2013 ኖቬምበር 28, ሐሙስ

                                                      በጅማ ከተማ ሀገረ ስብከቱ እያስገነባ ያለው ሁለገቡ ሕንጻ
                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                    

ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ ስለዕቅድ አፈጻጸሙ ግምገማ በማድረግ ላይ
                                                        






            የጅማ ሀገረ ስብከት የሦስት ወራት ዕቅድ                                                                                      
         አፈ ጻጸም ተገመገመ

በአዲስአበባሀገረስብከትየብፁዕወቅዱስፓትርያርክረዳትናየጅማዞንሀገረስብከትሊቀጳጳስብፁዕአቡነእስጢፋኖስበ14/3/2006 ዓ.ምበጅማሀገረስብከትበተደረገውአጠቃላይስብሰባየሦስትወራትዕቅድአፈጻጸምግምገማአድርገዋል ፡፡ የስብሰባውዋናዋናአጀንዳዎችሐምሌ  20እና21/2005 ዓ.ምበጎማወረዳአጋሮከተማበተደረገውየሀገረስብከቱጠቅላላጉባኤላይከታቀደውዕቅድመካከልበትናንትናውስብሰባላይየተነሳውበስብከተወንጌልእንቅስቃሴእናበጅማከተማሀገረስብከቱየሚያስገነባውንሁለገብሕንጻበተመለከተውይይትተደርገውባቸዋልበዚሁመሠረትየወረዳዎችናየጅማከተማአድባራትናገዳማትአፈጻጻምየተሻለመሆኑንየተገለጠሲሆንዝቅተኛውጤትላስመዘገቡትደግሞየማጠናከሪያተግሳፅደርሶአቸዋልበተለይበሕዝበክርስቲያኑከፍተኛርብርብእየተሰራእየተፈጸመየሚገኘውይህሕንጻ G+5 ሲሆንከትንሣኤበኋላይመረቃልተብሎይገመታልተብሎአልለዚሁማስፈጸሚ 4.500000/አራትሚሊዮንአምስትመቶሺህ ብር እስከመጋቢት ድረስለመሰብሰብመታቀዱንምተገልጦአልበከተማውየሚገኙማኅበረቅድሳንንጨምሮየሚገኙማኅበራትምከፍተኛርብርብእንዲያደርጉሊቀጳጳሱጥሪአቅርበዋልይህሁለገብሕንጻአገልግሎትየሚሰጠውበሀገረስብከቱየተዘጉትንአድባራትንማስከፈትናቀጠይልማትንምለማስቀጠልየሚችልመሆኑየታወቀሲሆንእስከአሁንእስከአራተኛፎቅድረስበመጠናቀቁእየተከራየይገኛል፡፡ <ዘመኑየውድድርነውመፍጠንይገባል>ያሉትሊቀጳጳሱበቀጣዩበከተማውመካከልበደጆችሽአይዘጉመንፈሳዊማህበርአማካይነትሊሰራየታቀደው G+4 ባለአራትፎቅሁለገብሕንጻበቀጣዩይጀመራልብለዋልይህሕንጻ ለ65 አድባራትናገዳማትመርጃይሆንዘንድመታሰቡንምጨምረውገልጠዋል፡፡ሁለገብሕንጻውንበተመለከተየውስጥዖዲተርእስከታሕሳስ 30 እንዲጠናቀቅመመሪያየሰጡሲሆንበመቀጠልምየውጪዖዲተርይመለከተዋልብለዋልሀገረስብከቱበልማትከተፋጠነስብከተወንግልበገጠሪቱሁሉይስፋፋልያሉትሊቀጳጳሱህገወጥሰባክያንናዘማርያንንበተመለከተበስብሰባውላይጥብቅመመሪያሰጥተዋልየሰባክያንንናዘማርያንንፎቶመለጠፍከቤተክርስትያናችንሥርዓትውጪነውያሉትሊቀጳጳሱይህንንበሚያደርጉአካላትላይእርምጃእንወስዳለንብለዋል፡፡
በተያያዘዜናጥር 18/ 2006 ዓ.ምብፁዕወቅዱስአቡነማትያስፓትርያርክዘኢትዮጵያበጅማሀገረስብከትውስጥየሚገኙትንየአበልቲ ቅ/ኪዳነምሕረትገዳምየአብነት ት/ቤትናበናትሪ ቅ/ገብርኤልቤተክርስቲያንለሚገነባውየካህናትናደቀመዛሙርትማሰልጠኛየመሠረትድንጋይለማስቀመጥእንደሚሄዱየተገለጠሲሆንለዚሁምከወዲሁዝግጅትእየተደረገመሆኑንታውቆአልበስብሰባውምላይየአድባራትናገዳማትአስተዳዳሪዎች ፤ሰበካጉባኤአባላት ፤ ካህናት፤ የማኅበራትተወካዮች፤ ሰባክያነወንጌልሌሎችምተገኝተዋል፡፡ሊቀጳጳሱከስብሰባውበኋላበሻሻአቡነገብረመንፈስቅዱስቤተክርስቲያንድረስበመሔድሕዝበክርስቲያኑንጎብኝተውናአጽናንተውተመልሰዋል፡፡በሻሻአቡነ ገ/መንፈስቅዱስቤተክርስቲያን በ1999 ዓ.ምካህናትናምእመናንየተሰየፉበትቦታመሆኑይታወሳል፡፡
                                                   

2013 ኖቬምበር 19, ማክሰኞ

                               

                                                           ከዲያቆን  ምትኩ አበራ


አንድ አላማ በሦስቱ መቅደሶች

November 20, 2013 at 2:35am
አጉራ ዘለል በመባል የሚታወቁትና ከጠቅላይ ቤተ ክህነታችን የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልዕኮ መምሪያ ይሁንታ ውጪ ራሳቸውን ያሰማሩት  ህገ ወጥ "ሰባኪያን" በባሌ ሀገረ ስበከት ቅንጣት  ታህል ቦታ የላቸውም፡፡ ይህ ሊሆን የቻለው ደግሞ በተለይም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ መምሪያው እያደረገ ያለው ጥብቅ ቁጥጥርና ክትትል እንዳለ ሆኖ የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ ያለምንም ጣልቃ ገብነት ለሀገረ ስብከቱ የስብከተ ወንጌል ክፍል ኃላፊ በሰጡት ሙሉ ሥልጣንና ኃላፊነት መሠረት በሚደረገው እልህ አስጨራሽ ትንቅንቅ ነው፡፡ይህ ብቻ እንኳን በራሱ ህገ ወጦችን መከላከል ሲገባቸው ጭራሽኑ ያለ ጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ፈቃድ በማን አለብኝነት እየጋበዙ ሀገረ ስብከታቸውን የአጉራ ዘለል ሰባክያን መፈንጫ ለሚያደርጉ አንዳንድ የሀገረ ስብከት ጳጳሳትና ሥራ አስኪያጆች በቂ ማስተማርያ ነው፡፡
ውድ አንባቢያን የጽሑፌ መነሻ ማኅበሬ ማኅበረ ቅዱሳን ተጠይቆና በቁጥር 740/141/2006 በቀን 3/3/2006ዓ.ም. ተጽፎ በስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልዕኮ መምሪያ ሓላፊ መልአከ ብርሐን ፍስሐ ጌታነህ ፊርማ ወጪ በሆነ ደብዳቤ ታዝዤ ለስብከተ ወንጌል አገልግሎት በባሌ ሀገረ ስብከት በጊኒር ወረዳ መገኘቴ ነበር፡፡ አብረውኝ በጠቅላይ ቤተ ክህነት የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልዕኮ መምሪያ የሳንሱር ክፍል ኃላፊና የጉባኤው አስተባባሪና የልዑካኑ መሪ የሆኑት መምህር ናዖድ ኢያሱ፣ ዘማሪ ገብረ አምላክ ዘማሪና የዜማ መሣሪያ ባለሙያ የሆነው በኃይሉና ዘማሪት ቡርቱካን ነበሩ፡፡
ጉባዔው የሦስት ቀን ጉባዔ ሲሆን ከህዳር 6-8/2006ዓ.ም.የቆየ ነበር፡፡ ዓርብ ለሚጀምረው ጉባዔ ከአዲስ አበባ የተነሳነው ሐሙስ ሌሊት ነበር ምክንያቱ ደግሞ ጊኒር በአንድ ቀን ጉዞ ስለማይደረስ ነበር፡፡ ከአዲስ አበባ ባሌ ሮቤ 445ኪ.ሜ. ተጉዘን እዛው ሮቤ ካደርን በኋላ መንገዱ  ፒስታ በመሆኑ ብቻ 135ቱን ኪ.ሜትር 5 ሰዓት ተጉዘን ነበር ከሮቤ ጊኒር      የገባነው፡፡ በጊኒር ያየነው ነገር አስደንቆናል ሁሉም ነገር ሦስት ሲሆን ግን አንድ ነው፡፡ እዚያ ሦስት መቅደስ አለ ሰንበት ትምህርት ቤቱ ግን አንድ ነው፣በዋናነት ሦስት ማህበራት አሉ(ሰ/ት/ቤት፣ማኅበረ ቅዱሳን፣ስብከተ ወንጌሉን ለመደገፍ በአጥቢያው የተሰባሰቡ ወጣቶች) አላማቸውና አገልግሎታቸው ግን አንድ ነው፣ምን አለፋችሁ ቦታው ፍቅር የነገሠበት፣የጠቅላይ ቤተ ክህነታችን መዋቅር የሚከበርበት፣ ሀገረ ስብከቱ ከወረዳው፣ ወረዳው ከአጥቢያው፣አጥቢያው ከሰንበት ትምህርት ቤቱ፣ ሰንበት ትምህርት ቤቱ ከማኅበረ ቅዱሳን……..ወዘተ ተናበውና ተገናዝበው፣ተረዳድተውና ተዋደው የሚሠሩበት የሰላምና  የበረከት ቦታ ነው፡፡
 የዚህ ሁሉ አንድነት ምክንያቶች የሆኑት ሦስቱ መቅደሦች የሚገኙት በአንድ ቅጽር ነው፡፡ ቅጽሩ የሚገኘው ደግሞ ልከ እንደ ጊሸን ተራራ ባለው ጉብታ ነው፡፡ የእመቤታችን ቅድስት ማርያምና የሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ አብያተ ክርስቲያናት በመጠኑ ተራርቀው፤ሲገኙ የመድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን ደግሞ በርቀት ታንጿል፡፡ እነዚህ ሁሉ ታዲያ ለምዕመኑ አንድ አጥቢያ  ሲሆኑ የሚተዳደሩት በአንድ ሰበካ ጉባዔ ሲሆን የሚገለገሉትም በአንድ ሰንበት ትምህርት ቤት ነው፡፡
የተሰጠው አገልግሎት ሦስት ዐይነት ነበር (ለምዕመናን በዓውደ ምሕረት ላይ፣ለስብከተ ወንጌል ማጠናከሪያ የበኩላቸውን ለማድረግ ለተሰባሰቡት ወጣቶች በማረፊያ ቦታችን፣ በማኅበረ ቅዱሳን የጊኒር ወረዳ ማዕከል አባላት በጽሕፈት ቤታቸው) ይሁን እንጂ አላማው ግን አንድ ነበር፡፡ ለማገልገል ወደ ቦታው የተጓዝነው ልዑካን የተውጣጣነው ከሦስት ቦታ  ነበር (ቅጠቅላይ ቤተ ክህነት፣ከማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማዕከል፣በግላቸው የሚያገለግሉ ዘማርያን ይሁን እንጂ አገልግሎቱ ግን በህብረት ነበር፡፡ መርሐ ግብሩን ሲያሳልጡ የነበሩ ባለ ድርሻ አካላት ሦስት ነበሩ(ስሙ እንዳይጠቀስ የተማጸነ የልዑካኑን ሙሉ ወጪ የቻለ አንድ ምዕመን፣እራሱ ፊት አውራሪ በመሆን ልዑካኑን ሲመራና ሲያስተባብር የነበረው የጠቅላይ ቤተ ክህነት ስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልዕኮ መምሪያና የባሌ ሀገረ ስብከት ከላይ እስከ ታች ባሉት መዋቅሮቹ)እነዚህ ሦስት አካላት ግን እንደ አንድ ልብ አስበው እንደ አንድ ቃል ተናግረዋል፡፡
በአጠቃላይ ይህ ታሪካዊና ታላቅ የሆነ የሦስት ቀን ጉባዔ፤ የጊኒር ከተማ ምዕመናን ነቅለው የወጡበት፣የማኅበረ ቅዱሳንና የጠቅላይ ቤተ ክህነትችን ጥምረት የታየበት፣ለስብከተ ወንጌሉ አገልግሎት ቀናዒያን የሆኑ ገንዘባቸውንና ጉልበታቸውን የማይሰስቱ ደጋግ ምዕመናን እናዳሉን ያየንበት፣መምሪያው አጉራ ዘለል ሰባክያንን ለማስታገስና ምዕመናንን ለመጠበቅ ያለውን ቁርጠኝነት ያሳየበት የተሣካ ጉባዔ ነበር ማለት ይቻላል፡፡
ውድ አንባቢዎቼ የተለመደ የፎቶ ግብዣዬን እነሆ፡፡ ታዲያ አንባችሁና አይታችሁ ስትጨርሱ የተሰማችሁን ሁሉ ብትጽፉልኝ ደስ ይለኛል፡፡
የልዑካኑ መሪ መ/ር ናዖድ ኢያሱ
የልዑካኑ መሪ መ/ር ናዖድ ኢያሱ
ሰበካ ጉባዔው ለሥራ እንጂ ለቢሮ አይጨነቅም
ሰበካ ጉባዔው ለሥራ እንጂ ለቢሮ አይጨነቅም
ትጉሃኑ የሰንበት ተማሪዎች ሊዘምሩ መጥተው ዘምረው አይሰወሩም ይማራሉ እንጂ
ትጉሃኑ የሰንበት ተማሪዎች ሊዘምሩ መጥተው ዘምረው አይሰወሩም ይማራሉ እንጂ
በመሰራት ላይ ያለው የቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን
በመሰራት ላይ ያለው የቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን
በመሠራት ላይ ላለችው ቅ/ማርያም ቤተ ክርስቲያን ስዕል እየሳለ የሚገኘው ሰዓሊ ሙሴ ከነ ስዕሉ
በመሠራት ላይ ላለችው ቅ/ማርያም ቤተ ክርስቲያን ስዕል እየሳለ የሚገኘው ሰዓሊ ሙሴ ከነ ስዕሉ
መ/ር ሰለሞን የወረዳው ሊቀ ካህን
መ/ር ሰለሞን የወረዳው ሊቀ ካህን
ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን
ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን
ሰዓሊው ከሚስላቸው ስእሎች አንዷ
ሰዓሊው ከሚስላቸው ስእሎች አንዷ
ዘማሪ ገብረ አምላክ
ወንጌል ናፋቂው ጊኒር ምዕመን
ወንጌል ናፋቂው ጊኒር ምዕመን
ወንጌል ናፋቂው ጊኒር ምዕመን
ወንጌል ናፋቂው ጊኒር ምዕመን
ወንጌል ናፋቂው ጊኒር ምዕመን
ወንጌል ናፋቂው ጊኒር ምዕመን
ወንጌል ናፋቂው ጊኒር ምዕመን
ወንጌል ናፋቂው ጊኒር ምዕመን
ወንጌል ናፋቂው ጊኒር ምዕመን
ወንጌል ናፋቂው ጊኒር ምዕመን
ትጉሃን ታዳሚዎች
ትጉሃን ታዳሚዎች
ልዑካኑ በከፊል የምንመገብባት ቦታ
ልዑካኑ በከፊል የምንመገብባት ቦታ
ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን
ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን
የጊኒር ከተማ በከፊል
የጊኒር ከተማ በከፊል
ልዑካኑ በከፊል
ልዑካኑ በከፊል
መ/ር ወጋየሁ የሀ/ስብከቱ ስ/ወ/ክ/ሓላፊ
ከተራራው ቁልቁል
ከተራራው ቁልቁል
የጊኒር ከተማ በከፊል
የጊኒር ከተማ በከፊል
ትጉሃኑ የሰንበት ተማሪዎች ሊዘምሩ መጥተው ዘምረው አይሰወሩም ይማራሉ እንጂ
ትጉሃኑ የሰንበት ተማሪዎች ሊዘምሩ መጥተው ዘምረው አይሰወሩም ይማራሉ እንጂ

                                                                                                                                                                                                                                                       

2013 ኖቬምበር 18, ሰኞ

                                                
                                             

በዲ/ን ታደሰ ወርቁ
                                                                                                                                                           Nationalization of <shame >in Ethiopia

November 16, 2013 at 11:48am
On the face of it, Ethiopia Government and we disagree about the political import of shame and humiliation to our beloved country. On the one hand, EPRDF uses the topic of <shame> to understand something else: how the Saudi Arabia mis/understand Ethiopia Economic success. On the other hand, we use the current Ethiopia nationalism to argue that the logic of humiliation itself needs to probe.
The EPRDF’s discourse marks that how national humiliation is used by the regime leaders to mobilize populations, but these populations are on opposite sides of the dispute: we consider nativity understanding of the Ethiopia self, while EPRDF examines a Saudi Arabia othering of western.
The complexity Suggested by this note demonstrates the Multi code nature of the word <shame> .To have shame is both a virtue and a problem along the lines of tension between having humility and humiliation. More to the point, both EPRDF and we agree that understand and humiliation is more complex than a simple political calculation of links between defeat, humiliation and revenge. Humiliation  thus is reframed from an irrational emotion that need to be cured, through (social) psychology ,to a social practice that needs to understood interims of political  and historical narratives .
Indeed, shame politics of EPRDF’S provide an interesting example how the self not only constructs the other as enemy, but how the other constructs the self-complex ways. Yet as #Dr.Tewoderos Adhanom’s ETV interview point out, shame discourse does not dominate Ethiopian images: shame is a product of ‎Saudi Arabia understanding of Ethiopian.
The contemporary Ethiopian nationalism is not just about celebrating the glories of Ethiopian civilization: it also commemorates Ethiopia’s weakness. This negative image comes our most directly in the discourse of Ethiopia’s decade of national humiliation.
To understand how Ethiopian nationalism works, we need to reverse #Paul Kennedy’s famous thesis about <the rise and fall of the great powers> to examine the < fall and rise >of Ethiopia: many of the titles of these books include the phrase <from humiliation to glory.> The discourse of national humiliation shows how Ethiopia’s insecurities are not just material, a matter of catching up to the the west militarily and economically, but symbolic. Indeed, one of the goals of Ethiopia foreign policy has been to  
 The brutal and inhuman crackdown on Ethiopian immigrants in Saudi Arabia context, international politics has been transformed from< conquer or be conquered> in to <humiliate or be humiliated.> Main stream commentators, thus have declared that history is<< strategic issue>>, especially as it informs the dynamic between nationalism and foreign policy.
Ethiopian nationalism is a huge field of inquiry. To gain purchase on this vast topic, it is helpful to take an oblique view of Ethiopian identity through an examination of the specialized field of EPRDF texts.
Finally, humiliation may still see like an odd place to look for nationalism: humiliation is something that you suffer, rather than promote. But as we have seen, in Ethiopia and in china, humiliation is not just about passive National humiliation discourse involves a very active notion of history and recovery.AS the ancient work #Liji tell us;<< the humiliation of a thing is sufficient to stimulate it: the humiliation of a country is sufficient to rejuvenate it.>> for me the day that happened  the brutal and inhuman crackdown on Ethiopian immigrants in Saudi Arabia and Ethiopian police crackdown on anti-Saudi Arabia protest following migrant worker attacks has been ,<official holiday> called National Humiliation Day./? However National humiliation is far from simply being an obscure historical curiosity. In other words, the narrative of national salvation depends upon national humiliation; the narrative of national security depends upon national insecurity. 

2013 ኖቬምበር 17, እሑድ


በደቡብ ጎንደር ሀ/ስብከት በሥራ አስኪያጁ ላይ የተላለፈውን የማሰናበት ውሳኔ የተቃወሙ መላው የጽ/ቤት ሠራተኞች ሥራ አቆሙ፤ ሀ/ስብከቱ ‹‹የመንበረ ጵጵስና ልዩ ጽ/ቤት›› እስከ ማቋቋም በደረሱ ሙሰኞች እና ጠንቋዮች እየታወከ ነው

  • የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት በሥራ አስኪያጁ ላይ የተላለፈውን የስንብት ውሳኔ ውድቅ በማድረግ ወደ ሓላፊነታቸው እንዲመለሱ ለሊቀ ጳጳሱ ትእዛዝ ሰጥቷል፡፡ ይኹንና ትእዛዙ በሀ/ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ዘንድ ተቀባይነት አግኝቶ ተፈጻሚ ባለመኾኑ የሀ/ስብከቱን ሥራ በማቆም የተወሰደው የመላው ሠራተኛ ርምጃ፣ በአሜሪካ ከብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ ጋራ በሐዋርያዊ ጉብኝት ላይ የሚገኙትን የብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ አቡነ ማቴዎስን መመለስ እየተጠባበቀ ነው፡፡
  • ራሳቸውን ‹‹የሊቀ ጳጳሱ የግል አማካሪ›› ብለው የሠየሙት ሙሰኞቹና ጠንቋዮቹ በሀ/ስብከቱና በሊቀ ጳጳሱ ስም ባስቀረፁት ማኅተምና ቲተር ጽ/ቤቱ የማያውቃቸውን ሕገ ወጥ ደብዳቤዎች ያዘጋጃሉ፡፡
  • ሥራ አስኪያጁ ከሓላፊነታቸው መሰናበታቸው የተገለጸው፣ ሊቀ ጳጳሱን የከበቡት ‹‹የሊቀ ጳጳሱ የግል አማካሪ›› ነን ባዮች በሐሰተኛ ማኅተምና ቲተር ባዘጋጁት ደብዳቤ ነው፡፡
  • በሀ/ስብከቱ በስምንት ዓመት ውስጥ 13 ሥራ አስኪያጆች ከሓላፊነታቸው መሰናበታቸው ሙሰኞች እና ጠንቋዮች በሊቀ ጳጳሱ ዙሪያ እየፈጠሩት ለሚገኙት ከፍተኛ ተጽዕኖ ማሳያ ኾኗል፡፡
Participants of the 32nd SGGA 02
አላግባብ ከሓላፊነታቸው የተሰናበቱት የደቡብ ጎንደር ሀ/ስብከት ሥራ አስኪያጅ አፈ መምህር አባ ገብረ ሥላሴ ጌትነት በመ/ፓ/አጠ/ሰ/መ/ጉባኤ ፴፪ኛው ዓመታዊ ስብሰባ ወቅት በተሳትፎ ላይ
  • ሥራ አስኪያጁ÷ መንግሥታዊ እና መንግሥታዊ ያልኾኑ ድርጅቶችን ድጋፍ በማስተባበር በሚያዘጇቸው የአቅም ግንባታ ሥልጠናዎች፣ ከሌሎች አህጉረ ስብከት ጋራ በሚካሄዱ የልምድ ልውውጥ መርሐ ግብሮች፣ በወቅታዊ ግምገማዎችና በግምገማዎቹ ላይ በተመሠረቱ የማስተካከያ ርምጃዎች በሀ/ስብከቱና በዐሥራ ሁለቱም የወረዳ ቤተ ክህነት ጽ/ቤቶች የዘለቀ መልካም አስተዳደር በማስፈን፣ የቤተ ክርስቲያንን ይዞታዎች የባለቤትነት መብት በሕግ አግባብ በፍትሕ አካል በማስከበር ሞያዊ ጥረታቸው ሀ/ስብከቱን በመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ‹‹የአህጉረ ስብከት የሥራ ብቃት ዓመታዊ ውድድር›› ላይ ተሸላሚ በማድረግ ይታወቃሉ፡፡
  • በሕግ ዲፕሎማ ያላቸውና ለአንድ ዓመት ከዘጠኝ ወራት በሀ/ስብከቱ በሥራ አስኪያጅነት ሓላፊነት የቆዩት አፈ መምህር አባ ገብረ ሥላሴ ጌትነት፣ የመሬት ይዞታቸውን በሕገ ወጥ መንገድ የተነጠቁ የ12 አብያተ ክርስቲያንን የባለቤትነት መብቶች እንደጠበቃ በተለያዩ ፍ/ቤቶች በራሳቸው እየተሟገቱ አስመልሰዋል፡፡
  • ከእኒህም መካከል÷ በፎገራ ወረዳ መነጉዞር ኢየሱስ የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ግንባታ የታቀደበትና በሀገር በቀል ደን የተሸፈነ አራት ሄክታር መሬት፣ በሊቦ ከምከም የዋሻ ተክለ ሃይማኖት አራት ሄክታር መሬት፣ በደብረ ታቦር ፀጉር ኢየሱስ 2.5 ሄ/ር መሬት፣ በፋርጣ ወረዳ የሞክሼ መርቆሬዎስ 2 ሄ/ር መሬት እና በስምና ጊዮርጊስ አንድ ሄክታር መሬት እንዲሁም በደብረ ታቦር እና ላይ ጋይንት ከተሞች ስፋታቸው 7012 ካሬ ሜትር የኾኑ የሕፃናት ማሳደጊያዎች የይዞታ መብቶች መረጋገጥ ይገኙበታል፡፡ የሀ/ስብከቱ የ፳፻፭ ዓ.ም. ዓመታዊ ሪፖርት እንደሚያሳየው 623 አብያተ ክርስቲያን የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር እንዲያገኙ ተደርጓል፡፡
  • በሥራ አስኪያጁ ላይ የተወሰደውን አላግባብ ከሓላፊነት የማሰናበት ርምጃ በመቃወም የሀ/ስብከቱ ጽ/ቤት ሠራተኞች ከኅዳር ፫ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም አንሥቶ ሥራ በማቆማቸው ሳቢያ ከፍተኛ የባለጉዳዮች መጉላላት እየታየ ነው፡፡ በሥራ እንቅሰቃሴው እና የሠራተኞች ቁጥጥሩ ቀናት ይፈጁ የነበሩ ሥራዎችን በሰዓታት ያሳጠረው ሀ/ስብከቱ በጽ/ቤት ደረጃ የቅሬታ ሰሚ ሠራተኛ በመመደቡ ክፍተት የሚታይባቸው አስተዳደራዊ ውሳኔዎችና አሠራሮች በቅሬታ መልክ በድጋሚ ቀርበው አፋጣኝ መፍትሔ ያገኛሉ፡፡
  • የጽ/ቤቱ ሠራተኞች ራሳቸውን ‹‹የሊቀ ጳጳሱ የግል አማካሪ›› ብለው በሠየሙና ለሥራ አስኪያጁ አላግባብ መታገድ ምክንያት ከኾኑ ግለሰቦች ውስጥ በሦስቱ ላይ ክሥ መሥርተዋል፡፡ ከእነርሱም መካከል በታች ጋይንት እና አዲስ ዘመን ከተሞች ሁለት ጊዜ በሥርዐተ ተክሊል ጋብቻ የፈጸመው የወረታ ወረዳ ቤተ ክህነት ስብከተ ወንጌል ሓላፊ መ/ር ዕንባቆም ዘርዐ ዳዊት ዋነኛው ሲኾን ካህናትንና ሊቃውንትን በመከፋፈልና በማጋጨት፣ የአጥቢያ ሰበካ ጉባኤያትን በጣልቃ ገብነት በመበጥበጥና ከሰንበት ት/ቤቶች ጋራ በማጋጨት በሚገባ ይታወቃል፡፡
  • ሌላው አዋኪ፣ በፎገራ ወረዳ የደራ ቅ/ጊዮርጊስ አስተዳዳሪው መልአከ ሰላም አፈ ወርቅ ወንድማገኝ የሚባሉ ሲኾን በመጋቢት ወር ፳፻፭ ዓ.ም. ጀምሮ በከፍተኛ የገንዘብ ማጭበርበር ተከሠው የታሰሩና ከሓላፊነታቸው የታገዱ ናቸው፡፡ መሪጌታ መፍቀሬ ሰብእ መኰንን እና መሪጌታ ኅሩይ ደመወዝ የተባሉት ግለሰቦች ደግሞ በደራ ወረዳ አንበሳሜ ከተማ እና በንፋስ መውጫ ቅድስት ሥላሴ በጥንቆላ ሥራ የሚተዳደሩ እንደኾኑ ተነግሯል፡፡
  • በሀ/ስብከቱ ሥራ አስኪያ ላይ የተላለፈው የማሰናበት ርምጃ አግባብነት የሌለው መኾኑን በመግለጽ ለሁለት ዓመታት ያህል ወደቆዩበት ሓላፊነታቸው እንዲመለሱ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ያስተላለፈውን ትእዛዝ ባለመቀበል ሁለተኛ የማሰናበት ደብዳቤ የጻፉት የሀ/ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ÷ በአማካሪ ነን ባይ ነገረ ሠሪዎች ላይ እንዲያውቁባቸውና ሀ/ስብከቱን ‹‹መቋጫ ከሌለው መካሠሥና ከፋ ብጥብጥ›› እንዲታደጉት የሀ/ስብከቱ አካላት በመምከር ላይ ናቸው፡
  • ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ በአንድ መልእክታቸው፣ ‹‹ሐላፊነት፣ ሐቀኝነትና ተጠያቂነት የተሞላበት መልካም አስተዳደር ከአጥቢያ አብያተ ክርስቲያን እስከ መንበረ ፓትርያርክ ድረስ እንዲሰፍን ማድረግ ተገቢነቱ አያጠያይቅም፡፡ መልካም አስተዳደር ከሌለ ሁሉም ነገር ከንቱ እንደኾነ እናምናለን›› እንዳሉት፣ በሥራ አስኪያጅነት በሚመሩት ሀ/ስብከት የመልካም አስተዳደር አብነት እንደኾኑ የሚነገርላቸው እንደ አፈ መምህር አባ ገብረ ሥላሴ ጌትነት ያሉ ሓላፊዎች በተቋማዊ ለውጥ አመራራቸው ይጎለብቱ ዘንድ ዕድል ሊሰጣቸውና አስፈላጊው ድጋፍ ሊደረግላቸው ይገባል፡፡
  • ሀ/ስብከቱ÷ ባለፈው ዓመት መነሻቸውን አዲስ አበባ ባደረጉና ራሳቸውን ደቂቀ ኤልያስ በሚል ሲቀስጡ የተገኙ ሁለት ዲያቆናት ነን ባይ ግለሰቦችን ለፍትሕ አካል አቅርቦና እስከ ክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ድረስ ተከራክሮ በስድስት ወራት እስራት እንዳስቀጣው ሁሉ በቡድን ተደራጅተው አስተዳደሩንና መንፈሳዊ አገልግሎቱን በሚያውኩት ሙሰኞች እና ጠንቋዮች ላይም የሚወስደውን ርምጃ አጠናክሮ በመቀጠል ከመዋቅሩ ማጽዳት ይጠበቅበታል፡፡
  • የደቡብ ጎንደር ሀ/ስብከት የአራቱ የምስክር ጉባኤ ቤቶች መገኛ እንደመኾኑ መጠን የበርካታ ቋሚ መንፈሳዊ ት/ቤቶችና የአብነት ት/ቤቶች ምንጭ ነው፡፡ በዚህም መሠረት ብዛታቸው 7,167 የኾነ የንባብ፣ የቅዳሴ፣ የቅኔ፣ የዝማሬና መዋስዕት፣ የድጓ፣ አቋቋምና የመጻሕፍት መምህራን እንዲሁም ከ27,928 በላይ ደቀ መዛሙርት እንደሚገኙበት የሀ/ስብከቱ ሪፖርት ያስረዳል፡፡ እኒህን የአብነት መምህራንና ደቀ መዛሙርት ለመደጎም በገቢ ምንጭነት የሚያገለግል ባለአራት ፎቅ ሁለገብ ሕንፃ በደብረ ታቦር ከተማ ለመገንባት ዲዛየኑ አልቆ፣ የመሠረት ደንጊያው ተጥሎ ወደ ግንባታ ሥራው በመግባት ላይ ይገኛል፡፡ የድጓ ምስክር የሚገኝበት የቅድስት ቤተ ልሔም ጉባኤ ቤት እና ሙዝየም በብፁዕ ሊቀ ጳጳ አቡነ እንድርያስ የቅርብ ክትትልና በማኅበረ ቅዱሳን የቅዱሳት መካናት መርጃና ማቋቋሚያ ድጋፍ ለፍጻሜ መብቃቱ ይታወሳል፡፡

2013 ኖቬምበር 15, ዓርብ

የ2005 ዓ.ም የቤተክርስቲያኒቱ ሀገራዊ ገቢ አንድ ቢሊየን የኢትዮጵያ ብር ተጠጋ



(አንድ አድርገን ህዳር 6 2006 ዓ.ም )፡- ዐዋጅ ነጋሪ ተብሎ ጥቅምት 2006 ዓ.ም በሰበካ ጉባኤ ማደራጃ መምሪያ  የተዘጋጀው መጽሔት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ስር በሀገር ውስጥ ብቻ  የሚተዳደሩ 50 የሀገረ ስብከቶች ጠቅላላ ገቢ የሚያሳይ መረጃ ይዞ ወጥቷል፡፡ በሰባካ ጉባኤ ማደራጃ መምሪያ የወጣው ስታስቲክሳዊ መረጃ   የእያንዳንዱን አህጉረ ስብከት የ2005 ዓ.ም የዘመኑን ገቢ ያሳያል፡፡ እንደ መረጃው የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በገቢ መጠን ከሁሉም በከፍተኛ ሁኔታ ልቆ ይታያል ፡፡ ጠቅላላ ገቢውም 322,739,515 ( ሶስት መቶ ሃያ ሁለት ሚሊየን ሰባት መቶ ሰላሳ ዘጠኝ ሺህ አምስት መቶ አስራ አምስት) ሲሆን  ከአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ቀጥለው  
1.     አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት               322,739,515.29

2.    ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት                  46,330,546.99

3.    የምስራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት              32,843,596.64

4.    ሰሜን ጎንደር ሀገረ ስብከት              29,805,415.24

5.    ሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት                25,853,270.26

6.    ምዕራብ ጎጃም ሀገረ ስብከት            21,894,699.00

7.    ደቡብ ወሎ ሀገረ ስብከት                20,456,331.63

8.    አርሲ ሀገረ ስብከት                      19,297,272.45

9.    መቀሌ ሀገረ ስብከት                     18,352,795.05

10.  ምስቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት               17,522,762.00

11.    ደቡብ ጎንደር ሀገረ ስብከት              16,896,645.44
እነዚህ ከላይ የተዘረዘሩት ከ15 ሚሊየን ብር በላይ አመታዊ ገቢ የሰበሰቡ ሲሆኑ ፤ ከበስተመጨረሻ ከ47-50 ደረጃ ላይ የተቀመጡት ከምባታ ጠንባሮ ሀገረ ስብከት ፤ ከሚሴ ሀገረ ስብከት እና ዳውሮ ሀገረ ስብከት ከ አንድ ሚሊየን ብር በታች ዓመታዊ ገቢ እንዳስገቡ መረጃው ይጠቁማል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም መረጃው ከገቢው የአህጉረ ስብከት 20 በመቶ እና የጠቅላ ቤተክህነት 35 በመቶ የገንዘብ መጠኑ ይጠቁማል፡፡ ይህ ሪፖርት በቤተክርስያቱ ስር የሚተዳደሩ ከሀገር ውጪ የሚገኙ ሀገረ ስከቶችን አይጨምርም፡፡ በጠቅላላው ቤተክርስቲያኒቱ በ2005 ዓ.ም የዘመኑ ገቢ ጠቅላላ 812,742,638.00 (ስምንት መቶ አስራ ሁለት ሚሊየን ሰባት መቶ አርባ ሁለት ሺህ ስድስት መቶ ሰላሳ ስምንት ብር) መድረሱን መረጃው ያመለክታል፡፡
ከጥቂት ዓመታት በፊት ወደ 300 ሚሊየን ብር የሚጠጋ ሀገራዊ ገቢ ያላት ቤተክርስቲያን በአሁኑ ሰዓት ከሀገር ውስጥ ብቻ ይህን ያህል ብር ልትሰበስ ችላለች፡፡ መሰረታዊው ነገር ይህን ያህል ብር መሰብሰብ መቻሉ ሳይሆን ይህ ብር በምን አይነት የቤተክርስያኒቱን ችግር በሚቀርፉ ስራዎች መዋል አለበት? የሚለው ነጥብ ነው ፡፡  በአሁኑ ሰዓት ከ40 ሚሊየን በላይ ተከታይ ያላት ቤተክርስቲያን የሚረባ ካህናትና ማሰልጠኛ ኮሌጅ የላትም ፤ በተቃራኒው ከአንድ ሚሊየን የማይዘሉት በኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙ የካቶሊክ እምነት ተከታዮች በአዲስ አበባ  ለመላ ሀገሪቱ ላይ ላሉ የእምነት ተከታዮቻቸው ከቫቲካን በተገኝ እርዳታ በዩኒቨርሲቲ ደረጃ ትልቅ የትምህርት ተቋም እያስገነቡ ይገኛሉ ፡፡ ይህን ዩኒቨርሲቲ ለመጨረስ ከ400 ሚሊየን ብር በላይ እንደሚያስፈልግ ያገኝነው መረጃ ያመለክታል፡፡
ስለሆነም ትውልዱ የአባቶቹን የእምነት መስመር ተከትሎ የጠለቀ ቤተክርስቲያን እውቀት ያለው ፤ ማዕበል የማንገላታው ቀጣይ ትውልድ ለመፍጠር ቤተክርስቲያኒቱ ደረጃውን የጠበቀ የማስተማሪያ እውቀት የማስገብያ ተቋም መገንባት ይኖርባታል ፡፡ ይህ ለነገ የሚባል ጉዳይ አይደለም ፤ ዛሬ በእምነት እና በእውቀት የተኮተኮቱ መምህራን ካላፈራች ነገ ምዕመኑ በተኩላ ገበያ ሰንሰለት ውስጥ መውደቁ የማይቀር ነው፡፡ በንዝህላልነትና ሥራዋችን በአግባቡ ካለመሠራታቸው የተነሳ ባለፉት 20 ዓመታት ያጣቻቸውን ነፍሳት በትምህርት መመለስ ይኖርባታል፡፡ ስለዚህ የተሰበሰበው ገንዘብ ከቁጥር በላይ የሚታይ የሚጨበት ሥራ መስራት መቻል አለበት የሚል ጽኑ እምነት አለን፡፡

2013 ኖቬምበር 14, ሐሙስ

Help us by sharing this pic for the world to see!
oneTellSaudiArabia

 

ለዚህማ አልተፈጠርንም!

ከዲያቆን ዓባይነህ ካሤ

                                                             

ኢትዮጵያውያን ደማቸው የዐረብን አስፋልት አቀለመው፡፡ ባንዲራውን በራሱ ላይ ሸብ ያደረገው የእማማዬ ልጅ የእኔ ጀግና ማንነቱን እየተናገረ በአናቱ ላይ የወረደውን የድንጋዩን ናዳ በሀገሩ ፍቅር ተቋቁሞ በክብር አሸለበ፡፡ ለእርሱ ከዚህ በላይ ሌላ ድል አልነበረምና፡፡ ድንጋዩስ እርሱን አሳርፎታል፡፡ ነፍሱን ይማርልን እንጂ! ባንዲራችን ግን እንደተመታች እንደታመመች ናት፡፡ እውን ይኽ የሆነው በእኛ ላይ ነው? 


ይህቺ ባንዲራ እኮ ጨርቅ አይደለችም፡፡ ያ በሳኡዲ መሬት ተወግሮ የሞተው ወንድሜ የኮራባት በሞቱ ጊዜ የለበሳት የክብሩ፣ የማንነቱ መገለጫ እንጂ፡፡ ማንም ባይደርስለት ባንዲራው ነበረችለት፡፡ በእርሷ ተጽናና፡፡ ሞተ አልለውም መሰከረ እንጂ፡፡ ባንዲራ ለብሶ መከራን መጋፈጥ የሰማእታት ወግ ነው፡፡ 

ዳግማዊ ሆሎኮስት በኢትዮጵያውያን ላይ? እንዴት እንዴት? ደግሞ በ ፳፩ኛው ክፍለ ዘመን፡፡ የሰውን ሕይወት የሚያስገብር ምን ጥፋት ተገኝቶ ነው ወይስ የሟርት መስዋእታቸው እኛ ነን፡፡ "ከሕግ አስከባሪው ፖሊስ" እስከ ዱርየው የእኅቶቻችን ክቡር ሰውነት እንደ ውሻ ሲጎተት ከማየት የሚዘገንን አረመኔነት ምን አለ? ይህ እኮ ንቀት ነው፡፡ ይህ እኮ ድፍረት ነው፡፡ ይህ እኮ የሀገርን ሉዐላዊነት መድፈር ነው፡፡ 

2013 ኖቬምበር 10, እሑድ


ኢሕአዴግ እና የሃይማኖት ነጻነት

FACT Magazine Cover 02(ፋክት መጽሔት፤ ቅጽ ፪ ቁጥር ፲፱ ጥቅምት ፳፻፮ ዓ.ም.)
ተመስገን ደሳለኝ
… ኢሠፓ መራሹ መንግሥት በኢሕአዴግ ከተተካ ጥቂት ወራት ቢያልፈውም፣ የተራዘመው የእርስ በርስ ጦርነት ያልደረሰባቸው በደቡብ ኢትዮጵያ የሚገኙ አንዳንድ ከተሞችን ገና በቅጡ አልተቆጣጠራቸውም፤ በአናቱም በኢሠፓ መንግሥት ሽንፈት ሳቢያ እንዲበተን ከተገደደው የአገሪቱ መደበኛ ወታደር አብዛኛው ከእነትጥቁ የትውልድ መንደሩንና ቤተሰቡን መቀላቀሉ በአገሪቱ ላይ ከባድ ፍርሃት አንብሯል፡፡ በሰላም ወጥቶ ለመመለስ ርግጠኛ መኾን የማይቻልበት ከባቢያዊ አየርም አስፍኗል፡፡ በበርካታ ቦታዎች ተጠንተውና ታቅደው የሚፈጸሙ ወንጀሎችም ከአምስት እስከ ዐሥራ አምስት በሚደርሱ ወታደሮች የተደራጁ ልዩ ልዩ ሕገ ወጥ ቡድኖች በየማዕዘኑ እያቆጠቆጡ መኾኑን አመላክትዋል፡፡
በሌላ በኩል ደግሞ የዐዲስ አበባ ቆዳ ስፋትና የነዋሮዎቿ የአኗኗር ዘይቤን በቀላሉ ለመልመድ የተቸገሩ ተጋዳላዮች ለትንሽ ለትልቁ ግርግር ጠመንጃን እንደ መፍትሔ መምረጣቸው ችግሩን አባብሶታል፡፡ ጉዳዩ እያሳሰባቸው የሄደው የኢሕአዴግ ዋነኛ መሪዎችም እንዲህ ዐይነቱን አለመረጋጋትና ሥርዐተ አልበኝነት ለመቆጣጠር የመንፈሳዊ መሪዎች አስተዋፅኦ ወሳኝ ስለ መኾኑ ከስምምነት ላይ ደርሰዋል(እንደ ቀደሙት ሥርዐቶች ኹሉ ለቅቡልነት ከሚጠቀሙበት በተጨማሪ ማለት ነው)፡፡ ይኹንና በመንበሩ ላይ የነበሩት ፓትርያርኩ አቡነ መርቆሬዎስ አገር ለቀው እንዲወጡ በመደረጉ ክፍተት ተፈጥሯል፡፡
ይህ ጊዜ ነው ከ፲፱፻፸፬ ዓ.ም. ጀምሮ [ከኢየሩሳሌም ተሰደው] መኖርያቸውን አሜሪካን አገር ያደረጉ አንድ መንፈሳዊ አባት ወደ ኢትዮጵያ እንዲመጡ የተወሰነው፤ በጥሪው መሠረትም ወደ አገራቸው ሲገቡ መንግሥት የክብር አቀባበል አደረገላቸው፡፡ እኚኽ አባት ዛሬ በመንበረ ፕትርክናው የተሠየሙት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ነበሩ፡፡ ኾኖም ከሳምንት ሽር ጉድ በኋላ አቡነ ‹‹የኢዲዩ አባል ነበሩ›› የሚል ወሬ በአመራሩ አካባቢ በስፋት መሰራጨቱ ያልተጠበቀ ዱብ ዕዳ አስከተለ፡፡
ምክንያቱ ደግሞ ኢሕአዴግ እና ኢዲዩ በ፲፱፻፸ዎቹ መጀመርያ ትግራይ እና ጎንደር ውስጥ በርካታ መሥዋዕትነት ያስከፈለ ውጊያ ማድረጋቸው ብቻ አልነበረም፡፡ የመጀመርያዎቹ ሊቀ መንበሮች ስሁል ገሰሰ እና መሐሪ ተኽሌ(ሙሴ) ‹‹የተገደሉት በኢዲዩ ነው›› የሚለው ወሬ በድርጅቱ ውስጥ ከጫፍ ጫፍ የተናኘና የታመነበት ጉዳይ መኾኑ ነበር፡፡ በዚህም ላይ የህ.ወ.ሓ.ት መሪዎች ግራ ዘመምነት ተደማምሮ አቡነ ማትያስ በወቅቱ ወደ ታሪክነት ከተቀየረ ዓመታትን ባስቆጠረው ኢዲዩ ተፈርጀው ከታጩበት የፕትርክና መንበር ተገፈተሩ፡፡
ከዚህ በኋላ ነበር አብላጫውን የትጥቅ ትግል ዘመን በአሜሪካ ያሳለፉት አሰፋ ማሞ እና ብርሃነ ገብረ ክርስቶስ ‹‹ዉድብ›› የሰጠቻቸውን ተልእኮ ተቀብለው ወደ ዋሽንግተን ዲሲ ያመሩት፤ እናም ቀድሞም ትውውቅ ወደነበራቸው ብፁዕ አቡነ ጳውሎስ ዘንድ ሄደው ለፕትርክና ወንበር መታጨታቸውን አበሠሯቸው፡፡ በእንዲህ ያለ መንገድ መንግሥት የቀባቸው አቡነ ጳውሎስም እስከ ኅልፈታቸው ድረስ አወዛጋቢ መሪ ኾነው ዘልቀዋል፡፡
(በነገራችን ላይ በአሜሪካ ለመጀመርያ ጊዜ ከሲኖዶሱ ተነጥሎ የቆመ ቤተ ክርስቲያን የመሠረቱት አቡነ ጳውሎስ እንደነበሩ ይነገራል፡፡ አቡኑ ደርግ ለጥቂት ዓመታት አስሮ ከለቀቃቸው በኋላ ወደ አሜሪካ ሄደው የፈጣሪያቸውን ሰማያዊ መንግሥት ሲሰብኩ ቆይተው የህወሓት ሠራዊት ክንዱ እየበረታ በቁጥጥሩ ሥር ያዋላቸው ከተሞችም እየበዙ ሲሄዱ እርሳቸውም ስብከታቸውን ወደ ትግርኛ ቋንቋ ከመቀየራቸውም በላይ ለ‹ነጻ አውጭ›ው ድርጅት የገንዘብ ድጋፍ ያሰባስቡ ጀመር፡፡ የሥርዐት ለውጥ መደረጉን ተከትሎም በፖሊቲከኞች በተቀነባበረ ሤራ ከአቡነ ጳውሎስ ጋራ ቦታ የተለዋወጡት አቡነ መርቆሬዎስም፣ እዚያው አሜሪካ ‹ተተኪ›ያቸው የጀመሩትን ብሔር ተኮርና ከሲኖዶሱ የተገነጠለ ቤተ ክርስቲያን አስፋፍተው ዛሬ ለደረሰበት ‹የጎንደሬ ማርያም›፣ ‹የትግሬ ገብርኤል›. . .ለተሰኘ አሳፋሪ ክፍፍል ዳርገውታል፡፡ በርግጥ ለአቡኑ[አቡነ መርቆሬዎስ] ከአገር መውጣት የኢሕአዴግ እጅ እንዳለበት እንድናምን የሚያስገድደን በቅርቡ ታምራት ላይኔ ‹‹በእኔ ፊርማ ነው ያባረርናቸው›› ማለቱን ዊኪሊክስ ካደረሰን መረጃ በተጨማሪ በትጥቅ ትግሉ ዘመን ህወሓት በተቆጣጠራቸው በትግራይና ወሎ ነጻ መሬቶች በሚገኙ ከተሞች ያሉ ነዋሪዎችን ቀስቅሶና አደራጅቶ ፓትርያርኩ ላይ ‹‹ሽጉጥ ታጣቂ ጳጳስ››፣ ‹‹ቀይ ደብተር ያለው/ለኢሠፓ አባላት የሚሰጥ/ የሸንጎ ተወካይ››. . .የመሳሰሉትን መፈክሮች እያሰሙ በተቃውሞ ሰልፍ እንዲያወግዟቸው ማስተባበሩን ስናስታውስ ነው)፡፡
ዛሬስ የሃይማኖት ነጻነት የት ድረስ ነው?
ከላይ ታሪክን ወደ ኋላ መለስ ብዬ በደምሳሳው ለመጠቃቀስ እንደሞከርኹት፣ ኢሕአዴግ በሃይማኖት ጉዳይ እጁን ጣልቃ ማስገባት የጀመረው ክንዱ ሳይፈረጥም ገና በረሓ ላይ ሳለ ነበር፡፡ በዚህ ኹኔታ የተጀመረው ጣልቃ ገብነት ዛሬም ድረስ ተባብሶ ቀጥሏል፤ ምንም እንኳ በሃይማኖት ጉዳዮች ጣልቃ እንደማይገባ በደፈናው ከሕገ መንግሥቱ አንቀጽ ፲፩ን በመጥቀስ በተደጋጋሚ ለማስተባበል ቢሞክርም ያለፉት ዓመታት ተጨባጭ ተግባሮቹ የሚመሰክሩት ግልባጩን ነው፡፡ ድርጅቱ ራሱም ቢኾን ጥያቄው በተነሣ ቁጥር ከሕገ መንግሥቱ አንቀጽ ፲፩ን የሚጠቅሰው ለስሙ እንጂ ሕጉ ተግባራዊ አለመኾኑን ሳይረዳ ቀርቶ አይደለም፤ አቶ ተፈራ ዋልዋም በ፲፱፻፺፰ ዓ.ም. ኅዳር/ታኅሣሥ ወር ከታተመችው ሐመር መጽሔት ጋራ ባደረጉት ቃለ መጠይቅ ጉዳዩን አስመልክቶ የሰጡት አስተያየት የኢሕአዴግን አጭበርባሪነት ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ ነው፡-
‹‹ኢሕአዴግ እኮ የሚመራው መንግሥት በደርግም ጊዜ፣ በኃይለ ሥላሴም ጊዜ እንደሚታወቀው ‹የቤተ ክርስቲያን ሥራ አስኪያጅ ሹምልን› ተብሎ ተጠይቆ ‹የለም ራስዋ ቤተ ክርስቲያኒቱ ትሾማለች እንጂ እንደ ቀድሞው መንግሥት አይሾምላችኁም› የሚል መልስ የሰጠ መንግሥት ነው፡፡››
በሕዝበ ሙስሊሙ ተመርጦ ለእስር የተዳረጉት የኮሚቴ አባላትም በአንድ ወቅት ለሚመለከተው የመንግሥት ባለሥልጣን የጻፉት ደብዳቤ ጣልቃ ገብነቱን በግልጽ ያሳያል፡-
‹‹መንግሥት እንደ መንግሥት ሕዝቡ ተበድዬአለኹ፤ ምርጫ ይካሔድ፤ የመጅሊሱን አመራር አላመንኹበትም፤ ውክልና የለውምና ሕገ ወጥ ነው ያለውን አካል ሕገ ወጥነቱ እንዲረዝም ምርጫውን እርሱው እንዲያካሒድ መወሰን ሕዝብን ግራ አጋቢ ነው፡፡››
ሥርዐቱ በሃይማኖት ጉዳዮች ላይ ጣልቃ እንደማይገባ ለማሳመን ይህን ያህል ቢዳክርም በቅርቡ ‹‹የፀረ አክራሪነት ትግል የወቅቱ ኹኔታና ቀጣይ አቅጣጫዎች›› በሚል ርእስ የተዘጋጀው ባለ 44 ገጽ ሰነድ፣ መንግሥት በዘወርዋራ በሃይማኖት ጉዳይ ጣልቃ መግባቱን ሙሉ በሙሉ የሚያምን ኾኖ አግኝቸዋለኹ፤
‹‹የመንግሥት መዋቅራትን ሴኩላር መንግሥት መኾናችንን ዐውቆ የመንግሥትን መዋቅር ተጠቅሞ የራሱን ሃይማኖት መሠረት ያደረገ አገልግሎት ከመስጠት ሙሉ በሙሉ ያልጸዳ መኾኑን የተለያዩ ጥቂት የማይባሉ ገሃድ የወጡ መገለጫዎች አሉ፡፡ እንዲያውም የትኛውም አክራሪ ኃይል ከመዋቅር(ከመንግሥት) አካል በርታ ሳይባልና ሽፋን ሳይሰጠው የሚንቀሳቀስ እንደሌለ አማኞቹ በገሃድ ይገልጻሉ፡፡››
መቼም ይህን ያነበበ ዜጋ መረጃው የተገኘው በመንግሥት ከተዘጋጀ ሰነድ ሳይኾን በኒዮሊበራሊስት›ነት ከተፈረጁት እነ‹‹ሂዩማን ራይትስዎች›› እና ‹‹አምንስቲ ኢንተርናሽናል›› ቢመስለው አይደንቅም፡፡ ሐቁ ግን ይኸው ነው፡፡ አገዛዙ ላለፉት ኻያ ሁለት ዓመታት መንግሥት እና ሃይማኖት እንዲለያዩ ማድረጉን ሲለፍፍ ከመቆየቱም በላይ በሃይማኖት ጉዳይ ጣልቃ መግባቱን የዘገቡ ጋዜጠኞችን ከሥሦ ዛሬም ድረስ ፍርድ ቤት እያመላለሳቸው እንደኾነ ይታወቃል፡፡ ከዚህ አንጻር ይመስለኛል ዓለም አቀፍ ማኅበረሰቡን ጨምሮ በርካታ ኢትዮጵያውያን በእስር ላይ የሚገኙት የእነ አቡበበከር መሐመድ ክሥ፣ የሼኽ ኑር ሑሴን ግድያ፣ በማኅበረ ቅዱሳን ላይ እየተሰነዘሩ ያሉ ውንጀላዎችንና መሰል ፍረጃዎችን አምኖ ለመቀበል የተቸገሩት፡፡
ያም ኾነ ይህ ሃይማኖትን ብቻ ሳይኾን ዕድርና ዕቁብንም ሳይቀር ‹ካልተቆጣጠርኹ ሞቼ እገኛለኹ› በሚል የቁጥጥር ልክፍት የተያዘው ኢሕአዴግ፣ በተለይም 99.6 ድምፅ አግኝቼ አሸንፌአለኹ ብሎ ካወጀበት ከምርጫ ፳፻፪ ማግሥት ጀምሮ ‹‹አናት ላይ ከተቀመጡ መሪዎቻቸው በቀር ሙሉ በሙሉ አልተቆጣጠርናቸውም›› የሚላቸውን የኦርቶዶክስ ክርስትና እና የእስልምና እምነቶችን ዋነኛ አጀንዳ አድርጎ እየሠራ ለመኾኑ በርካታ መረጃዎች አሉ፡፡
በ፳፻፫ ዓ.ም. ኅዳር ወር ‹‹የአምስት ዓመት የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድና የኢትዮጵያ ሕዳሴ›› በሚል ርእስ በአቶ መለስ ዜናዊ ተሰናድቶ የተሰራጨው ጥራዝ፣ የሥርዐቱን ቀጣይ አካሔድና ይህን ኹናቴ የሚያሳይ ከመኾኑም በተጨማሪ ዛሬም ድረስ በሃይማኖት ጉዳዮች ላይ መንግሥት የሚያዘጋጃቸው ሥልጠናዎችም ኾኑ ጥናታዊ ጽሑፎች መነሻ ሐሳባቸው ይኸው ዳጎስ ያለ ጥራዝ እንደኾነ ይነገራል፡፡
ጥራዙ የእምነት ተቋማትን በተመለከተ ከገጽ 128 – 132 ያካተተው ሐሳብ፣ ለኪራይ ሰብሳቢነት ዋነኛው ምክንያት ‹‹የሃይማኖት አክራሪነት›› መኾኑን ከጠቃቀሰ በኋላ ችግሩን ‹‹ተኪ የኾነ ልማታዊ አስተሳሰብ›› በማምጣት ማስወገድ እንደሚቻል ይመክራል፡፡ ይህን ከግብ ለማድረስ ደግሞ ሚዲያዎችንና ተያያዥነት ያላቸውን ማኅበራት መጠቀሙ አዋጭ እንደኾነ ይተነትናል፡፡ የኢሕአዴግ አባላት በየእምነት ተቋሞቻቸው ያሉ ማኅበራትን በዐይነ ቁራኛ መከታተል እንዳለባቸውም ያሳስባል፡- ‹‹[የግንባሩ አባላት] ከእምነት ተቋማት ውጭ ባላቸው አደረጃጀት አማካይነት በሰፊው መሥራት አለብን››፡፡ በርግጥም የእስልምና እምነት ተከታዮች ‹‹የሃይማኖት ነጻነት ይከበር›› የሚል ተቃውሟቸውን ባጠናከሩበት ሰሞን፣ አዲስ አበባን ጨምሮ በተለያዩ ክልሎች የሚገኙ ሙስሊም አባላቱን ለብቻ እየሰበሰበ እንቅስቃሴውን የማክሸፍ ሥራ መሥራት ግዴታቸው መኾኑን የሰበከው ከዚኹ አቶ መለስ ዜናዊ አዘጋጅተውት ከነበረው ጥራዝ ነው ብሎ መከራከር ይቻላል፡፡
ከጣልቃ ገብነት ወደ ጠቅላይ ተቆጣጣሪነት
በዘወርዋራም ቢኾን በሃይማኖት ጉዳይ ጣልቃ መግባቱን ሙሉ በሙሉ የሚያምነው ከላይ የተጠቀሰው ሰነድ በአገሪቱ ‹‹የሃይማኖት አክራሪነት›› መከሠቱን ካተተ በኋላ ዋነኛ ተጠያቂዎች አድርጎ ያቀረበው እንደወትሮው ኹሉ ለተደጋጋሚ መሸማቀቅ የተዳረጉትን መንፈሳዊ መሪዎችንና ማኅበራትን ሳይኾን የመንግሥት መዋቅርን ነው፡-
‹‹የመንግሥት መዋቅራችን አካል ኾነው አክራሪነቱን በድብቅም በገሃድም የሚደግፍ አካል በፌዴራልም በክልልም ከሞላ ጎደል የሚታወቁ ናቸው፡፡ እነዚኹ አካላት በተቻላቸው ኹሉ በመድረክ ጤናማ እየመሰሉ የሚኖሩ ናቸው፡፡ የፀረ አክራሪነቱን ትግል ማጧጧፍ የሚፈልገውን መዋቅር አካልም ይኹን የሕዝብ አካል በተደራጀና በመረባቸው አማካይነት ከፍተኛ ጫና የሚያሳድሩ፣ የተቋማቸውን ምቹ ኹኔታ ተጠቅመው በፀረ አክራሪነት የሚንቀሳቀሱትን አካል የሚቀጡ፣ አሉባልታ እየፈጠሩ የሚያሸማቅቁ፣ ኾን ብለው ድጋፍ የሚነፍጉና በሐሰት ምስክርም ጭምር ዜጎችን የሚያሳስሩ ናቸው፡፡ የመንግሥትን አቅሞች ተጠቅመው አክራሪነትን የሚያስፋፉና ከአክራሪነት እንቅስቃሴ ጋራ በተለያዩ ጥቅሞች የተሳሰሩ ናቸው፡፡››
እነኾም በእንዲህ ዐይነቱ የውንብድና ተግባር የተሠማሩ ባለሥልጣናት የተሰባሰቡበት፣ ውንብድናው መኖሩንም የሚያምን መንግሥት አንድም ተጠያቂዎቹን ለሕግ አሳልፎ አለመስጠቱ፣ አልያም ሥልጣኑን በፈቃዱ አለመልቀቁ በአገር ላይ ሊያስከትል የሚችለውን አደጋ ለመረዳት ነቢይነትን አይጠይቅም፡፡ በአናቱም ሥርዐቱ ለሕግ የበላይነት ተገዥ አለመኾኑን የሚያሳየው በዚህ ደረጃ ‹‹ችግሩን ተረድቸዋለኹ›› እያለም እንኳ፣ ዛሬም የቅጣት ብትሩን ያሳረፈው ከመዋቅሩ ጋራ አንዳችም ንክኪ በሌላቸው መንፈሳዊ መሪዎች ላይ መኾኑ ነው፡፡ በርግጥም ይህ ዐይነቱ አሠራር ከዐምባገነን አስተዳደር መገለጫዎች አንዱ ነው፡፡ ኢሕአዴግም ያለፉትን አራት ምርጫዎች ጨምሮ በተለያየ ጊዜ የዴሞክራሲም ኾነ የሰብአዊ መብትን በዐደባባይ መጣስ፣ የሐሰት ክሦችንና ፍረጃዎችን እንደ ምክንያት መጠቀም ነባር ስልቱ እንደኾነ ይታወቃል፡፡ በማኅበረ ቅዱሳን ላይ እየዘረዘረ ያለው የፈጠራ ውንጀላ እና ለሙስሊሙ ‹‹መፍትሔ አፈላላጊ›› ተብለው በተመረጡት የኮሚቴ አባላት ላይ የወሰደው ዕመቃ መግፍኤ ይኸው ነው፡፡
ሌላው ቀርቶ ከዚህ ቀደም በተቃዋሚ ፓርቲ አባላት ላይ ስለሚፈጸመው የግፍ ግድያዎች ይሰጥ የነበረውን ምክንያት በመንፈሳዊ ሰዎችም ላይ ያለአንዳች የይዘት ለውጥ ለመጠቀም አላመነታም፡፡ እንደሚታወሰው በድኅረ ምርጫ – ፺፯ በአምቦና በኢተያ በታጣቂዎች የተገደሉትን የኦሕኮ አባላት ከተፈጥሮ ሕመም ጋራ አያይዞት ነበር፡፡ በያዝነው ዓመት ጥቅምት ወር መጀመርያ ላይ በተካሔደው የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ዓመታዊ ስብሰባ ላይ ደግሞ የምዕራብ ወለጋና አሶሳ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አቡነ ኄኖክ ‹‹ቤጊ›› ወረዳ በመንግሥት ባለሥልጣናት ተፈጸመ ያሉትን ግድያ ለፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስትር ተወካይ፡-
‹‹በቤተ ክርስቲያን 70 ሜትር ርቀት ላይ የሌላ እምነት ተከታዮች የራሳቸውን ቤተ ክርስቲያን እንዲሠሩ መፈቀዱን ከተቃወሙት መካከል አንድ ዲያቆን ተደብድቦ በሦስተኛው ቀን ሕይወቱ ሲያልፍ ‹በወባ በሽታ ነው የሞተው› ተብሎ ለፍርድ ቤቱ የሐሰት ማስረጃ ከዶክተሩ እንዲቀርብ ታዘዘ›› ማለታቸውን መጥቀሱ ለጉዳዩ አስረጅነት በቂ ይመስለኛል፡፡
የኾነው ኾኖ አገዛዙ በዘረጋው ግዙፍ መዋቅሩ ውስጥ ያልታቀፉ ማኅበራትንም ኾነ የሃይማኖት ተቋማትን የስጋት ምንጭ አድርጎ ማየቱ፣ በእምነት ነጻነት ላይ ጣልቃ ለመግባትም ኾነ ምንም ዐይነት ገለልተኛ ተቋማት እንዳይኖሩ ዕንቅልፍ ዐጥቶ መሥራቱን ያሳያል ብዬ አስባለኹ፤ በሚቆጣጠራቸው የኤሌክትሮኒክስና የኅትመት ሚዲያዎች ቀን ከሌት የፕሮፓጋንዳ ከበሮ የሚመታበት የ‹አክራሪነት› ፍረጃም መነሾው ይኸው ይመስለኛል፡፡ ሰነዱን ከዚህ ቀደም ካየናቸው ለየት የሚያደርገው፣ በመንግሥት መዋቅር ውስጥ አሉ ከሚላቸው ወንበዴዎች በተጨማሪ የሚከሥሣቸውን መንፈሳውያን ማኅበራት በደፈናው ‹‹በክርስትና እምነት ውስጥ ያሉ›› ብሎ አለማለፉ ነው፤ ቃል በቃል እንዲህ ይላልና፡-
‹‹በማኅበረ ቅዱሳን ውስጥ የመሸጉ የትምክህት ኃይሎች ጽንፈኛ የፖሊቲካ ኃይሎች አካል በመኾን በጋዜጣና በመጽሔት ሕዝባችንን ለዐመፅና ለሁከት ለማነሣሣት ከፍተኛ ጥረት አድርገዋል፡፡. . .በራሳችንም ኃይል እንደሌላው ሰልፍ ልንወጣ ይገባል በሚል የዐመፅና የሁከት ቅስቀሳ ለማድረግ ይፈልጋሉ፡፡››
ይህ ኹኔታ መንግሥት መንፈሳውያን ማኅበራትን ጠቅልሎ ለመቆጣጠር በመፈለጉ ለተቃዋሚዎች ያሠመረውን ‹ቀይ መሥመር› መጣሱን ያሳያል፡፡ አስገራሚው ጉዳይ ደግሞ የሃይማኖት ተቋማትን የፖሊቲካ መሣርያ አድርጎ መጠቀሙ አልበቃ ብሎት ወደ መንፈሳውያን ማኅበራቱ መዞሩ ነው፡፡
በገሃድ እንደሚታወቀው የክርስትና ይኹን የእስልምና እምነት መሪዎች በተለያየ ጊዜ ከሥርዐቱ ጎን ተሰልፈው ‹ናዳን ለመግታት› ያደረጉት አበርክቶ በቀላሉ የሚገመት አለመኾኑ ነው፡፡ በርግጥም ‹‹የቄሣርን ለቄሣር›› በሚል አስተምህሮ የሚያድሩ፣ ደመወዛቸው በምድር ያልኾኑት መንፈሳውያን አባቶች በድኅረ ምርጫ – ፺፯ ሕፃናትን ሳይቀር በጥይት የፈጀውን ሥርዐት ማውገዝ ቀርቶ መምከር ያለመፈለጋቸው ምክንያት ፍርሃት ብቻ ሳይኾን የግል ጥቅምን ታሳቢ ያደረገው ግንኙነታቸው ያሳደረው ተጽዕኖ ይመስለኛል፡፡ ከቅዱሳን መጻሕፍት ይልቅ አብዮታዊ ዴሞክራሲን ‹አዳኝ› አድርገው የመቀበላቸው መግፍኤ ይኸው ነው፡፡ ኢሕአዴግም ‹ነገረ መለኰት›ን ለሲኖዶሱና ለመጅሊሱ እስከ ማስተማር ድረስ የደፈረው የእነርሱ ለሁለት ጌታ መገዛት ነው – ለገንዘብ እና ለጌታ፡፡
የሲኖዶሱ እና የመንግሥት ፍጥጫ
በኦርቶዶክስ ክርስትና እምነት ሕገ ቤተ ክርስቲያን ሲኖዶስ ከፍተኛውን ሥልጣን የሚይዝ ሲኾን ፓትርያርክንም የመሾምና የመሻር ሥልጣን አለው፡፡ ኾኖም ይህ የላዕላይ መዋቅር እስከ አቡነ ጳውሎስ ኅልፈት ድረስ ለእርሳቸውም ኾነ ለሥርዐቱ ሰጥ ለጥ ብሎ የሚገዛ ጥርስ የሌለው አንበሳ በመኾኑ ለትችት ከመዳረጉም በላይ በምእመናን ዘንድ ለመንፈሳውያን አባቶች የሚሰጠው ክብርም ተነስቶት ቆይቷል፡፡
ይኹንና በያዝነው ዓመት ጥቅምት ወር መጀመርያ በተካሄደው የመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ፴፪ ዓመታዊ ስብሰባ ላይ ከመንግሥት የተወከሉ ሓላፊዎች÷ ‹‹የብዝኃነት አያያዝ አክራሪነት/ጽንፈኝነት ዝንባሌዎቹና መፍትሔዎቹ›› በሚል ርእስ ያቀረቡትን ጥናት ተከትሎ ስድስት ጳጳሳት ቀድሞ ባልታየ መልኩ ጠንካራ ተቃውሞ ማቅረባቸው፣ በብዙዎች ዘንድ የሃይማኖት መሪዎች ለመንፈስ ልዕልና ሊገዙ ይኾን? ከምድራዊው ይልቅ ሰማያዊውን ሊመርጡ ይኾን? ‹‹እመን እንጂ አትፍራ›› የሚለውን አስተምህሮአቸውን ሊተገብሩ ይኾን? የሚል ጥያቄ አጭሯል፡፡
በዕለቱ የመጀመርያው ተናጋሪ የነበሩት የሰሜን ወሎና ዋግ ኽምራ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አቡነ ቄርሎስ በጥናቱ ላይ መቻቻል አስመልክቶ የቀረበውን ድምዳሜ እንዲህ ሲሉ ነበር ያጣጣሉት፡-
‹‹ይኼ አክራሪነት፣ ጽንፈኝነት የሚለውን ቋንቋ እናንተው ናችኹ ያሰማችኹን፤ ከዚህ በፊትም አይታወቅም፣ በደርግም ይኹን በሌላ፡፡ እንደገና ደግሞ ብዙ ጊዜ ጽንፈኝነት፣ አክራሪነት እያላችኹ ዕድሜ ሰጥታችኹ ያበለጸጋችኋቸው እናንተው ናችኹ፡፡››
በርግጥም አቡኑ የተቹት ሥርዐቱ የፕሮፓጋንዳው ፋሽን ያደረገውን ‹‹መቻቻል››ን ብቻ አይደለም፤ ‹‹በመቃብሬ ላይ ነው የሚሻሻለው›› የሚለውን የመሬት ፖሊሲንም ነው፡፡. . . ‹‹በፊት መሬትም ሕዝብም የነገሥታቱ ነበር፤ አሁንስ የማን ነው? ይልቁንም ከአንድ ቤት ‹ግድግዳው የቤቱ ባለቤት ነው፤ ሳሎኑ የመንግሥት ነው› የሚለው ዐዋጅ የአሁን አይደለም እንዴ? ለኢትዮጵያዊነቱ ዋስትና የለውም፤ ይኼ የእኔ ነው የሚለው ከሌለ ምንድን ነው? ይህች የእኔ የኢትዮጵያዊነቴ መገለጫ ናት ካላለ ምንድን ነው ኢትዮጵያዊነት? አሁንም መሬቱም ሕዝቡም የእናንተው ኹኖ ሳለ ለፊቱ፣ ለነገሥታቱ መስጠታችኹ በምን ተመልክተውት ነው?››
የደቡብ ጎንደር ሀ/ስብከት ሊቀ ጳጳስ አቡነ እንድርያስም በሚያስተዳድሩት አካባቢ ያለውን የመንግሥት ጣልቃ ገብነትና ተጽዕኖን ከዘረዘሩ በኋላ ለተሰነዘረው ፍረጃና ማሸማቀቂያ እንዲህ የሚል አስተያየት ሰጥተዋል፡-
‹‹የተበደለ ሰው ሲናገር ‹ፖሊቲካ ተናገረ› እየተባለ የውሸት ውሸት ሲያተራምሱን የሚኖሩ ብዙዎች ናቸው፡፡. . .እንዴ! የመንግሥት ሥልጣን የተረከቡ ወንድሞች የእኛን አፍ፣ የእኛን አንደበት ብቻ ነው እንዴ የሚጠብቁት፤ ለሌሎች ሞራል ይሰጣሉ ማለት ነው?. . .ለምንድን ነው ግን በሽፋንነት የምትጠቀሙብን? መንግሥት እኛን ሽፋን አድርጎ ነው ሲበዘብዘን የምንኖረው፡፡ ሌባውም ቀጣፊውም ሰርጎ ገቡም ሲያጭበረብረን ሲያታኩሰን መንግሥትን ሽፋን አድርጎ ነው፡፡››
የወላይታ ሀ/ስብከት ሥራ አስኪያጅም በተመሳሳይ መልኩ መንግሥት በሃይማኖት ጉዳይ ጣልቃ መግባቱን ቤተ ክርስቲያኗ ስትቃወም ጉዳዩን ወደ ፖሊቲካ እየቀየሩ ማስፈራራቱ እንደተለመደና ለቀብር ማስፈጸሚያ የሚኾን መሬት ከመስተዳድሩ በሚጠየቅበት ጊዜ የሚሰጠው መልስ በሐሰት መወንጀል እንደኾነ ከገለጹ በኋላ ጉዳዩ መፍትሔ ካላገኘ ሊከተል ስለሚችለው ስጋታቸውን ተናግረዋል፡-
‹‹ ‹የፖሊቲካ ጉዳይ ነው፤ ሕዝብን በሃይማኖት ሽፋን ታንቀሳቅሳላችኹ› እየተባልን እየተሸማቀቅን ያለንበት ኹኔታ ነው ያለው፡፡ ይህን እንዴት ታዩታላችኹ? መቻቻልስ የሚመጣው ከምን አኳያ ነው? ዝም ብለን የምንቀመጥ ከኾነ ምናልባት ሓላፊነት ለመውሰድ ስለሚከብደን ይህን ወርዳችኹ እንድትፈትሹ ለማለት ነው፡፡››
(በነገራችን ላይ የአጠቃላይ ጉባኤው ዓመታዊ ስብሰባ በተጠናቀቀ ማግሥት ከማኅበረ ቅዱሳን አመራር ሦስት አባላት ወደ ፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ተጠርተው ዶ/ር ሽፈራውን ጨምሮ ከሚመለከታቸው ሓላፊዎች ጋራ ውይይት ማድረጋቸውን ከመሥሪያ ቤቱ ምንጮቼ ሰምቻለኹ፡፡ ሚኒስትሩ ከማኅበሩ አመራሮች ጋራ ለመወያየት የተገደዱት ካልተጠበቀው የሲኖዶሱ አባላት ድፍረት ጀርባ ‹የማኅበረ ቅዱሳን እጅ አለበት› የሚል ጥርጣሬ በመያዙ ነው፡፡ በውይይቱም ላይ የተንጸባረቀው የአባላቱ መለሳለስ፣ ማኅበሩን አክራሪ ብለው እንደማያምኑና ከዚህ ቀደም የተሰራጩት ወንጃይ ሰነዶችን ሳይቀር ‹አናውቃቸውም› እስከማለት የደረሰ እንደነበር አረጋግጫለኹ፡፡ ይኹንና ይህ እሳት ማጥፊያ ስልት ከሥርዐቱ ጋራ የቆየ መኾኑ ይታወቃል፤ የማኅበሩ አመራርም ይህ ይጠፋዋል ብዬ ባላስብም፤. . .)
የኾነው ኾኖ [በአጠቃላይ ጉባኤው ዓመታዊ ስብሰባ] ከፌዴራል ጉዳዮች ከመጡት ሦስት ተወካዮች መካከል አቶ ገዛኽኝ ጥላሁን አብዛኛውን ጥያቄ በተመለከተ የሰጡት ምላሽ የወከሉት መንግሥት ዛሬም በተሳሳተ ታሪክ ንባብ እያሸማቀቀ፣ እያስፈራራ፣ ሕግን እየጠመዘዘ፣ እስር ቤት እየከተተ. . . የፖሊቲካ ጥቅሙን ማስከበር ላይ ያተኮረ መኾኑን ያሳያል፡፡ ሓላፊው ማስጠንቀቂያውን ያስተላለፉት እንዲህ በማለት ነው፡-
‹‹መጀመርያ ግንዛቤ ላይ እንሥራ በሚል ርምጃ አልወሰድንም፡፡ ኮሽ ባለ ቁጥር ወደ ቃሊቲ መፍትሔ አይኾንም፡፡››
. . .‹ቃሊቲ›ን ምን አመጣው? መቼም ለጣልቃ ገብነቱ ከዚህ የበለጠ ማሳያ መፈለግ ‹ዐውቆ የተኛን. . .› እንደመኾን ነው፡፡ ‹‹መንግሥት እና ሃይማኖት የተለያዩ ናቸው›› ብሎ መከራከሩም ጊዜ ያለፈበት ፕሮፓጋንዳ ይመስለኛል፡፡ እናም የተሻለው መንገድ ከላይ በጠቀስኹት ሰነድ ‹‹በየማእከላዊ ኮሚቴው በሚካሄደው የስምሪት ተግባር በፀረ አክራሪነት ትግል ላይ ያለው የእያንዳንዱ ግለሰብ ቁመና መፈተሽ አለበት›› ተብሎ የተገለጸውን ማሳሰቢያ በፍጥነት በመተግበር፣ በቅድሚያ ራስን ከአክራሪነትና አሸባሪነት ማራቅ ነው፡፡ ማረጋገጫ የማይቀርብበትን አፈ ታሪክንም እየለቃቀሙ በአንድ ሃይማኖት ላይ መለጠፉ አስተማሪ አይመስለኝም፡፡
ከዚህ ባለፈ ‹‹የሃይማኖት ኮማንድ ፖስት አቋቁመን ለችግሩ እልባት እንሰጣለን›› የምትሉት ጉዳይ በቀጥታ መንግሥት በሃይማኖት ጉዳይ እጁን ማስገባቱን በዐደባባይ ከማመን ያለፈ የፖሊቲካ ጠቀሜታ አይኖረውም፡፡ ጳጳሳቱም ኾኑ ሼኾቹ ሓላፊነትና ግዴታቸው ሰማያዊውን መንግሥት መስበክ እንጂ ከሰላይ አለቆችና ከፖሊስ አዛዦች ጋራ ቢሮ ዘግተው የመንፈስ ልጆቻቸውን ‹‹ትምክህተኛ››፣ ‹‹አሸባሪ››፣ ‹‹አክራሪ››. . .እያሉ እንዲፈርጁ መፈታተኑ ያልታሰበ ሕዝባዊ ቁጣ መቀስቀሱ አይቀርም፡፡

                                   በአውሮጳ   የካህናት አንድነት ማኅበር ሊቋቋም መሆኑ ታወቀ በ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከመላዋ አውሮጳ   የተውጣጡ ካህናት፡” የ...