማያያዝ የማኅበሩን መሪዎች አልፎ አልፎ ‹‹ተረፈ ደርግ›› እና ‹‹መአሕድ›› እያሉ ከማሸማቀቅ ባለፈ ብዙም ጫና አያደርጉባቸውም ነበር፡፡ ዛሬ ማኅበሩን በመንግሥት ጥቁር መዝገብ በቁጥር አንድ ጠላትነት እንዲሰፍር ካደረጉት ልዩነቶች(ያለመግባባቶች) መካከል ዋናዎቹን በአዲስ መሥመር እጠቅሳለሁ፡፡
ኢሕአዴግ የአገሪቱን ምሥረታ ከዐፄ ምኒልክ ዘመን የሚጀምር የመቶ ዓመት ማድረጉ ማኅበሩ ዓላማዬ ከሚለው ‹‹ታሪክን ጠብቆ ለትውልድ ማስተላለፍ›› ጋራ መታረቅ አለመቻሉ ያስከተለው ውጥረት የመጀመሪያው ነው፡፡ ማኅበሩ ‹‹የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ታሪክ 2000 ዓመት ወደኋላ ሄዶ ማስላቱ ብቻውን፣ ‹‹አንዲት ኢትዮጵያን በመፍጠር ስም ምኒልክና ተከታዮቹ ያስፈኑትን ጭቆና በጠመንጃ ለማስወገድ በረሓ ገባን›› ከሚሉት የህወሓት መሥራቾች ጋራ ሊያጋጨው መቻሉ የሚጠበቅ ነበር፡፡ ጉዳዩን ከለጠጥነው ደግሞ ‹‹ማኅበሩን በ1980ዎቹ አጋማሽ እንደ ስጋት ይመለከተው የነበረውን ‹የሸዋ ፊውዳል› ወደ ሥልጣን ለማምጣት ያደፈጠ ተቃናቃኝ አድርጎ ፈርጆት ነበር›› ወደሚል ጠርዝ ሊገፋን ይችላል፡፡ በነገራችን ላይ፣ በፖሊቲካው መንገድ ለሹመት የበቁት አቡነ ጳውሎስም እስከ ኅልፈታቸው ድረስ ማኅበሩ በሸዋ ተወላጅ ጳጳስ ሊተካቸው የሚያሤር ይመስላቸው እንደነበር ይነገራል፡፡
በጥቅሉ በኢሕአዴግና በማኅበረ ቅዱሳን መካከል የርእዮተ ዓለም (በብሔር እና በኢትዮጵያዊነት ላይ የተመሠረተ) ልዩነት መኖሩ ላለመግባባቱ መነሾ ነው፡፡
ሌላው የቅራኔአቸው መንሥኤ፣ በወርኃ ሚያዝያ ፲፱፻፺፫ ዓ.ም ፕሮፌሰር መስፍን ወልደ ማርያምና ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ጋራ ሰብአዊ መብትንና አስተዳደራዊ ጉዳዮችን በተመለከተ የግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይት ባደረጉ ማግሥት፣ በዋናው ግቢ ከተቀሰቀሰው ተቃውሞ ጋራ የሚያያዘው ኹነት ነው፡፡ በወቅቱ ተማሪዎቹ በሰላማዊ መንገድ ላቀረቡት ጥያቄ የጸጥታ አስከባሪዎች የኃይል ምላሽ መስጠታቸው ጉዳዩን ከቁጥጥር ውጭ አደረገው፡፡ ድብደባውና ማሠቃየቱ ከአቅም በላይ የኾነባቸው የተወሰኑ ተማሪዎችም ከመንበረ ፓትርያርኩ በአጥር ወደሚለየው ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ሸሽተው ይገባሉ፡፡ በአካባቢው የነበሩ የጸጥታ ሠራተኞችም የግቢውን በር ይቆልፋሉ፤ ተማሪዎቹንም በኃይል አስወጥተው ደብድበው አሰሯቸው፤ ድርጊቱንም ማኅበረ ቅዱሳን በስምዐ ጽድቅ ጋዜጣ የቤተ ክርስቲያኗን ለሸሸ መጠለያነት ታሪክ አጣቅሶ አጠንክሮ መቃወሙ ከመንግሥት ጋራ በዐደባባይ ቅራኔ ውስጥ ከተተው፡፡
ሌላው ቅራኔአቸውን ያጦዘው ክሥተት ደግሞ በአቶ ተፈራ ዋልዋ በ፲፱፻፺፰ ዓ.ም ወርኃ ጥቅምት ‹‹መንግሥትና አብዮታዊ ዴሞክራሲ›› በሚል ርእስ ለዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ሥልጠና በተሰጠበት ወቅት ኦርቶዶክስን ‹‹የነፍጠኞች ምሽግ››፣ ጥምቀቱንም ‹‹በውኃ መንቦጫረቅ›› ብሎ ማጣጣሉ ሲኖዶሱን ግድ ባይሰጠውም፣ ማኅበረ ቅዱሳንን አስቆጥቶ መልስ እንዲሰጥ ያደረገበት ኩነት መፈጠሩ ነበር፡፡
የመዋቅሩ ስፋትና የውጥረቶቹ ጡዘት
የማይቆጣጠረውን የተደራጀ ኃይል አጥብቆ ለሚፈራው ኢሕአዴግ፣ የማኅበሩ መዋቅር እየሰፋ መሄድ ስጋት ላይ ጥሎታል፡፡ አባላቱ የዩኒቨርስቲ ወይም ኮሌጅ ምሩቃን መኾናቸው ከገጠር እስከ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ቢሮ ድረስ የራሱ ሰዎች እንዲኖሩት አድርጓል፡፡ የአገዛዙም ጭንቀት ‹‹ይህ ኃይል አንድ ቀን በተቃውሞ ፖሊቲካ ሊጠለፍ ይችላል›› የሚል ነው፡፡ ይህንንም የሚያረጋግጠው አቶ ኣባይ ፀሃየ መስከረም ፲፪ ቀን ፳፻፪ ዓ.ም. የማኅበሩን አመራር በሲኖዶስ ጽ/ቤት ባነጋገረበት ወቅት ‹‹ኢሕአዴግ ገለልተኛ የሚባል ነገር አይገባውም›› የሚል መኾኑን ስናስታውስ ነው፡፡
. . .በኢሕአዴግና በቅንጅት መካከል በድኅረ ምርጫ – 97 የተፈጠረውን አለመግባባት ቤተ ክርስቲያኗ የቄሣርን ለቄሣር ብላ ለማንም ሳትወግን ዕርቅ እንዲፈጠር መሸምገል እንዳለባት ማኅበሩ በልሳኖቹ መወትወቱ የተገላቢጦሽ አገዛዙን አስኮረፈው፡፡ በአናቱም ከአማራ ክልል የተላከው ሪፖርት፣ ‹‹በገጠር ያሉ የማኅበሩ አባላት ለተቃዋሚዎች ቀስቅሰዋል›› ማለቱ ውጥረቱን አንሮታል፡፡
በሌላ በኩል መንግሥት ለሦስተኛ ጊዜ ባካሄደው የሕዝብ ቆጠራ ‹‹የ[ኦርቶዶክስ]ክርስቲያኑ ብዛት 33 ሚልዮን ነው›› ማለቱ፣ ‹‹45 ሚልዮን ነው [የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ መምሪያን መረጃ በመጥቀስ ከሚለው ማኅበረ ቅዱሳን ጋራ አለመግባባት ውስጥ ከቶት እንደነበር ይታወሳል፡፡
የኢሕአዴግ ክሦች
ኢሕአዴግ በ፲፱፻፺፱ ዓ.ም በጅማ በሻሻ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ካህናትና ምእመናን ‹‹የእስልምና እምነት ተከታዮች ናቸው›› በተባሉ አንገታቸው በስለት ተቆርጦ መገደላቸውን የሚያሳየውን ፊልም በሲዲ አባዝቶ ያሰራጨውም ኾነ ከጭፍጨፋው ጀርባ የመንግሥት እጅ አለበት የሚል የስም ማጥፋት ዘመቻ የመራው ማኅበሩ ነው ብሎ ያምናል፡፡
ከዚህ በተጨማሪ በአዲስ አበባ ‹‹ኢትዮጵያ የክርስቲያን ደሴት ናት››፣ በጎንደር ‹‹ጎዶልያስ›› (የእግዚአብሔር ጦር) የሚል ጽሑፍ የታተሙባቸው ቲሸርቶች አዘጋጅቶ ያሰራጨው ማኅበረ ቅዱሳን ነው ሲል ይከሳል፡፡ በነሐሴ ወር ፳፻፭ ዓ.ም በፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ሽፈራው ተክለ ማርያም ስም ‹‹የአክራሪነት/ጽንፈኝነት ዝንባሌዎችና መፍትሔዎቻቸው›› በሚል ርእስ የተሰራጨው ሰነድ ክሡን፡- ‹‹ኢትዮጵያ የክርስቲያን ደሴት ነች፤ አንድ አገር አንድ ሃይማኖት ወዘተ ጉዳዮችን በማቅረብ በአንድ በኩል የሃይማኖት ብዝኃነትን የሚፃረር፣ በሌላ በኩል ደግሞ አገራችን የሃይማኖት ብዝኃነት መኾኗን የሚቃወም አካሄድ ነው፤›› ሲል ያጠናክረዋል፡፡
የኦቦይ ስብሃት ኩዴታ
በ፳፻፩ ዓ.ም ፓትርያርኩ አቡነ ጳውሎስ ከሲኖዶሱ ጠንካራ ተቃውሞ አጋጥሟቸው እንደነበር ይታወሳል፡፡ ይኹንና ከዚህ ንቅናቄ ጀርባ አቡነ ሳሙኤልና ሁለት የማኅበረ ቅዱሳን አባላትን የያዙት ኦቦይ ስብሃት ነጋ እንደነበሩበት ለጉዳዩ ቅርብ ከነበሩ ሰዎች አረጋግጫለኹ፡፡ አቦይ ስብሃት ‹‹አቡነ ጳውሎስ ለኢሕአዴግ ዕዳ ነው›› ብለው መደምደማቸው ለኩዴታ እንዳነሣሣቸው ይነገራል፡፡
. . .[በተቃውሞው] ውጤት ፓትርያርኩ አሸነፉ፡፡ ማኅበሩ የእንቅስቃሴው ተቃዋሚ መኾኑን የተረዱት አቦይ ስብሃት ነጋ ጥርስ እንደነከሱበት ይነገራል፡፡ በነገራችን ላይ፣ የአቦይ ዕቅድ ቢሳካ ኖሮ ተያይዘው የሚነሡ አለመግባባቶችን በመጠቀም ማኅበሩን መምታትንም የሚያካትት ነበር፡፡
የዋልድባ ጉዳይ
በመንግሥትና በማኅበረ ቅዱሳን መካከል የነበረውን አለመግባባት ወደላቀ ጠርዝ ያደረሰው በዋልድባ ገዳም አካባቢ ይቋቋማል የተባለው የስኳር ፋብሪካ ጉዳይ ነው፡፡ በገዳሙ የሚኖሩ ምእመናንን ጨምሮ በርካታ የእምነቱ ተከታዮች ያሰሙትን ተቃውሞ ችላ በማለት ወደ ሥራ ለመግባት በሞከረው መንግሥት ላይ የተነሣው ተቃውሞ ተጠናክሮ ቀጠለ፡፡ ይኹንና ሥርዐቱ ገዳሙ ላይ አልደርስም ብሎ ሲከራከር፣ ቤተ ክህነትም የማጣራት ሥራ መሥራቱን ገልጦ ‹‹ምንም ዐይነት ችግር የለም›› ብሎ ከመንግሥት ጎን ቆመ፡፡
ማኅበረ ቅዱሳን ጉዳዩን ቦታው ድረስ ሄዶ የሚያጣራ አምስት አባላት ያለው ቡድን ወደ ዋልድባ ላከ፡፡ ቡድኑ አጥንቶ ባቀረበው ሪፖርት፡- ‹‹16.6 ሄክታር መሬት ከገዳሙ ተወስዷል፤ ገዳሙን የውኃ መጥለቅለቅ ያሰጋዋል፤ . . .›› የሚል ሪፖርት ለመንግሥት አቅርቧል፡፡ በተቃራኒው ደግሞ የዶ/ር ሽፈራው ሰነድ የማኅበሩን ጥናት እንዲህ ሲል ኮንኖታል፡- ‹‹መንግሥት በሃይማኖታችን ጣልቃ ገብቷል በሚል ገሃድ ፍላጎትና ድብቅ አሠራር ካላቸው የውጭ ቡድኖች ጋራ በማበር ሰላምን አደጋ ውስጥ የማስገባት፣ ሕገ መንግሥታዊ ሥርዐቱን በሃይማኖት ሽፋን ለመናድ ይንቀሳቀሳሉ፡፡ በቅርብ በነበረው የፓትርያርክ ምርጫና በዋልድባ ገዳም ዙሪያ የተፈጠረው ዝንባሌ የነዚህ ፍላጎቶች ማሳያ ነው፡፡››
የፓትርያርኩ ኅልፈት
በ፳፻፬ ዓ.ም መጨረሻ አቡነ ጳውሎስ ማለፋቸው ሌላ ፍጥጫን አስከትሏል፡፡ ማኅበሩ ስደተኛውን ፓትርያርክ አቡነ መርቆሬዎስን ከአሜሪካ አምጥቶ ወይም እንዳሻው የሚያሽከረክረውን ጳጳስ መንበሩ ላይ ለማስቀመጥ ምርጫው በሚፈልገው መንገድ እንዲጠናቀቅ በርትቶ እየሠራ ነው የሚለው ወቀሳ የመንግሥት ቁጣን የበዛ አድርጎታል፡፡ የጠቀሱት ሰነድም ውንጀላውን በገደምዳሜ ገልጾታል፡- ‹‹በእስልምናም ይኹን በክርስትና ሃይማኖቶች ሽፋን የሚደረገው የአክራሪነት/ጽንፈኝነት እንቅስቃሴ በዋናነት እየነጣጠረ የሚገኘው የተቋማቱን የበላይ አመራር ዕርከኖች መቆጣጠር ነው፡፡››
ናዳው እየመጣ ነው?
ባለፉት ሁለት ዓመታት የእስልምና እምነት ተከታዮች ‹‹መንግሥት በሃይማኖታችን ጣልቃ አይግባ›› በሚል የጀመሩትን ትግል ተከትሎ አገዛዙ ማኅበረ ቅዱሳንንም ደርቦ የመምታት ዕቅድ እንዳለው የሚጠቁሙ ምልክቶች ታይተዋል፡፡ የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤትን በሚኒስትር ማዕርግ የሚመራው አቶ ሬድዋን ሑሴን፣ ‹‹መንግሥት ጉዳዩን በሰላም ቢጨርሰው የተሻለ ነው›› ሲሉ ምክር ለመለገሥ ለሞከሩ የምዕራብ አገሮች ዲፕሎማቶች፣ ‹‹የአወሊያን ቡድን በዚህ መልኩ ሳናበረክከው ቀርተን መጅሊሱን እንዲወስድ ብናደርግ፣ ነገ ደግሞ ማኅበረ ቅዱሳን ‹ሲኖዶሱን አምጡ› ቢለን ምን መለስ ይኖረናል?›› ሲል የሰጠው ምላሽ ይህንኑ የሚመለክት ነው፡፡
የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር መ/ቤት ባለፈው ዓመት ወርኃ የካቲት ‹‹ለሃይማኖት ተቋማት የተዘጋጀ›› ብሎ ያሰራጨው ሰነድ ማኅበረ ቅዱሳን እና መብታቸው እየጠየቁ ያሉ የእስልምና እምነት ተከታየች የጥቃቱ ዒላማ እንደኾኑ ያሳያል፡፡ ሂደቱን በመምራትም ኾነ በማስፈጸም ከፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስትር ጀርባ ኾኖ በዋናነት የሚሠራው የፀረ ሽብር ግብረ ኃይል እንደኾነ ይታወቃል፡፡ ዶ/ር ሽፈራው ተክለ ማርያም ‹‹የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የፖሊቲካ ርብርብ ሜዳ አይኾኑም፤ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶችም ከማንኛውም ሃይማኖታዊ እንቅስቃሴ ነጻ መኾን አለባቸው›› ያሉበት ዐውድ ‹‹በዩኒቨርስቲዎች የአካዳሚ ትምህርትን ተገን በማድረግ እምነትን ማስፋፋት አይቻልም›› በማለት ማኅበሩ እንደ ቀድሞው አባላቱን ለማስተማር የሚችልበትን ኹኔታ የሚያግድ ነው፡፡
በ፳፻፮ ዓ.ም በዩኒቨርስቲዎች ይተገበራል የሚባለው አለባበስንና አመጋገብን የሚመለከተው መመሪያም ራሱን የቻለ አደጋ አለው፡፡ እንዲሁም የሃይማኖት ማኅበራት ዓላማቸውን አሳውቀው እንዲመዘገቡ የሚያስገድደውን ሕግ በምክር ቤት ለማጸደቅ ዝግጅቱ ተጠናቋል፡፡ መዝጋቢው ክፍል ማኅበራቱን በፍርድ ቤት ከማስቀጣት እስከ ማፍረስ የሚያደርስ ሥልጣን እንደሚሰጠው ምንጮቼ መረጃ አድርሰውኛል፡፡ ይበልጥ የመንደነግጠው ደግሞ በዚህ መልክ ማኅበራቱን ከጠለፉ በኋላ ማንም ሰው ‹‹ቅዱስ ቃሉን›› ለመስበክ ፈቃድ ማግኘትን ግዴታ ለማድረግ መታቀዱን ስናነብ ነው፡-
‹‹የሰባክያን/ዳኢዎች ሚናን የበለጠ ለማጎልበትና የተጠያቂነት ሥርዐት ለመትከል እያንዳንዱ የሃይማኖት ተቋም የራሱን መምህራን የሚለይበትን የመታወቂያ ሥርዐት ሊያበጅና በዚህም የክትትል ሥራ እንዲሠሩ መደገፍ ይቻላል፡፡››
ሰነዱ ወደ መንፈሳዊ ኮሌጅ የሚገቡ ተማሪዎችንም መልምሎ የሲኖዶሱን፣ የማኅበረ ቅዱሳንን፣ የመጅሊስን. . .አመራርነት የመያዝ ዕቅድ እንዳለው በዘወርዋራ ይጠቁማል፡፡ የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር በ፳፻፬ ዓ.ም ባዘጋጀው የሥልጠና ማንዋል ላይም ‹‹በኦርቶዶክስ ክርስትና መድረክ አክራሪው ኃይል ማኅበረ ቅዱሳን ነው›› ሲል መፈረጁ ይታወሳል፡፡ ከዚህ ጎን ለጎንም የማኅበረ ቅዱሳንን ግቢ ጉባኤ በማዳከም፣ ከሰንበት ት/ቤቶች፣ ከሰበካ ጉባኤና ከሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጆች ጋራ በማጋጨት፣ በካህናት በማስወገዝና በመሳሰሉት ተጠቅሞ ሊያፈርሰው እንደተዘጋጀ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡
በጥቅሉ ሰነዱ ማኅበረ ቅዱሳንን ‹‹በሃይማኖት ሽፋን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ሃይማኖት መንግሥታዊ ሃይማኖት መኾን ይገባዋል በሚል በአቋራጭ በአቋራጭ የፖለቲካ መሣርያ ለማድረግ የሚንቀሳቀስ›› ሲል ይኮንነዋል፡፡ ‹‹የአክራሪነትና ጽንፈኝነት ምንጩን ለማድረቅ እየተሠራ የሕግ የበላይነትን የማስከበር ሥራም ጎን ለጎን መፈጸም ያለበት ነው፤›› ሲል ጥቁምታ ይሰጣል፡፡
መፍትሔው ምንድን ነው?
ከላይ በጥቅሉ እንደጠቀስኩት የ22 ዓመታቱ ሂደት የሚያስረግጠው፣ የኢሕአዴግን ማንኛውም ዓለማዊም ኾነ ሃይማኖታዊ ተቋማት ነጻነት ያለማክበሩ ብቻ ሳይኾን ቀስ በቀስ ህልውናቸውን ለዘላለሙ ለማጥፋት በሙሉ ኃይሉ እየሠራ እንደኾነ ነው፡፡
. . . ማኅበሩ ዝምታውን በመግራት የራሱን ህልውና እጅግ በፍጥነት ለመታደግ መሞከር ይኖርበታል፡፡ ከሥርዐቱ የፖሊቲካ ዘዬ እንደተረዳነው ቀስ በቀስ እየተረዳነው በመጣው አፈና ላይ ማኅበሩ አንገቱን ቀብሮ፣ ጣልቃ ገብነቱን ቸል ብሎ የማንገራገሩ አካሄድ፣ በአንድ ክፉ ቀን በመጅሊሱ የተፈጸመው ታሪክ በራሱም ላይ መደገሙ አይቀሬ እንደኾነ ለመናገር ነቢይ መኾንን አይጠይቅም፡፡ የትምህርት ተቋማትን የረገጡ ከተሜ ወጣቶች በማኅበሩ ውስጥ መብዛታቸው የመውጫ መንገዱን በአመራሩ ላይ ይጥለዋል፤ ‹‹ለትላንት አናረፍድም፤ ለነገ አንዘገይም›› እንዲሉ የቤተ ክርስቲያኗ ሊቃውንት፡፡
ማስታወሻ፡- ጽሑፉ ከአንዳንድ መረጃውና ይዘቱ አንጻር መጠነኛ አርትዖት ተደርጎበት የቀረ

ለስሕተታቸው ሊቃነ ጳጳሳትን ይቅርታ የጠየቁ ግለሰቦች ጉዳይ፣ የቤተ ክርስቲያንን አንድነትና ቀኖና በጠበቀና ባገናዘበ መልኩ ሊወሰንበት ይገባል!

በቤተ ክርስቲያናችን ዐውደ ምሕረት ሰፍነውና በቢሮክራሲዋ ውስጥ ተሰግስገው የፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ ኑፋቄን ለሚያራምዱ ድርጅቶች ተልእኮ አስፈጻሚና የቅስቀሳ ኃይል የኾኑ ሕገ ወጥ ቡድኖችና ግለሰቦች የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ ለመመከት በኦርቶዶክሳዊ ቀናዒነትና በበጎ ፈቃድ ተሰባስቦ በጥቅምት ወር ፳፻፫ ዓ.ም አገልግሎቱን የጀመረው የፀረ – ፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ ሰባክያንና ዘማርያን ጥምረት÷ ባለፈው ሳምንት አጋማሽ ወቅታዊ ጉዳዮችን የገመገመበትንና ቀጣይ የአገልግሎት አቅጣጫዎችን የተለመበትን የግማሽ ቀን ውይይት አካሂዷል፡፡
ከጥምረቱ መምህራን አንዱ የኾኑት መ/ር ያረጋል አበጋዝ÷ ‹‹ከቅድስት ቤተ ክርስቲያን የወጡ(ያፈነገጡ) ሰዎች የሚመለሱት እንዴት ነው?›› በሚል በመድረኩ ያቀረቡት ጽሑፍ የውይይቱ ዋነኛ መነሻ ነበር፡፡ የጽሑፉን ዋና ዋና ክፍሎችና ተያያዥ ሐሳቦች በማስቀደምና ሙሉ ይዘቱን በማስከተል አቅርበነዋል፡፡ እንዲመለከቱት ተጋብዘዋል፡፡
*             *           *
የቤተ ክርስቲያን የአንድነቷ መሠረት ሃይማኖት ነው፡፡ ይህ ሃይማኖት ደግሞ ከእግዚአብሔር የተሰጠ አንድና ብቸኛ እውነት ነው፡፡ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እግዚአብሔር ለሰው ልጆች ሁሉ የሰጠውን የመዳን ጸጋ ሰዎች በሃይማኖት ዐውቀውና ተረድተው ይጠቀሙበት ዘንድ፡- የምሥራቹን ለዓለም ሁሉ የመናገር(የማስተማር፣ የመግለጥ)፤ ያመኑትን ምእመናን የመጠበቅና ምስጢራትን የመፈጸም፤ በራሳቸው ስንፍናና በመናፍቃን ቅሰጣ ከበረቷ የጠፉትን የመፈለግ፤ ኑፋቄ በተባለ የእምነት በሽታ የታመሙትንና የተለከፉትን የማከምና የማይድኑ ከኾነ ስለመንጋው ጤንነትና ስለ መናፍቁ በጎ ስትል እያዘነች በውግዘት የመለየት ተግባር አላት፡፡
ቅድስት ቤተ ክርስቲያን የእግዚአብሔር መንግሥት ወካይና መገለጫ ናት፡፡ ስለዚህ በሰማያዊቷ ኢየሩሳሌም፣ በእግዚአብሔር መንግሥት ተቀላቅሎና ተመሳስሎ መግባት እንደሌለ ሁሉ በዚህ ዓለም ያለችው ቤተ ክርስቲያንም የዚያ ወካይና መገለጫ ናትና የእርሷ ወገኖች ያልኾኑትን ትለያቸዋለች እንጂ፣ ጭፍን የምድራዊ መንግሥት ካድሬዎችና በመንግሥት የፀረ – አክራሪነት አጀንዳ ስም ስሑታኑ ከእነ ኑፋቄያቸው ወደ ቤተ ክርስቲያን ተመልሰው እንዲገቡና የልዩ እምነት ፍላጎታቸው የኾነውን የቤተ ክርስቲያናችንን መዳከምና መከፈፋል እንዲያሳኩላቸው ‹‹የአስተምህሮ መቻቻል ዴሞክራሲ›› ከንቱ ፕሮፓጋንዳ እንደሚነዙት አንዳንድ ባለሥልጣናት በዝምታ ወይም በግዴለሽነት አታዝላቸውም!!!
አንድ ምእመን በቤተ ክርስቲያን የሚኖረው በእውነትና በሃይማኖት እስከተገኘ ድረስ ብቻ ነው፡፡ ያን እምነትና እውነት ሲክድና ሌላ ባዕድ ነገር ውስጥ ሲገባ ግን ያንጊዜውኑ ከቤተ ክርስቲያን ራሱን በራሱ ያወጣል! በራሱ ድርጊት ራሱን ከድኅነት ውጭ ያደርጋል!! በመኾኑም በዚህ ዓለም ያለችው ቤተ ክርስቲያን አውግዛ የምትለየው ቀድሞውንም ራሱን በኑፋቄ አስተሳሰቡና ድርጊቱ ከቤተ ክርስቲያን የእውነት መሠረትና ዓምድ የለየውን ሰው ነው፡፡
ከቤተ ክርስቲያን ትምህርት ግልጽ ተቃርኖ የያዘ ኑፋቄ ሁሉ በአጠቃላይ የተወገዘ ነው፡፡ የታወቀና የተወገዘ ኑፋቄ ይዘው የሚነሡ ሰዎች አዲስ ነገረ ሃይማኖታዊ ውይይት አያስፈልጋቸውም፤ በቀደመው ውግዘት እስከ ዕለተ ምጽአት የሚነሡት ሁሉ ተወግዘዋልና፡፡ ለእንዲህ ዐይነቱ ኑፋቄ የሚያስፈልገው አንድ ነገር ብቻ ነው፤ እርሱም፡- ያን ኑፋቄ የሚያራምደው ግለሰብ በትክክል ያን ኑፋቄ መያዝ አለመያዙን፣ የሚመለስ መኾን አለመኾኑን ማረጋገጥ ብቻ ነው፡፡ ከተረጋገጠ በኋላ ያ ሰው ከቤተ ክርስቲያን መለየቱ(ማውገዙ) በአጥቢያ ሰበካ ጉባኤ ወይም በአገረ ስብከት ደረጃ ሊፈጸም ይችላል፡፡
ቤተ ክርስቲያን በኑፋቄ ተወግዘው (ይፋዊ በኾነ ውግዘት ይኹን ራሳቸውን በኑፋቄ በመለየታቸው) የተለዩ ሰዎች የመመለሳቸው ዜና ታላቅ የምሥራች ነው!! ከኑፋቄያቸው እንዲመለሱ የቤተ ክርስቲያን ናፍቆቷና ምኞቷ ነው፡፡ ቀድሞም እንዲወገዙ የሚደረገው፣ ነፍሳቸው በምጽአት ቀን እንድትድን ራሳቸው ሰዎቹን ለመርዳት ሲባል እንጂ እንዲጠፉ አይደለም፡፡ ስለኾነም በኑፋቄያቸው ጠፍተው ሲባዝኑ የቆዩቱ ስሕተታቸውን በርግጥ አምነው ወደ እናት ቤተ ክርስቲያናቸው ከመመለሳቸው የበለጠ ደስታ የለም፡፡
ነገር ግን፣ መናፍቃን የነበሩ ሰዎች ወደ ቤተ ክርስቲያን እንመለሳለን ሲሉ ሊደረጉ የሚገባቸው ዋና ዋና ጥንቃቄዎች እና ተግባራት አሉ፡፡ እኒህም፡-
  • እንመለሳለን የሚሉት ሰዎች በትክክል ከልባቸው ነው? ወይስ በንስሐ፣ ዕርቅና ይቅርታ ሰበብ እንደ ግብር አባቶቻቸው እንደ አርዮሳውያንና እንደ ሕንድ ማር ቶማ ቸርች ፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ ተገንጣዮች ውስጥ ገብተው ለመበጥበጥና ለመከፋፈል ነው? የሚለውን በሚገባ ማጤን ያስፈልጋል፡፡ ለዚህም ከቅዱስ ሲኖዶስ ጀምሮ እያንዳንዱ ምእመን ሊያተኩርበትና ግዴታውን ሊወጣ ይገባል፡፡
  • የጅምላ ንስሐ የለም! እንመለሳለን የሚሉ ወገኖችን ጉዳያቸውን በየግለሰቡ/እያንዳንዱ ጥፋቱ ምን እንደነበር፣ ለምን እመለሳለሁ እንዳለ፣ ወዘተ በዝርዝር መለየት፣ ማጥናትና መወሰን ይገባል እንጂ በጅምላ ከዚህ ወዲያ ወይም ከዚያ መለስ ብሎ ማድረግ አይገባም፡፡ ይህ እንመለሳለን ለሚሉትም ሰዎች፣ ለማኅበረ ምእመናኑም ጠቃሚና አስፈላጊ ነው፡፡ ያን ኑፋቄ ዳግመኛ ሲያስተምሩ ቢገኙ ማንነታቸውን በግልጽ ለመለየት ይጠቅማል፡፡
    Yared Ademe
    በዘማሪት ወ/ሮ ፋንቱ ወልዴ አቅራቢነት መስከረም ፰ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም ብፁዕ አቡነ ሉቃስንና ብፁዕ አቡነ ገብርኤልን በመኖርያ ቤቶቻቸው ተገኝቶ ይቅርታ የጠየቀውና ይቅርታ በመጠየቁ ይዞት ከወጣው ጠርዘኛ የፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ አቀንቃኝ ቡድን በተነሣበት ተቃውሞ አጣብቂኝ ውስጥ የገባው ዲ/ን ያሬድ አደመ
  • መናፍቃን ሲመለሱ በጓዳና ለሌሎች በማይታወቅ ኹኔታ ሳይኾን በግልጽ፣ ምእመናን ሁሉ በሚሰሙበትና በሚያውቁበት መድረክ በይፋ መኾን አለበት፡፡ በፊት የካዱት፣ ቤተ ክርስቲያንን ያሳጡትና የነቀፉት በይፋ እንደነበር ሁሉ ሲመለሱም በይፋ መኾን ይኖርበታል፡፡ መመለሳቸው በይፋ ከተደረገ፣ የቀድሞ ኑፋቄያቸውን እናስተምራለን ቢሉ እንኳ ‹‹ተመልሰናል ብላችሁ አልነበረምን? የቀድሞ ስሕተታችንን ትተናል ብላችሁ አልነበረምን?›› ብሎ ለመጠየቅና በቶሎ ማንነታቸውን ለማወቅ ይረዳል፡፡
  • የሚመለሱ መናፍቃን በእውነት ከመናፍቃን የተለዩና ከቅድስት ቤተ ክርስቲያን ጋራ የተዋሐዱ ስለመኾናቸው አንዱ ምስክር የሚኾነው ከቀድሞ  ጀምሮ  የተነሡ  ዋና  ዋና  የኑፋቄ አመንጪዎችን  በይፋ  በማውገዛቸው  ነው፡፡ ስለኾነም በጥንቃቄ በተዘጋጀ የመናፍቃን ዝርዝር ላይ እነዚያን መናፍቃን ማውገዝና ለዚህም መፈረም ይኖርባቸዋል፡፡ 
  • የሚመለሱ መናፍቃን እስከ ዛሬ ድረስ በስብከቶቻቸውና በመጻሕፍት ያስተማሯቸውንና የጻፏቸውን የኑፋቄ ትምህርቶች ሁሉ ቀድሞ ኑፋቄው ከተላለፈበት ልሳን (ሚዲያ) እና የሚዲያ ውጤቶች ዐይነትና ተደራሽነት ጋራ ተመጣጣኝ በኾነ መንገድ እንዲያወግዙና ስሕተት መፈጸማቸውን ተቀብለው ከአሁን በኋላ እንደዚያ ዐይነት የስሕተት ትምህርት እንደማያስተምሩ በጽሑፍ ቃል መግባት ይኖርባቸዋል፡፡ ይህም በተለያየ ጊዜና ቦታ በኑፋያሳሳቷቸው ሁሉ ስሕተታቸውን አምነው መመለሳቸውን እንዲረዱ፣ ወደ ስሕተታቸው ዳግመኛ በማይመለሱበትና በአስተማማኝ መልኩ ለመጥቀስና ምስክር ይኾንባቸ ዘንድ ነው፡፡
  • መናፍቃን ሲመለሱ በስሑት ትምህርታቸው የተነሣ ከእናት ቤተ ክርስቲያን ለመውጣታቸውና ለነፍሳቸው ጥፋት ምክንያት የኾኑባቸው ሰዎች እንዲመለሱ ጥረት ማድረግና መመለስ አለባቸው፡፡
  • የሚመለሱ መናፍቃን ከቀድሞ ጀምሮ የተነሡ ዋና ዋና የኑፋቄ አመንጪዎችን በይፋ እንዳወገዙ ሁሉ፣ የቤተ ክርስቲያኒቱን አስተምህሮ የሚቀበሉ ስለመኾናቸውም ግልጽና ጠንቃቃ ቃለ ጉባኤ አዘጋጅቶ እንዲፈርሙ ማድረግ ይገባል፡፡
  • ፍትሐ ነገሥታችን ለሌላው ሰው ክሕደት ምክንያት የሚኾን ሰው ሲመለስ ቀኖናው ከበድ ያለ እንዲኾን ያዝዛል፡፡ ስለዚህ ተመላሾቹ ከበድ ያለ ቀኖና ተሰጥቷቸውና በነገረ ሃይማኖት የበሰሉ ሊቃውንት ተመድበውላቸው ከእነርሱ መማራቸው ቅድሚያ ሊሰጠው ይገባል፡፡ ተመልሰናል የሚሉት ሰዎች መመለሳቸውና ንስሐቸው የእውነት መኾን አለመኾኑ የሚገለጥበትና የሚፈተንበት አንዱ መንገድም ይኽ ነው፤ የተመለሱት በእውነት ከኾነ ግድ እናስተምር፤ በመድረክ እንቀጥል አይሉም፤ ነገር ግን የተንኮልና የስልት ከኾነ መድረኩ ላይ ካልቀጠልን ብለው የሙጥኝ ይላሉ፡፡ እንመለስ የሚሉ ሰዎች ጭንቀታቸው መድረክ ላይ ስለ መዘመራቸውና ስለ መስበካቸው ከኾነ ጉዳዩ ዓላማን በውጭ ኾኖ ማስፈጸም ስለማይመች ወደ ውስጥ ገብቶ ተሐድሷዊውን ዓላማ ለማስፈጸም የአስገቡኝ ጥያቄ እንጂ የመመለስና የንስሐ ጥያቄ አይደለም ማለት ነው፡፡ ይኼ የድርድር እንጂ የንስሓ መንገድ አይደለም፡፡
    Begashaw Dessalegn
    በዘማሪት ወ/ሮ ፋንቱ ወልዴ አቅራቢነት መስከረም ፰ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም ብፁዕ አቡነ ሉቃስንና ብፁዕ አቡነ ገብርኤልን በመኖርያ ቤቶቻቸው ተገኝቶ በግል ስላደረገባቸው መደፋፈር ይቅርታ የጠየቀውና ይቅርታ በመጠየቁ ይዞት ከወጣው ቡድን ጋራ ውዝግብ ውስጥ የገባው የቅ/ሲኖዶስ ፍርደኛ በጋሻው ደሳለኝ
  • የጠፉትን መቀበል ተገቢና መልካም ቢኾንም በሌላ በኩል ደግሞ በዚህ ሂደት የሚደረገው እያንዳንዱ ነገር ሊያስከትል የሚችለውን አደጋ አርቆ ማየት ያስፈልጋል፤ የተመላሾቹን ጭምብሎቻቸውን ገልጦ ትክክለኛ ማንነታቸውንና አደጋውን መረዳትና መለየት ያስፈልጋል፡፡ ‹‹ሰላም ሰላም›› በሚል ቃል ብቻ እውነተኛ የቤተ ክርስቲያንን ውሳጣዊ ሰላም፣ እንዲሁም ጊዜያዊ ችግር የፈታንና ያቃለልን ሲመስለን ለወደፊቱ ችግር እያወሳሰብንና እያቆላለፍን እንዳይሆን መጠንቀቅ ያስፈልጋል፡፡ ለዚህ ደግሞ በቅርብ ጊዜ ከስድስቱ አኃት አብያተ ክርስቲያናት መካከል አንዷ በኾነችው በሕንድ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የኾነውን አሳዛኝ ነገር ልንረሳው አይገባንም፡፡
  • ከቤተ ክርስቲያን ታሪክ እንደተማርነው፣ እንመለሳለን ባይ መናፍቃን የፖለቲካ ሰዎችንና ባለሥልጣናትን በመዘወርና ከጎናቸው በማሰለፍ በኩል ይዋጣላቸዋል፡፡ በኒቅያ ጉባኤ በቅዱሳን አባቶች ተወግዞ የተለየው አርዮስና የኑፋቄ ጓደኞቹ የተለያዩ ሰዎችን በመላክና በውስጥ ለውስጥ በሠሩት የፕሮፓጋንዳ ሥራ ንጉሥ ቆስጠንጢኖስ አርዮስን ከፈረደበት ከግዞቱ እንዲወጣና ወደ ቤተ መንግሥቱ እንዲመጣ ካደረጉ በኋላ ቅዱስ አትናቴዎስን ጨምሮ ኦርቶዶክሳውያን ጳጳሳትንና ካህናትን ከየመናብርታቸውና አብያተ መቅደሳቸው እያሳደዱ ሲፈነጩባቸው ኖረዋል፡፡ ዛሬም እውነተኛ ዓላማቸው የተነቃባቸው እንመለሳለን ባይ መናፍቃን፣ ለቤተ ክርስቲያናቸው ቀናዒ የኾኑ አገልጋዮችንና ምእመናንን የመንግሥት የወቅቱ አጀንዳ በኾነው የፀረ አክራሪነት እንቅስቃሴ ተሸፍነው በጽንፈኝነት ውንጀላ ማሸማቀቃቸው የባሕርያቸው ነው፡፡
  • እንመለሳለን ለሚሉ ግለሰቦችና ቡድኖች በሽምግልና ይኹን በአጣሪነት ከሚሳተፉ ሰዎች አንዳንዶቹ፣ ‹‹ዕርቅን ማን ይጠላል? ይቅርታና ሰላም ምን ክፋት አለው›› በሚሉ መሸፈኛዎች ከመታለልና ከማታለል መጠበቅ ይገባቸዋል፡፡ ይልቁንስ ይቅርታ ጠያቂዎቹና እንመለሳለን ባዮቹ ከጠየቁት ጉዳይ ጋራ በተያያዘ ምን እያደረጉ እንደነበርና ምን በማድረግ ላይ እንደኾኑ ለመመርመር ብስለቱና ቅንነቱ ሊኖራቸው ያስፈልጋል፡፡
  • ራሳቸውን በአስታራቂነት ጎራ መድበው፣ እነርሱ ከሌሎቹ የተሻሉ አስተዋዮችና ያላከረሩ ብልሆች እንደኾኑ አድርገው ራሳቸውን የሚቆጥሩ ሰዎች÷ አስታረቁ ተብለው ስም ለማሰርና ጀብድ እንደሠሩ ለመቆጠር፣ በስሕተቱ ተለይቶ የወጣውን አካል በሽፍንፍን በመመለስ በሌሎች አጀንዳዎች ከተቀየሙት አካል በተፃራሪ በወደረኛነት በማሰለፍና ጎልቶ በመታየት እንበቀላለን ብለው የሚንቀሳቀሱ ግለሰቦች ይኸው ፍላጎታቸው ሊጋለጥ ደረጃቸውን ዐውቀው አድበው እንዲቀመጡ ሊደረግ ይገባል!!

2013 ኦገስት 15, ሐሙስ

፯. መናፍቃን የሚወገዙት እንዴት ነው?
የመናፍቃን አወጋገዝ ሂደት እንደ ኑፋቄው ዓይነት ነው፡፡ የኑፋቄው ዓይነት ምንድን ነው? የሚለውን ማጤን ይገባል፡፡ ይህም:-
  • የታወቀ ኑፋቄ፣ እና
  • እንግዳ ዓይነት ኑፋቄ
የታወቀ ኑፋቄ - ስንል
ሀ. ከመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርትና ከቤተ ክርስቲያን ትውፊት ጋር ተቃርኖው ግልጽና የማያሻማ የሆነ ኑፋቄ፣ እና
ለ. ከዚያ በፊት በአካባቢያዊም ሆነ በዓለም አቀፋዊ ጉባኤ የተወገዘ ኑፋቄ ማለታችን ነው፡፡
እንዲህ ያለ ኑፋቄ ይዞ ለሚነሣ ሰው አዲስ ነገረ ሃይማኖታዊ ውይይትና ውሳኔ አያስፈልገውም፡፡ የአርዮስን ኑፋቄ ይዞ ለሚነሣ ግለሰብም ሆነ ቡድን የኒቅያ ጉባኤ በየጊዜው ሲሰበሰብ አይኖርም፤ የንስጥሮስን ኑፋቄ ይዞ ለሚነሣም እንዲሁ የኤፌሶን ጉባኤ በየጊዜው አይሰበሰብም፡፡ በቀደመው ውግዘት እስከ ዕለተ ምጽአት የሚነሡት ሁሉ ተወግዘዋል፡፡ ከቤተ ክርስቲያን ትምህርት ግልጽ ተቃርኖ የያዘ ኑፋቄ ሁሉ በአጠቃላይ የተወገዘ ነው፡፡ ለእንዲህ ዓይነቱ ኑፋቄ የሚያስፈልገው አንድ ነገር ብቻ ነው፤ እርሱም ያን ኑፋቄ የሚያራምደው ግለሰብ በትክክል ያን ኑፋቄ መያዝ አለመያዙን፣ የሚመለስ መሆን አለመሆኑን ማረጋገጥ ብቻ ነው፡፡ ከተረጋገጠ በኋላ ያ ሰው ከቤተ ክርስቲያን መለየቱ (ማውገዙ) በአጥቢያ ሰበካ ጉባኤ ወይም በአገረ ስብከት ደረጃ ሊፈጸም ይችላል፡፡
እንግዳ ዓይነት ኑፋቄ ሲባል ደግሞ በግልጽ ስህተቱ ይህ ነው ለማለት ቀላል ያልሆነና ጉዳዩን ከቤተ ክርስቲያን እምነት አንጻር በጥንቃቄ መመዘን የሚያስፈልገው ማለት ነው፡፡ እንዲህ ሲሆን የኑፋቄውን ምንነት፣ ነገረ ሃይማኖታዊ አንድምታውን፣ ጥልቀቱንና ስፋቱን በጥንቃቄ መመርመር ያስፈልጋል፡፡ ይህን የሚያደርጉትም በሳል የሆነ ነገረ ሃይማኖታዊ እውቀት ያላቸው ሊቃውንት መሆን ይኖርባቸዋል፡፡ የመጨረሻ ውሳኔውን የሚሰጠው የቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ነው፡፡

፰. መናፍቃን እንዴት ይመለሱ?

ከቤተ ክርስቲያን በኑፋቄ ተወግዘው (ይፋዊ በሆነ ውግዘትም ሆነ ራሳቸውን በኑፋቄ በመለየታቸው) የተለዩ ሰዎች እንዲመለሱ የቤተ ክርስቲያን ናፍቆቷና ምኞቷ ነው፡፡ እንዲወገዙ የሚደረገውም ከላይ እንዳየነው ለራሳቸው ለሰዎቹ ጥቅም ሲባል፣ ነፍሳቸው በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ቀን እንድትድን ለመርዳት ሲባል እንጂ እንዲጠፉ አይደለም፡፡ ስለሆነም የመመለሳቸው ዜና ታላቅ የምሥራች ነው፣ ከዚህ የበለጠ ደስታም የለም፡፡ ጌታችን በትምህርቱ የጠፋው ልጅ ሲመለስ ስለሆነው ነገር ሲናገር እንዲህ አለ፡- “አባቱ ለአገልጋዮቹ ፈጥናችሁ ከሁሉ የተሻለ ልብስ አምጡና አልብሱት፣ ለእጁ ቀለበት ለእግሩም ጫማ ስጡ፤ የሰባውን ፊሪዳ አምጥታችሁ እረዱት፥ እንብላም ደስም ይበለን፤ ይህ ልጄ ሞቶ ነበርና ደግሞም ሕያው ሆኖአል፤ ጠፍቶም ነበር ተገኝቶአልም። ደስም ይላቸው ጀመር፡፡” ሉቃ. 15፡22-24 ቅድስት ቤተ ክርስቲያን አንድ የጠፋ ልጇ ሲመጣ እንዲህ ደስ ይላታል፡፡ ቅዱሳን መላእክትም በሰማይ ንስሐ ስለሚገባ አንድ ኃጥእ ደስ ይሰኛሉ፡፡
ይህ እንዳለ ሆኖ፣ በሌላ በኩል ደግሞ ሊደረጉ የሚገባቸው ጥንቃቄዎችና ተግባሮችም አሉ፡፡ ይህም ቤተ ክርስቲያንን ከመጠበቅ አንጻር አስፈላጊ በመሆኑ ነው፡፡ መናፍቃን የነበሩ ሰዎች ወደ ቤተ ክርስቲያን እንመለሳለን ሲሉ ሊደረጉ የሚገባቸው ዋና ዋና ጥንቃቄዎችና ተግባራት የሚከተሉት ናቸው፡-
1. መመለሳቸው (ተመልሰናል ማለታቸው) የእውነት ነው? ከልብ ነው? ወይስ ለስልትና ለዘዴ ነው?
ቤተ ክርስቲያን እስካሁን በተጓዘችባቸው ዘመናት ሁለቱም ዓይነት ሰዎች በየጊዜው ሲገጥሟት ነበር፤ እነዚህም በአንድ በኩል በእውነት ተጸጽተው የሚመለሱ ሲሆኑ በሌላ በኩል ደግሞ ከልባቸው ሳይመለሱ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ተመልሰው በመግባት ብዙ ምእመናንን ለመበረዝና ለማታለል ያመቻቸው ዘንድ በተንኮል ተመልሰናልና ተቀበሉን የሚሉ ናቸው፡፡ ስለዚህ ተመልሰናል ስላሉ ብቻ ዝም ብሎ መቀበል የዋህነት ሳይሆን ጅልነት ስለሆነ በሚገባ ማጣራትና መጠንቀቅ በእጅጉ አስፈላጊ ነው፡፡
በኒቅያ ጉባኤ በቅዱሳን አባቶች ተወግዞ የተለየው አርዮስና የኑፋቄ ጓደኞቹ የተለያዩ ሰዎችን በመላክና በውስጥ ለውስጥ በሠሩት የፕሮፓጋንዳ ሥራ በመጨረሻ ላይ ንጉሥ ቆስጠንጢኖስ አርዮስን ከፈረደበት ከግዞቱ እንዲወጣና ወደ ቤተ መንግሥቱ እንዲመጣ አደረገው፡፡ ንጉሥ ቆስጠንጢኖስም እምነቱን በጽሑፍ እንዲያቀርብ አዘዘው፡፡ አርዮስም በፊት የፈጠራቸውን የኑፋቄ ቃላትና ሐረጎች ሁሉ፣ እንዲሁም የተወገዘባቸውን የክህደት አንቀጾች ሁሉ ለጊዜው ወደ ጎን ትቶ ከመጽሐፍ ቅዱስ በቀጥታ ያሉና ማንም ሰው ሊቀበላቸው የሚችላቸውን ነገሮች ብቻ ጽፎ “በፊትም ቢሆን ከዚህ የተለየ ሃሳብም ሆነ እምነት አልነበረኝ፣ አሁንም የማምነው ይህን ነው” በማለት ፈርሞ፣ በመሐላ አጽንቶ ሰጠው፡፡ ያ አርዮስ ጽፎ የሰጠው አንቀጸ እምነት እነርሱ (አርዮሳውያን) በፈለጉት መንገድ ሊተረጉሙትና የያዙትን አርዮሳዊ እብደት በቀላሉ በማያጋልጥ መልኩ በፈሊጥ ተሸፍኖ የቀረበ ማታለያ ነበር፡፡ ንጉሥ ቆስጠንጢኖስ ግን እንዲያ ሲያደርግ ሲያየው አርዮስ በእውነት የተመለሰና ኦርቶዶክሳዊ የሆነ መሰለው፡፡
ይህን አጋጣሚ በመጠቀም አርዮሳውያን የነበሩ ጳጳሳት አርዮስ በይፋ መጀመሪያ በተወገዘበት በእስክንድርያ ወደ ቤተ ክርስቲያን እንዲገባና ከምሥጢራት እንዲካፈል የሚል ደብዳቤ ንጉሡ እንዲጽፍላቸው አደረጉና ያን ደብዳቤ ከዛቻና ከማስፈራሪያ ጋር ወደ ቅዱስ አትናቴዎስ ወደ እስክንድርያ እንዲላክ አደረጉ፡፡ ለየአብያተ ክርስቲያናቱም አርዮስና ጓደኞቹ ኦርቶዶክሳውያን መሆናቸውን ንጉሡ ቆስጠንጢኖስ የመሰከረላቸው ስለሆነ፣ በሲኖዶስም የተወሰነ በመሆኑ ወደ ቤተ ክርስቲያን አንድነትና ወደ ሱታፌ ምሥጢራት ይቀበሏቸው ዘንድ በጥብቅ የሚያሳስብ ደብዳቤ በፍጥነት ላኩ፡፡ የአርዮስ ቀኝ እጅ የነበረው አውሳብዮስ ዘኒቆምድያ ንጉሥ ቆስጠንጢኖስ በደብዳቤው ላይ ቅዱስ አትናቴዎስን “ወደ ቤተ ክርስቲያን ሊመለሱ የሚፈልጉትን ሁሉ የማትቀበል ከሆነ እኔ ራሴ ሰው ልኬ ከመንበርህ አወርድሃለሁ” የሚል ዛቻ እንዲላክበት አደረገ፡፡ ብዙ ጊዜ ከታሪክ ስናይ መናፍቃን የፖለቲካ ሰዎችንና ባለ ሥልጣናትን በመዘወርና ከጎናቸው በማሰለፍ በኩል ጠንካሮችና የተሳካላቸው ናቸው፡፡ ቅዱስ አትናቴዎስ ግን “የክርስቶስ ጠላት የሆነው አርዮስና ኑፋቄው ከኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ጋር ምንም ኅብረት የላቸውም” በማለት በጉባኤ የተወገዘውን አርዮስን በንጉሥ ቀላጤ አልቀበልም አለ፡፡ የቅዱስ አትናቴዎስ ስለ ኦርቶዶክሳዊት ሃይማኖት ከአርዮሳዊ ክህደት አቀንቃኞችና ደጋፊዎች ጋር የገባው እልህ አስጨራሽ ትግል በዚህ ሁኔታ እየጠነከረ ሄደ፡፡ ከመንበሩ ስድስት ጊዜ እንዲሳደድና ከአርባ አምስት ዓመት ዘመነ ፕትርክናው አሥራ ሰባት ዓመቱን ያህል በስደትና በእንግልት እንዲያሳልፍ ያደረገው ይህ የአርዮሳውያን ተንኮልና ዘመቻ ነበር፡፡
በአጠቃላይ አርዮሳውያን ያን ንጉሡ ከግዞት መመለሱን እንደ መልካም ካርድ በመጠቀም ከዚያ ቀጥሎ በነበሩት ሃምሳ ዓመታት ያህል ቤተ ክርስቲያንን በእጅጉ ሲያውኳትና ሲፈትኗት ኖረዋል፡፡ ነገሥታትን ሳይቀር ከጎናቸው እያሰለፉ ኦርቶዶክሳውያን ጳጳሳትንና ካህናትን ከየመናብርታቸውና አብያተ መቃድሳቸው እያሳደዱ እነርሱ ሲፈነጩባቸው ኖረዋል፡፡ ነገሩ የማታ የማታ እውነት ይረታ ሆነ እንጂ፡፡
ስለዚህ ዛሬም እንመለሳን የሚሉት ሰዎች በትክክል ከልባቸው ነው? ወይስ እንደ ግብር አባቶቻቸው እንደ አርዮሳውያን ውስጥ ገብተው ለመበጥበጥ ነው? የሚለውን በሚገባ ማጤን ያስፈልጋል፡፡ “ታሪክ የሚያስተምረው ሰዎች ከታሪክ አለመማራቸውን ነው” የተባለው እንዳይደርስብን ማሰብ ይገባል፡፡ “በሬ ሆይ፣ ሣሩን አየህ እንጂ ገደሉን ሳታይ” እንደ ተባለውም እንዳይሆን እያንዳንዱ ምእመን፣ እስከ ቅዱስ ሲኖዶስ ድረስ ሊያስቡበትና ተገቢውን ነገር ሊያደርጉበት የሚገባ ጉዳይ ነው፡፡
2. ጉዳዮችን በቡድን ወይም በጅምላ ሳይሆን በእያንዳንዱ ሰው ደረጃ መመልከትና መለየት፣
እንመለሳለን የሚሉትን ወገኖቻችንን ጉዳያቸውን በእያንዳንዳቸው ማየትና ማጥናት ይገባል እንጂ በጅምላ ከዚህ ወዲያ ወይም ከዚያ መለስ ብሎ ማድረግ አይገባም፡፡ እግዚአብሔር የሚፈርደው በእያንዳንዱ ሰው እንጂ በቡድን ወይም በጅምላ አይደለም፤ “እስመ አንተ ትፈድዮ ለኩሉ በከመ ምግባሩ - አንተ ለእያንዳንዱ እንደ ሥራው ታስረክበዋለህና” እንደ ተባለ፡፡ መዝ. 61፡ እንዲሁም “እንግዲያስ እያንዳንዳችን ስለ ራሳችን ለእግዚአብሔር መልስ እንሰጣለን” ተብሏልና። ሮሜ 14፡12 ስለሆነም እያንዳንዱን በየግለሰቡ ጥፋቱ ምን አንደ ነበር፣ ለምን እመለሳለሁ እንዳለ፣ ወዘተ በዝርዝር ማጥናትና መወሰን ይገባል እንጂ “እነ እገሌ” በሚል የጅምላ ንስሐ የለምና ይህን ማስታወሱም ተገቢ ነው፡፡
3. ከቤተ ክርስቲያን እንዲወጡ (እንዲያፈነግጡ) ያደረጓቸውን ምክንያቶች በሙሉ እንዲዘረዝሩ ማድረግና መመዝገብ፣
አንድ ሰው ዳነ ሲባል ታምሞ የነበረ መሆኑ፣ ተመለሰ ሲባል ደግሞ ወጥቶ ወደ ሌላ ሄዶ የነበረ መሆኑን ያጠይቃልና እንመለሳለን የሚሉት ሰዎች እያንዳንዳቸው ቀድሞ እንዲወጡ ያደረጋቸው ምክንያት ምን እንደ ነበረ በግልጽ መታወቅ ይኖርበታል፡፡ አለበለዚያ በሽታውን ደብቆ እንዲሁ አክሙኝ እንደሚል ሰው መምሰል ይሆናል፡፡ ይህን ማድረግ ግን እንመለሳለን ለሚሉት ሰዎችም፣ ለማኅበረ ምእመናኑም ጠቃሚና አስፈላጊ ነው፡፡ ያን ኑፋቄ እንደገና ሲያስተምሩ ቢገኙ ማንነታቸውን በግልጽ ለመለየት ይጠቅማል፤ አለበለዚያ “ሞኝን እባብ ሁለት ጊዜ ነከሰው” (መጀመሪያ ሲያይ፣ ሁለተኛ ደግሞ ሲያሳይ) እንደ ተባለው ይሆናል፡፡
4. መመለሳቸውን፣ እንዲሁም ከምን ዓይነት ስህተት እንደ ተመለሱ ለሕዝቡ በይፋ መነገር ይኖርበታል፡፡
መናፍቃን ሲመለሱ በጓዳና ለሌሎች በማይታወቅ ሁኔታ ሳይሆን በግልጽ፣ ምእመናን ሁሉ በሚሰሙበትና በሚያውቁበት መድረክ በይፋ መሆን አለበት፡፡ በፊት የካዱትና ቤተ ክርስቲያንን ያሳጡትና የነቀፉት በይፋ እንደ ነበር ሁሉ ሲመለሱም በይፋ መሆን ይኖርበታል፡፡ ቅዱስ ባስልዮስ ስለ መናፍቃን አመላለስ በጻፈው ቀኖና ላይ እንዲህ ይላል፡-


“በማንኛውም መንገድ ቢሆን ከኑፋቄ ወደ ቤተ ክርስቲያን የሚመለሱ ሰዎች ምእመናን ባሉበት መሆን አለበት፤ ወደ ምሥጢራት ሊቀርቡ የሚገባቸውም እንዲህ ባለ ይፋዊ ሁኔታ ካለፉ በኋላ ብቻ ነው፡፡” ቀኖና ዘቅዱስ ባስልዮስ፣ ቁ. 1
እንዲህ ካልሆነ ብዙ ችግር ያስከትላል፡፡ እንዲህ ማድረግ ለአጭበርባሪዎችና ለተንኮለኞች መጠቀሚያ ሰፊ በር ይከፍታል፡፡ ነገ ተመልሰው ያንኑ ዓይነት ችግር እንዳይፈጥሩ በይፋ መነገሩ በእጅጉ ይጠቅማል፡፡ አለበለዚያ ውስጥ ውስጡን ምእመናንን እየበከሉ ላለመቀጠላቸው ዋስትና አይኖርም፡፡ መመለሳቸው በይፋ ከተደረገ ግን የቀድሞ ኑፋቄያቸውን እናስተምራለን ቢሉ እንኳ “ተመልሰናል ብላችሁ አልነበረምን? የቀድሞ ስህተታችንን ትተናል ብላችሁ አልነበረምን?” ብሎ ለመጠየቅና በቶሎ ማንነታቸውን ለማወቅ ይረዳል፡፡
5. ከጥንት ጀምሮ የተነሡ የተለያዩ የኑፋቄ መሪዎችንና ዋና ዋና መናፍቃንን በጥንቃቄ ከተዘረዘሩ በኋላ ማውገዝ ይገባቸዋል፣
የሚመለሱ መናፍቃን በእውነት ከመናፍቃን የተለዩና ከቅድስት ቤተ ክርስቲያን ጋር የተዋሐዱ ስለ መሆናቸው አንዱ ምስክር የሚሆነው ከቀድሞ ጀምሮ የተነሡ ዋና ዋና የኑፋቄ አመንጪዎችን በይፋ ማውገዝ ነው፡፡ ስለሆነም በጥንቃቄ በተዘጋጀ የመናፍቃን ዝርዝር ላይ እነዚያን መናፍቃን ማውገዝና ለዚህም መፈረም ይኖርባቸዋል፡፡
6. እስከ ዛሬ ድረስ በስብከቶቻቸውና በመጻሕፍት ያስተማሯቸውንና የጻፏቸውን የኑፋቄ ትምህርቶች ሁሉ ቀድሞ ኑፋቄው ከተላለፈበት ልሳን ጋር ተመጣጣኝ በሆነ መንገድ እንዲያወግዙና ስህተት መፈጸማቸውን ተቀብለው ከአሁን በኋላ እንደዚያ ዓይነት የስህተት ትምህርት እንደማያስተምሩ በጽሑፍ ቃል መግባት ይኖርባቸዋል፡፡
የስህተት ትምህርቱን በመጽሐፍ ወይም በቪሲዲ ወይም በካሴት እና በመሳሰለው ያስተላለፈ ሰው ስህተቱን ሲያምንና ወደ እውነት ሲመለስ የቀደመውን አስተምህሮውን ስህተትነት መግለጽ የሚገባው በዚያው የስህተት ትምህርቱን ባስተላለፈበት መንገድ (ልሳን - ሚዲያ) ነው፡፡ አለበለዚያ ተደራሽነቱ ተመጣጣኝ አይሆንም፡፡ የስህተት ትምህርቱን በመጽሐፍ የጻፈ ሰው በቃሉ “አጥፍቼ ነበር፣ አሁን ተመልሻለሁ” ቢል መመለሱንና የቀድሞውን አስተምህሮውን ስህተትነት ማመኑን የሰሙት በተናገረበት ጊዜና ቦታ የሚገኙት ሰዎች ብቻ ናቸው፤ ሌሎቹ ግን በመጻሕፍት የተጻፈውን ኑፋቄውን እንጂ በቃል የተናገረውን የሚያውቁበት መንገድ የለም፡፡ እንዲሁም በቃሉ ብቻ “ያ ቀድሞ ያልሁት ስህተት ነው” ብሎ ቢናገር ያ ነገር ከአንድ ትውልድ ያለፈ ሊታወስና አስተማማኝ በሆነ ሁኔታ ሊጠቀስ አይቻልም፣ መጽሐፉ ግን ለዘመናት ትውልድን እየተሻገረ ሊጠቀስ የሚችል ነው፡፡
ስለሆነም በእነዚህና በሌሎችም ምክንያቶች አንድ ወደ ቤተ ክርስቲያን የሚመለስ ሰው ቀድሞ የስህተት ትምህርቱን ካስተማረበት የሚዲያ ዓይነትና ተደራሽነት ጋር ተመጣጣኝ በሆነ መንገድ መግለጽ ይኖርበታል፡፡ አለበለዚያ ቀድሞ በቤተ ክርስቲያን ላይ ለብዙዎች መሰናከያ አድርጎ ያስተማረው እንክርዳድ መበከሉን እየቀጠለና ትውልድ እየተሻገረ ስለሚሄድ ስለ አንዱ ሰው መመለስ እንደምንጨነቀው ሁሉ ይህ ሰው በኑፋቄ ትምህርቱ ስላጠፋቸው ስለ ብዙዎቹም ማሰብ የግድ ይላል፡፡ አለበለዚያ ያ ሰው ያጠፋቸውን የብዙዎቹን ሰዎች ነፍሳት ረስተን ለአንዱ ብቻ የተጨነቅን መስሎን የምናደርገው ነገር ውስጡ ወይ አለመረዳት ወይም ደግሞ ሌላ ነገር እንዳይሆን ማሰብ ይገባል፡፡
7. በእርሱ የኑፋቄ ትምህርት ምክንያት ከቤተ ክርስቲያን የወጡትን ወደ ቤተ ክርስቲያን መመለስ ይኖርበታል፡፡
ኑፋቄውን በማስተማሩ ምክንያት ለብዙዎች ከቤተ ክርስቲያን መውጣት ምክንያት የሆነና በነፍሳቸው እንዲሞቱ ያደረገ ሰው ሲመለስ በመጀመሪያ እነዚያ ያጠፋቸውን ወደ ቤተ ክርስቲያን መመለስ ይኖርበታል፡፡ መርቅያን የተባለው መናፍቅ ብዙ ሰዎችን ካጠፋና የራሱን አንጃ መሥርቶ ከኖረ በኋላ በሕይወቱ መጨረሻ አካባቢ በኑፋቄው ተጸጽቶ ወደ ቤተ ክርስቲያን ልመለስ ብሎ ጠይቆ ነበር፡፡ የቤተ ክርስቲያን አባቶች ከሁሉም አስቀድሞ በመጀመሪያ ማድረግ እንዳለበት የነገሩት ነገር ቢኖር ወደ ስህተት የመራቸውን ሁሉ ወደ ቤተ ክርስቲያን እንዲመልስ ነበር፡፡ ያን ለማድረግ በመሯሯጥ ላይ እያለ ታመመና ሞተ፡፡ ይህ በየዘመናቱ እንመለስ ሲሉ በነበሩ ሰዎች ላይ ሲፈጸም የኖረ ቀኖና ነው፡፡ ሽዎችን አጥፍቶ አንድ እርሱ ብቻ ቢመለስ እግዚአብሔር ስለ ጠፉት ስለ ብዙዎቹ ግድ የለውምን? እንዲህ የሚያደርጉትንስ ዝም ብሎ ይመለከታቸዋልን? ስለዚህ ይህን ጉዳይ መዘንጋት አይገባም፣ ለመጥፋታቸው ምክንያት የሆኗቸውን ሰዎች (በእነርሱ ምክንያት የጠፉትን ሁሉንም ለይቶ ማወቅ ባይቻልም እንኳ) ለመመለስ ከፍተኛ ጥረት ማድረግና መመለስ ይኖርባቸዋል፡፡


8. እያንዳንዳቸውን በኦርቶዶክሳዊ መንገድ የሚመራቸው በነገረ ሃይማኖት በሳል የሆኑ አባቶችን መመደብ፣
ኦርቶዶክሳዊነት ከሁሉም በላይ እሳቤው፣ መንፈሱ እንዲገባቸውና እንዲሠርጻቸው ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ የቤተ ክርስቲያኒቱን ትምህርቷን ሳያውቁ፤ ከሁሉም በላይ ደግሞ ኦርቶዶክሳዊ እሳቤና እይታ እንዲሁም መንፈስ ሳይኖራቸው በሌላ ቅኝት መንፈስ የኖሩ ሰዎች እንደ መሆናቸው እንመለስ ስላሉ ብቻ አብሯቸው የኖረውና የሠረጻቸው የኑፋቄ ትምህርትና መንፈስና እንዲሁ በአንድ ጊዜ ውልቅ ብሎ የሚወድቅ አይደለም፡፡ የያዛቸው የኑፋቄ መንፈስ እንዲለቃቸው፣ እርሾው ጭልጥ ብሎ እንዲጨለጥላቸው ማድረግ ይገባል፡፡ ይህ ደግሞ በአንድ ጀምበር የሚፈጸም አይደለም፡፡ ጌታችን “ዝንቱ ዘመድ ኢይወጽእ ዘእንበለ በጾም ወበጸሎት - ይህ ዓይነት አብሮ አደግ ክፉ መንፈስ ያለ ጾምና ጸሎት አይወጣም” እንዳለ፡፡ ስለዚህ ኦርቶዶክሳዊ ነገረ ሃይማኖታዊ መንፈስንና እይታን፣ ኦርዶክሳዊ አስተምህሮንና በአጠቃላይ ኦርቶዶክሳዊ ክርስትና ምን እንደሆነ በበሰለ እውቀት፣ በእውቀት ብቻም ሳይሆን በሕይወት የሚያስተምራቸው በሳል አባት ያስፈልጋቸዋል፡፡ ቆዳ በማውለቅና ልብስ በመቀየር ብቻ ከኑፋቄ ወደ ኦርቶዶክሳዊነት መመለስ አይቻልም፡፡
ባለፉት የቅርብ ጊዜያት (በ1990ዎቹ ዓመታት) በሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ ከፍተኛ መንፈሳዊ ትምህርት ቤት ተፈጥሮ በነበረው ችግር ምክንያት ቅዱስ ሲኖዶስ ካጣራ በኋላ በሃይማኖት ችግር (በተሐድሶነት) የተጠረጠሩትን ወደ አንዳንድ ቦታዎች ሄደው የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት እንዲማሩ ተብሎ ነበር፡፡ ከእነዚያ ለቀኖና ተብለው ከተላኩት መካከል ግን አጋጣሚውን ሌላ ጥፋት ለመሥራት እንደ ምቹ አጋጣሚ የተጠቀሙበት ነበሩ፡፡ ከዚህም የተነሣ እየተማሩ ይቆዩ ተብለው ከተላኩት መካከል ሌሎችን የቤተ ክርስቲያን አባቶች አስክደው ወደ እነርሱ የጥፋት መንገድ ለማስገባት የተጠቀሙበት ነበሩ፡፡ ሌሎች ደግሞ የፕሮቴስታንታዊ ትምህርቶችን በተለያዩ መንገዶች ለማስፋፋት ሲሞክሩ የተደረሰባቸው ነበሩ፡፡ ስለዚህ ያን ጊዜ እንደ ተደረገው እንዲሁ ሁለት ሁለት እያደረጉ ወደ ሆነ ገዳም ወይም ቦታ መላክ ብቻውን ሰዎቹን አይለውጣቸውም፡፡ ስለዚህ በዚህም ከፍተኛ ሥራና ጥንቃቄ ያስፈልጋል፡፡ “ከሞኝ ደጅ ሞፈር ይቆረጣል” እንደሚባለው እንዳይሆን፡፡
9. የቤተ ክርስቲያኒቱን አስተምህሮ የሚቀበሉ ስለ መሆናቸው ግልጽና ጠንቃቃ የሆነ ቃለ ጉባኤ አዘጋጅቶ እንዲፈርሙ ማድረግ
ይህም አስፈላጊ ነው፡፡ የሰው ነገር ነገ የሚሆነው ስለማይታወቅ ለወደፊቱም ጥሩ መሠረትና ማስረጃ፣ ምስክርም ይሆን ዘንድ የቤተ ክርስቲያኒቱን አስተምህሮና ሥርዓት ያለ አንዳች ቅሬታ የሚቀበሉ ስለመሆናቸው ቃለ ጉባኤ ተይዞ በሚዘጋጅ ወረቀት ላይ መፈረም ይኖርባቸዋል፡፡
10. ቀኖና መስጠት - (በመድረክ ላይ ይቀጥላሉ ወይስ አይቀጥሉም?)
ይህ ለአባቶች የሚተው ጉዳይ ቢሆንም እዚህ ላይ ያነሣነው እንዲሁ ለትምህርት ያህል ግን አስፈላጊነቱን ሳይጠቅሱ ማለፍ አይገባም በሚል ነው፡፡ እንዲያውም ፍትሐ ነገሥታችን ለሌላው ሰው ክህደት ምክንያት የሚሆን ሰው ሲመለስ ቀኖናው ከበድ ያለ እንዲሆን ያዝዛል፡-
“ወለዘኢአከሎ ክሕደቱ ባሕቲቱ እስከ ያወጽኦ ለካልኡ እምሃይማኖቱ ወኮነ ምክንያተ ለክህደቱ ይኩን ንስሓሁ ፈድፋደ - የራሱ ክህደት ብቻ አልበቃው ብሎ ባልንጀራውን ከሃይማኖቱ እስኪያወጣው ድረስ ለመካድ ምክንያት ቢሆን ንስሓው ጽኑዕ ይሁን፡፡” አንቀጽ ፳ ቁ. ፯፻፷
ከዚሁም ጋር ገና ተመለስን እንዳሉ “በዚያው በለመድነው ማስተማራችንን እንቀጥላለን፣ ከመድረክ አንወርድም የሚሉ ከሆነም ሌላ መታየት ያለበት ጉዳይ ነው፡፡ በመጀመሪያ አንድ ሰው ቀኖናውን ሳይጨርስ እንዲያ ማድረግ ተገቢ መሆን አለመሆኑን ማየት ያስፈልጋል፡፡ ከዚህም በላይ ደግሞ አንድ በኑፋቄ የነበረ ሰው እንዲሁ “ተመልሻለሁ” ስላለ ብቻ በውስጡ የነበረው ኑፋቄ በአንድ ጊዜ በተአምራት በኦርቶዶክሳዊ ትምህርት አይሞላም፡፡ ስለዚህ በመድረክ እቀጥላለሁ ካለ የሚያስተምረው ያንኑ ከመመለሱ በፊት ሲያስተምረው የነበረውን የቀድሞ የስህተት ትምህርት ካልሆነ በስተቀር ሌላ ከየት ያመጣል? ጌታችን “ኄር ብእሲ እምሠናይ መዝገበ ልቡ ያወጽኣ ለሠናይት ወእኩይሰ ብእሲ እምእኩይ መዝገበ ልቡ ያወጽኣ ለእኪት እስመ እምተረፈ ልብ ይነበብ አፍ - በልብ ሞልቶ ከተረፈው አፉ ይናገራልና፣ መልካም ሰው ከልብ መልካም መዝገብ መልካሙን ያወጣል፥ ክፉ ሰውም ከልብ ክፉ መዝገብ ክፉውን ያወጣል” እንዳለ፡፡ ሉቃ. 6፡45
ታዲያ በኑፋቄ የኖረና ልቡ በዚያ ተሞልቶ፣ ከዚያ ውስጡን ከሞላው ኑፋቄ ለሌሎችም ሲናገር የኖረ ሰው ተመልሻለሁ ስላለ ብቻ ኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮና መንፈስ በአንድ ጊዜ ውስጡ ይመላበታልን? ይኽ ጌታችን ካስተማረው ትምህርት ጋር የማይሄድ ስለሆነ በሚገባ ሊጤን ይገባዋል፡፡ ተመልሰናል የሚሉት ሰዎች መመለሳቸውና ንስሐቸው የእውነት መሆን አለመሆኑ የሚገለጥበትና የሚፈተንበት አንዱ መንገድም ይኽ ነው፤ የተመለሱት በእውነት ከሆነ ግድ እናስተምር፣ በመድረክ እንቀጥል አይሉም፤ ነገር ግን የተንኮልና የስልት ከሆነ መድረኩ ላይ ካልቀጠልን ብለው የሙጥኝ ይላሉ፡፡
በዚህም ላይ አንድ በእውነተኛ መንፈስ ንስሐ የሚገባ ሰው በመጀመሪያ የሚያሳስበው ነገር እግዚአብሔርን በመበደሉ ይቅር እንዲለው፣ በደሉና ንስሓው እንጂ አሁንም መድረክ ላይ የመቀጠሉ ጉዳይ ሊሆን አይገባውም፡፡ እንመለስ የሚሉ ሰዎች ጭንቀታቸው መድረክ ላይ ስለ መዘመራቸውና ስለ መስበካቸው ከሆነ ጉዳዩ ዓላማን በውጭ ሆኖ ማስፈጸም ስለማይመች ወደ ውስጥ ገብቶ ተሐድሷዊውን ዓላማ ለማስፈጸም የአስገቡኝ ጥያቄ እንጂ የመመለስና የንስሐ ጥያቄ አይደለም ማለት ነው፡፡ ይኼ የድርድር እንጂ የንስሓ መንገድ አይደለም፡፡ የእንመለሳለን ጥያቄው ትኩረቱ በመድረክ ላይ ስለ መዘመርና ስለ መስበክ ከሆነ ጉዳዩ በእውነትም የእድሜ ማራዘሚያና የተንኮል ስልት እንጂ በቅንነት የተደረገ የእንመለሳለን አካሄድ ሆኖ አይታይም፡፡
11. የሚደረጉትን እያዳንዳቸውን ነገሮች ሁሉ በከፍተኛ ጥንቃቄና ማስተዋል ማድረግ
የጠፉትን መቀበል ተገቢና መልካም ቢሆንም በሌላ በኩል ደግሞ በዚህ ሂደት የሚደረጉት እያንዳንዳቸው ነገሮች ሁሉ ቤተ ክርስቲያኒቷ ለኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ እምነት ያላት ቁርጠኝነትና ድርጊቶቹ በኅብረተሰቡ ሥነ ልቡናዊና ሃይማኖታዊ አረዳድና መንፈስ ላይ ሸርሻሪ መሆን አለመሆናቸውን መጠየቅና በጥንቃቄ መመርመር ያስፈልጋል፡፡ በአንዳንዶች ዘንድ መናፍቃን የነበሩትን መቀበል የቤተ ክርስቲያንን እምነት መሸርሸር ተደርጎ እንዳይታይ መጠንቀቅ ይገባል፡፡ አለበለዚያ አንዱን እገነባለሁ ሲሉ ሌላውን ማፍረስ እንዳይሆን፡፡
እነዚህ ነገሮች በሚሆኑበት ጊዜ የሕዝቡን አረዳድና ሊያስከትል የሚችለውን ተጽእኖ በሚገባ ማጤን ያስፈልጋል፡፡ ገና ለገና ለወደፊቱ ይጠቅማል በማለት በጊዜው ያለውን ተጨባጭ ሁኔታ ያላገናዘበ ውሳኔና ድርጊት ውስጥ መግባት አደገኛ ነው፡፡ ሊያስከትል የሚችለውን አደጋ አርቆ ማየት ያስፈልጋል፣ ጭምብሎቻቸውን ገልጦ ትክክለኛ ማንነታቸውንና አደጋውን መረዳትና መለየት ያስፈልጋል፡፡
“ሰላም ሰላም” በሚል ቃል ብቻ እውነተኛ የቤተ ክርስቲያንን ውሳጣዊ ሰላም፣ እንዲሁም ጊዜያዊ ችግር የፈታንና ያቃለልን ሲመስለን ለወደፊቱ ችግር እያወሳሰብንና እያቆላለፍን እንዳይሆን መጠንቀቅ ያስፈልጋል፡፡ ለዚህ ደግሞ በቅርብ ጊዜ በዘመናችን ከስድስቱ አኃት አብያተ ክርስቲያናት መካከል አንዷ በሆነችው በሕንድ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የሆነውን አሳዛኝ ነገር ልንረሳው አይገባንም፡፡ በዋናነት በአንግሊካን ፕሮቴስታንት ቸርች (በእንግሊዝ ቤ/ክ) ቀያሽነትና አስፈጻሚነት በውስጣቸው ተፈልፍለው ያደጉት ተሐድሶዎች ገና ከመጀመሪያው ጉዳዩን የተረዱ አባቶችና ምእመናን ለይተው የማውገዝና የማጥራት ሥራ ሊሠሩ ሲሉ ተሐድሶዎቹ የእንመለሳን፣ የአስታርቁን ሽምግልና በተለያዩ ሰዎች በኩል ይልኩባቸው ነበር፡፡ በሽምግልናው ይሳተፉ የነበሩት ሰዎች አንዳንዶቹ እንዲሁ በሽፍኑ እርቅ ማን ይጠላል፣ ሰላም ምን ክፋት አለው በሚሉ መሸፈኛዎች የተታለሉና ምን እያደረጉ እንደሆኑ የማያውቁ ነበሩ፡፡ አንዳንዶቹ ደግሞ አስታረቁ ተብለው ስም ለማሰርና ጀብድ እንደ ሠሩ ለመቆጠር ነበር፡፡ አንዳንዶቹ ደግሞ ራሳቸውን በአስታራቂነት ጎራ ሲመድቡ እነርሱ ከሌሎቹ የተሻሉ አስተዋዮችና ያላከረሩ ብልሆች እንደሆኑ አድርገው ራሳቸውን ይቆጥሩ ነበር፡፡ ከእነዚህ ውስጥ ዋናዎቹ ከጀርባ ሽማግሌዎቹን የሚልኳቸውና በሽምግልናውም ውስጥ ዋናውን ሥራ ይሠሩ የነበሩት ጥቂቶቹ ግን ዓላማው ገብቷቸው ተሐድሶዎቹ በደንብ ሳይጠነክሩና ሳይጎለምሱ፣ ብዙዎችን ወደ እነርሱ ጎራ ሳይለውጡ እንዳይወጡ እንደ እድሜ ማራዘሚያ ስልት ለመጠቀም ነበር፡፡
በዚህ ምክንያት ሳይወገዙ “እርቅ”፣ “ይቅርታ፣ “ንስሐ” እየተባለ ውስጥ ውስጡን ብዙ ካህናትንና ምእመናንን ከመለመሉና ከቀሰጡ በኋላ ራሳችንን የቻልንበት ደረጃ ላይ ደርሰናል ብለው ሲያስቡ መላዋን ቤተ ክርስቲያን መቆጣጠር ስላልቻሉ በይገባኛል የቤተ ክርስቲያኒቱን ነገር ሁሉ በፍርድ ቤት ተካፍለው ከሕንድ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ውስጡን ተሐድሶ ያደረጓቸውን ካህናትና ምእመናን ይዘው በመውጣት የራሳቸውን የተሐድሶ ቤተ እምነት መሥርተዋል፡፡ እነዚህም “ማር ቶማ ቸርች” ይባላሉ፡፡ ምሥራቃዊ ፕሮቴስታንትም (Oriental Protestant) ይሏቸዋል፡፡ እርቁንና ሽምግልናውን እየተቀበሉ ተወግዘው እንዳይለዩ ሲደግፉና ሓሳብ ሲሰጡ፣ በጊዜው ጊዜ ተወግዘው እንዲለዩና ምእመናን እንዲያውቋቸው ለማድረግ ይጥሩ የነበሩ ጳጳሳትንና ምእመናንን እየለመኑና እያግባቡ “እርቅ፣ ሰላም፣ አንድነት” በሚሉ ቃላት ተታለው ሲያታልሉ የነበሩት ጳጳሳትና ምእመናን ግን የኋላ ኋላ ጥቅም የሌው ጸጸት ብቻ ነበር ያተረፉት፡፡ ነገሩ ጅብ ከሄደ ሆነባቸው፡፡
ስለሆነም ይህ ጉዳይ አንድ ጊዜ ከመቁረጥ በፊት አሥር ጊዜ፣ ካስፈለገም ከዚያም በላይ፣ መለካት የሚያስፈልገው ጠንካራ ጉዳይ ነው፡፡ እንዲሁ በይሁን ይሁን፣ በምናለበት፣ ያለ ማስተዋልና ያለ አርቆ ማሰብ የሚደረግ ነገር በኋላ በእግዚአብሔርም ዘንድ፣ በትውልድም ዘንድ ያስጠይቃልና መጠንቀቅ ይገባል፡፡ ይኼው የሕንድ ቤተ ክርስቲያን የደረሰባትን አሳዛኝ ነገር እኛ እያዘንን እንደምንጠቅሰው፣ ሌላውም ዛሬም ወደፊትም እንደ አሳዛኝ ታሪክ ማሳያ እያደረገ እንደሚጠቅሰው ሁሉ የእኛ ቤተ ክርስቲያን አባቶችና ምእመናን በዚህ ጉዳይ ላይ ከፊታችን የሚሠሩት ሥራም በበጎም ሆነ በክፉ ተጠቃሽ ነው፡፡ ግን በአስተዋይነት የተሠራ መልካም ሥራ ሆኖ በበጎ ታሪክነትና በአስተማሪነቱ የሚጠቀስ ይሆን? ወይስ በስህተትና “በእነርሱ የደረሰ እንዳይደርስባችሁ” በሚል ማስፈራሪያነት? ውጤቱን ወደፊት የምናየው ይሆናል፡፡ ግን ከአፍንጫ ሥር ያለውንና ከፊት የቀረበውን ብቻ አሽትቶና አይቶ የሚወሰን ሳይሆን ወደ ኋላ ከዘመነ ሐዋርያት አንሥቶ የነበረው ታሪከ ቤተ ክርስቲያንና አስተምህሮን፣ አሁን ደግሞ ያለንበትን ጠቅላላና ዝርዝር ተጨባጭ ሁኔታ፣ ወደፊትም በእግዚአብሔርና በትውልድ ያለብንን ኃላፊነት ታሳቢ ያደረገ ቀኖናዊ ሂደት ይኖራል ብለን ተስፋ እናደርጋለን፣ እንዲኖርም እንፈልጋለን፡፡ ቤተ ክርስቲያን የሁላችንም ናትና እያንዳንዳችንም ችላ ሳንል፣ “እንዳረጉ ያድርጉት፣ እኔ ምን አገባኝ” ሳንል የቤተ ክርስቲያንን አንድነትና ቀኖናዊነት በጠበቀና ባገናዘበ መልኩ የየድርሻችንን እንወጣ፡፡
  • “ከወዳጆችህ ጋር ብቻ ሳይሆን ከጠላቶችህም ጋር እንኳ ሳይቀር በሰላም ኑር፤ ነገር ግን እንዲህ የምልህ ካንተ ከግል ጠላቶችህ ጋር እንጂ ከእግዚአብሔርና ከቤተ ክርስቲያን ጠላቶች ጋር አይደለም፡፡”አንድ ገዳማዊ አባት ለአንድ በቤተ ክርስቲያን ኃላፊነት ላይ ለነበረ ሌላ አባት ከጻፈው መልእክት ላይ የተወሰደ
  •  “ሰውን ከእግዚአብሔር ከሚለየው አጉል ሰላም ይልቅ ከእግዚአብሔር የማይለየው ጦርነት ይሻላል፤ ስሜታዊ ከሆነና ለቤተ ክርስቲያን ዘለቄታዊ ጉዳት ከሚኖረው ስምምነትና አንድነት ይልቅ ስለ ሃይማኖት መጠበቅ ዘለቄታዊ ጠቀሜታ የሚኖረውና ለዚህ ሲባል የሚሆን አለመስማማት ይሻላል፡፡”
ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ፣ ትምህርት 2፡82

                                   በአውሮጳ   የካህናት አንድነት ማኅበር ሊቋቋም መሆኑ ታወቀ በ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከመላዋ አውሮጳ   የተውጣጡ ካህናት፡” የ...