2014 ኦገስት 11, ሰኞ

ኦ ፍና/ቆፍና ቅዱስ አማኑኤል ቤተክርስቲያን


ከአዲስ አበባ 185 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በመርሐቤቴ ወረዳ በዓላም ከተማ  የሚገኝ  በ4ኛው ክፍለ ዘመን በአባ ሰላማ ካሣቴ ብርሃን አማካይነት በአብርሃ ውአጽብሃ ነገሥታት  እንደታነጸ ይነገራል፡፡
ነገሩ እንዲህ ነው በ4ኛው ክ/ዘ ነገስታቱ አብርሃ ወአጽብሃ ከጳጳሱ አባ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን ጋር በመሆን አብያተ ክርስቲናትን በማሳነጽ  በማስፋፋት ላይ በነበሩበት  ጊዜ በመርሐቤቴ ሲያልፉ አሁን ቤተክርስቲያኑ የታነጸበት ቦታ  ጳጳሱ አባ ሰላማ አረፍ አሉ፡ እዚያው እያሉ ጌታችን የተወለደባትን  ቤተልሔምን በራእይ  አሳያቸው ከቦታውም ጋር አመሳስሎ ካሳያቸው በኋዋላ  ቤተ ክርስቲን መስራት እንዳለባቸው ተገነዘቡ፡፡ ይህ መንገድ በጣም ድንቅ ነው ሲሉ ኦ ፍና ብለው ጠሩት /ቆፍና ማለት፡  ቆፍ  ብሂል ቅሩበ እግዚአብሔር ማለት ነውና  እገዚአብሔር የቀረበው ቦታ ነው ሲሉ እንዲህ ሰይመውታል፡፡ከዚያ ተነሳ  በእውነት እግዚአብሔር ከኛ ጋር ነው  በማለት የቅዱስ አማኑኤል ቤተክርስቲያን እንዲታነጽ ወሰኑ፡፡አማኑኤል ማለት እገዚአብሔር ከኛ ጋር ነው ማለት ነውና፡፡ይህ ጥንታዊ ቤተ ክርስቲያን እጅግ በጣም የቆዩ ቅርሳቅርስ የሚገኙበት ታርካዊ  ጥንታዊ ነው ፡፡ ባሁኑ ሰዓት በቦታው የሚገኙትን ቅርሶች ለጎብኚዎች በሚመች መልኩ ላስቀመጥና ለጉብኝት ዝግጁ ላማድረግ የደብሩ ሰበካ ጉባዔ ከሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች ጋር በጋራ በመስራት ላይ መሆናቸውን የደብሩ አስተዳዳሪ ሊቀ ትጉሃን ጳውሎስ ገልጸዋል፡፡ ኦ ፍና ቅዱስ አማኑኤል በአሁኑ ሰዓት ኦ ፍና አምሳለ ቤተልሔም ቅዱስ አማኑኤል ቤተ ክርስቲያን በሚል በብፁዕ አቡነ ኤፍሬም የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ተሰይሞአል፡፡ ይህ ጥንታዊ ደብር ከርእሰ አድባራት ተድባበ ማርያም  ቤተ ክርስቲያን  ቀጥሎ መሠራቱ  ይታውቃል፡፡ቦታውን ከፍ አድርጎ ትራራ ላይ ለመሥራት ታስቦ በውቅቱ የነበሩት  ምእመናን  ከተለያ ቦታዎች አፈር አምጥተው ስለደለደሉት አራት አይነት አፈር በቦታው ይገኛል፡፡ ደብሩም በግራኝ አህመድ ጊዜ በመቃጠሉ ብዙ ቅርሶች የወደሙ ሲሆን በየጊዜው የተነሱ ነገሥታት መልሰው  አሳንጸውታል፡፡ ምእመናን!  ወደ ቦታው በመሄደ እንድትጎበኙ የደብሩ ሰበካ ጉባኤ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡


2014 ኦገስት 8, ዓርብ

ልጆችም ወላጆችም የሚተባበሩበት የፍልሰታ ለማርያም መታሰቢያ ጾምና በዓል


(አለቃ አያሌው ታምሩ)
  • በኢትዮጵያ እመቤታችንን መውደድ በልማድ እንደ ተረት በማይታይ ዓይነት ኹኔታ ተስፋፍቶ የኖረ አይደለም፡፡ ወንድም ሴትም ቢኾኑ እንዳላቸው የእምነት መጠን በእመቤታችን ስም ጸሎት ጸልየው፣ ስእለት ተስለው፣ ምጽዋት አድርገው፣ ዝክርዋን ዘክረው፣ ስምዋን ጠርተው፣ በአማላጅነትዋ ተማፅነው ዐሳባቸው እየተፈጸመላቸው፣ የጎደለው እየሞላላቸው፣ የጠመመው እየተቃናላቸው፣ ድውያን ፈውስ በማግኘት፣ ሠራተኞች ለሥራቸው የተቃና መንገድ በማግኘት፣ መምህራን በሚያስተምሩበት፣ ቅዱሳን ገድላቸውን በሚፈጽሙበት ጊዜና ምክንያት ኹሉ የእመቤታችንን ረድኤት እያገኙ ስለሔዱና ዛሬም ያው ያልተቋረጠ ስለኾነ ነው፡፡
  • ከቀደሙ ሰዎች ታሪክ ከእስራኤል መሳፍንት አንዱ ለኾነው የዮፍታሔ ልጅ መታሰቢያ ልጆች ወይም ደናግል በየዓመቱ በዓል ሲያከብሩ እንደነበረ ተነግሯል፡፡ (መጽ. መሳ.፲፩፥፵፡፡) እንዲህ ከኾነ ዘንድ ኢትዮጵያውያት ቆነጃጅትና ሕፃናት፥ ኢትዮጵያውያን ጎልማሶች የእናታችንን፥ የእመቤታችንን የቅድስት ድንግል ማርያምን መታሰቢያ በየዓመቱ ሲያከብሩ የበለጠ ነገር ፈጽመዋል ማለት ነው፡፡
    *                 *                 *
መሠረተ ቃል፡-
  • ‹‹ተንሥአ እግዚኦ ውስተ ዕረፍትከ አንተ ወታቦተ መቅደስከ፡፡›› ‹‹አቤቱ ወደ ዕረፍትህ
    ተነሥ፤ አንተና የመቅደስህ ታቦት፡፡›› (መዝ.፻፴፩፥፰)
  • ‹‹ተንሥኢ ወንዒ ቅርብትየ እንቲአየ ሠናይት ርግብየ ውስተ ጽላሎት ኰኵሕ ቅሩበ
    ጥቅም፡፡›› ‹‹አቅራቢያዬ መልካማ ርግቤ ተነሽ ነዪ በግንቡ አጠገብ ወዳለው ወደ ዋሻው
    ጥላ፡፡›› (መኃ.፪፥፲-፲፬)
ቅዱስ እግዚአብሔር ሰው ለመኾን፥ የሰው ልጅ ለመባል ባሰበው የመጀመሪያው የተስፋው መንገድ የምትገኘው፥ ለእናትነት የመረጣት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት፡፡ ኢትዮጵያ በእመቤታችን ስም ቤተ ክርስቲያን ትሠራለች፤ ልብዋንም በረድኤትዋ ላይ አሳርፋ በቤተ ክርስቲያንዋ ውስጥ ለእግዚአብሔር መሥዋዕት፥ ጸሎት፥ ምጽዋት፥ ስግደት ታቀርባለች፡፡ በእመቤታችን አማላጅነትም ትማልዳለች፡፡ እንዲኹም የማይጠፋ ስም ተሰጥቷታልና በመዝሙር ፵፬ ፥ ፲፪ – ፲፮ በተጻፈው መሠረት ወላጆች ከነልጆቻቸው ተሰብስበው የእመቤታችንን የልደትዋን፥ ጌታን ለመውለድ ብሥራት የመቀበልዋን፥ የመውለድዋን፥ የዕረፍትዋን፥ የትንሣኤዋን፥ የዕርገትዋን በዓል ያከብራሉ፡፡
በኢትዮጵያ ከፍ ብሎ የሚታየው በብዛት ልጆች ተሳትፎ የሚያደርጉበት የፍልሰታ ጾምና በዓል ነው፡፡ ፍልሰታ የሚለው ቃል የእመቤታችን ሥጋ ከጌቴሴማኒ ወደ ገነት መፍለሱን፣ ኋላም በገነት በዕፀ ሕይወት ሥር ከነበረበት መነሣቱን ለማመልከት የሚነገር ቃል ነው፡፡
filseta lemariam
የአምላክ እናት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አምላክን በወለደችበት፣ ስብሐተ መላእክትን በሰማችበት፣ ባየችበት የልደት ወራት አካባቢ በ፷፬ኛ ዓመቷ ጥር ፳፩ ቀን ከዚኽ ዓለም በሞት ተለይታ ወደ ሰማይ ስትወጣ በሰማይም በምድርም ለሰውም ለመላእክትም ከልጅዋ፣ ከባሕርይ አባቱ ከእግዚአብሔር አብ፣ ከባሕርይ ሕይወቱ ከእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ የተሰጣት ጸጋና ክብር ተገልጧል፡፡ ለእናታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም በሰማይ በፍጹም ደስታ አስተርእዮ ኾኗል፡፡ በመጀመሪያ ዐብረዋት የኖሩት ልጆችዋ ቅዱሳን ሐዋርያት በሥጋ ያሉት ከየሀገረ ስብከታቸው ተሰብስበው፣ ከዚኽ ዓለም የተለዩት በአካለ ነፍስ ተገኝተው የዕረፍቷን ጊዜ እየተጠባበቁ ሳሉ፤ እመቤታችን፤ ‹‹ማዕጠንት አምጡ፤ በጸሎትም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ጥሩት፤›› አለቻቸው፡፡ እነርሱም ትእዛዟን በመፈጸም ላይ ሳሉ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱሳን መላእክትን አስከትሎ በክብር፥ በጌትነት ተገለጠ፡፡ እናቱንም፤ ‹‹የተወደድሽ እናቴ ሆይ! ዛሬ ድካምና ሕማም ወደሌለበት ወደ ዘለዓለም መንግሥት ላሳርግሽ መጥቻለኹ፤ ወደ እኔ ነዪ፤›› እያለ ሲያነጋግራት ቅድስት ነፍስዋ ከክቡር ሥጋዋ በልጅዋ ሥልጣን ተለየች፤ ልጅዋም በክብር ተቀበላት፡፡ በዚኽ ጊዜም ነቢዩ ዳዊት፤ ‹‹ወትቀውም ንግሥት በየማንከ በአልባሰ ወርቅ ዑጽፍት ወኁብርት፤›› እያለ ያመሰግናት ነበር፡፡ ቅዱሳን መላእክት፥ ነቢያት፥ ሐዋርያት፥ ጻድቃን፥ ሰማዕታት በዚያው ከበው ቆመው፤ ‹‹ጸጋን የተመላሽ ሆይ! እግዚአብሔር ከአንቺ ጋራ ነውና ደስ ይበልሽ፤›› እያሉ ያመሰግኗት ነበር፡፡ በዚኽ ዓይነት ጸጋና ክብር በልጇ ሥልጣን፥ በልጇ ቸርነት ወደ መንግሥተ ሰማያት አሳርገዋታል፤ ‹‹እቴ ሙሽራዬ ከሊባኖስ ከእኔ ጋራ ነዪ፤›› የሚለው ተፈጽሞላታል፡፡ ሥጋዋንም ቅዱሳን ሐዋርያት ለጊዜው ጌቴሴማኒ በተባለ ቦታ አሳርፈውታል፡፡ በሦስተኛው ቀን ግን መላእክት ከዚያ አፍልሰው በገነት በዕፀ ሕይወት ሥር አኑረውታል፡፡ ከመቃብር እስከ ተነሣችበትና ፍጹም ዕርገት እስካገኘችበት እስከ ነሐሴ ፲፮ ቀን ለኹለት መቶ አምስት ቀኖች በዚያው ቆይቷል፡፡ በዕለተ ዕረፍቷ ብዙ ተኣምራት ተደርገዋል፡፡ ለድውያን የፈውስ ጸጋ ታድሏል÷ ስሟን ለሚጠሩ ኹሉ ፍጹም በረከት ተሰጥቷል፡፡ የፈውስ ጸጋ ከደረሳቸው አንዱ ታውፋንያ ወይም ሶፎንያስ የሚባለው አይሁዳዊ ነው፡፡
ታሪኩ እንደሚገልጸው፣ እመቤታችን ካረፈች በኋላ ቅዱሳን ሐዋርያት በኀዘን ላይ እንዳሉ ለጊዜው በኢየሩሳሌም ያልተገኘውና በሀገረ ስብከቱ የነበረው ቅዱስ ቆማስ ከሀገረ ስብከቱ ወደ ኢየሩሳሌም ሲመጣ ቅዱሳን መላእክት ሥጋዋን ወደ ገነት ሲያፈልሱ አይቶና ደርሶ ነገሩንም ከመላእክት ተረድቶ ለወንድሞቹ ለሐዋርያት ነግሯቸው ነበር፡፡
ሐዋርያትም ከእመቤታችን በመለያየታቸው እያዘኑ ምስጢሩን ለማወቅ ይጓጉ ስለነበር ጌታ ተገልጾላቸው፤ ‹‹እናቴን አሳያችኋለሁ፤›› የሚል ተስፋ ሰጥቷቸው ነበር፡፡ በዚህ ተስፋ ላይ ሳሉም ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ፣ ‹‹ከነሐሴ ፩ ቀን ጀምረን በጾም እመቤታችንን እንዲያሳየን ፈጣሪያችንን እንጠይቀው፤›› አላቸው፡፡ እነርሱም ዐሳቡን ተቀብለው ከነሐሴ ፩ ቀን ጀምሮ ኹለት ሱባዔ ከጾሙ በኋላ ነሐሴ ፲፮ ቀን ጌታ መላውን ሐዋርያት ወደ ገነት አውጥቶ በገነት በዕፀ ሕይወት ሥር ከነበረው መቃብር እመቤታችንን ነፍስዋን ከሥጋዋ አዋሕዶ አንሥቶ ትንሣኤዋንና ዕርገትዋን አሳይቶ ለዓለም ይህንኑ እንዲያስተምሩ አዘዛቸው ይላል፡፡
መሠረቱ ግን ቀደም ሲል የገለጥነው በመዝሙር ፻፴፩፥፰ ላይ፤ ‹‹አቤቱ ወደ ዕረፍትህ ተነሥ፤›› የሚለው ነውና እንግዳ ነገር ሊኾን አይችልም፡፡ በዚኹ መሠረት ኢትዮጵያ ይህን ጽሑፍ ካገኘችበት ጊዜ ጀምሮ፣ ‹‹ለሐሴቦን ንጉሥ ልጅ ኹሉ ክብርዋ ነው፤ በወርቀ ዘቦ ልብስ ተሸልማለች፤ በኋላዋም ለንጉሥ ደናግልን ይወስዳሉ፤ ባልንጀሮችዋንም ይወስዱልኻል፡፡ በአባቶች ፈንታ ልጆች ተወለዱልሽ፤ ወንዶች ልጆችሽን በዕቅፋቸው፥ ሴቶች ልጆችሽንም በትከሻቸው ያመጡልሻል፤›› ተብሎ በተነገረው የነቢያት ቃል መሠረት ልጆችም ወላጆችም በመተባበር የእመቤታችንን የፍልሰታ ጾምና በዓል ሲጠብቁ ይኖራሉ፡፡
ከቀደሙ ሰዎች ታሪክ ከእስራኤል መሳፍንት አንዱ ለኾነው የዮፍታሔ ልጅ መታሰቢያ ልጆች ወይም ደናግል በየዓመቱ በዓል ሲያከብሩ እንደነበረ ተነግሯል፡፡ (መጽ. መሳ.፲፩፥፵፡፡) እንዲህ ከኾነ ዘንድ ኢትዮጵያውያት ቆነጃጅትና ሕፃናት፥ ኢትዮጵያውያን ጎልማሶች የእናታችንን፥ የእመቤታችንን የቅድስት ድንግል ማርያምን መታሰቢያ በየዓመቱ ሲያከብሩ የበለጠ ነገር ፈጽመዋል ማለት ነው፡፡
Filstea LeMariam
ጌታ በሕይወተ ሥጋ በዚኽ ዓለም በነበረበት ጊዜ ሽቱ ለቀባችው ሴት ወንጌል በተሰበከበት ኹሉ ያቺ ሴት የሠራችው እንዲነገርላት÷ ወንጌል በተነበበበት ቦታ ኹሉ እንድትታሰብ ጌታ ቃል ሰጥቷል፡፡ (ማቴ. ፳፮ ÷ ፲፫፡፡) እንግዲህ፤ ‹‹መርጫታለኹና አድርባታለኹ፤›› ሲል ለመሰከረላት አምላክን ለወለደች የተስፋችን መዳረሻ÷ ፍጻሜ÷ የድኅነታችን ምክንያት ለኾነችው ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም በቤተ ክርስቲያን ወንጌል በሚነበብበት÷ አምላክን የመውለዷ ምስክርነት በሚሰጥበት ቦታ ኹሉ ልናስባት ልናከብራት ይገባል፡፡ እኛ ስሟን ብናከብር÷ መታሰቢያዋን ብናደርግ እንጠቀምበታለን እንጂ ለእርሷ የምንጨምርላት ክብር የለም፤ ባናደርግም የምናጎድልባት ነገር የለም፡፡ እግዚአብሔር አንድ ጊዜ እናቱ እንድትኾን በመምረጥ ከፍጥረት ኹሉ አልቋታል፤ አክብሯታልና፡፡ ስለዚህም፤ ‹‹ባልንጀሮቿን ላንተ ይወስዱልኻል፡፡›› ‹‹በአባቶችሽ ፈንታ ልጆች ተወለዱልሽ፡፡›› ‹‹ለምድር ኹሉ አለቆች አድርገሽ ትሾሚያቸዋለሽ፡፡›› ‹‹ለዘላለም ስምሽን ይጠራሉ፡፡›› ‹‹ጽዮንን ክበቧት ዕቀፏትም፤ በቤቷ ውስጥም በጸሎት ተነጋገሩ፤ ልባችኁን በረድኤትዋ ላይ አሳርፉ፤ ሀብቷን በረከቷን ትካፈላላችኹ፤›› ይላልና፤ በፍቅሩ ተማርከው እርሷን መስለው በድንግልና እግዚአብሔርን ለማገልገል የቆረጡ ደናግል÷ በጸሎት በምስጋና ስሟን የሚጠሩ÷ በልጇ ቸርነት÷ በእርሷ አማላጅነት የሚታመኑ ምእመናን ኹሉ በረከቷን ይሳተፋሉ፤ ልጆቿ ተብለው ይጠራሉ፡፡ ስለኾነም ኹልጊዜ፤ ‹‹ሰዓሊ ለነ ቅድስት፡፡›› ‹‹ቅድስት ሆይ ለምኝልን፤ አማልጅን፤›› እያልን በጸሎት ልንጠራት ይገባል፡፡ ይልቁንም እኛ ኢትዮጵያውያን በዚኽ ኹኔታ እጅግ በጣም ከፍ ያለ አስተሳሰብና አስተያየት ሊኖረን ያሻል፡፡ ባዕድ ባዕድ ነው፡፡ ሰው ከተባለ የወላጆቹን ክብር የማያስቀድም የለም፤ ለእርሱ የክብሩ መሠረቶች ናቸውና፡፡ አንደበታቸውን የማይገቱ ሰዎች ተላልፈው የወላጆቹን ክብር ቢነኩበት እስከ መሞት ይደርሳል፤ ይህም እንኳ ባይኾን ከዚያ ቀን ጀምሮ የወላጆቹን ክብር ከደፈሩት ሰዎች ጋራ ያለውን አንድነት ያቋርጣል፡፡ ነቢዩ ዳዊት ስለ ኢትዮጵያና ኢትዮጵያውያን በመዝሙር ፹፮/፹፯ በተናገረው ቃል÷ ‹‹ወሕዝበ ኢትዮጵያ እለ ተወልዱ በህየ፤ እምነ ጽዮን ይብል ሰብእ፡፡›› ‹‹በዚያው ከተወለዱት ከኢትዮጵያ ሰዎች ሰው እናታችን ጽዮን ይላል፤›› ብሏል፡፡ እንግዲህ፤ ‹‹ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች፤›› ከሚለው ቃል ጋራ፤ ‹‹ሰው እናታችን ጽዮን ይላል፤›› የሚለው ቃል የኢትዮጵያውያንን ዕድል እንደሚያመለክት አያጠራጥርም፡፡ ኢትዮጵያውያን ክርስቲያኖች ለእመቤታችን የዐሥራት ልጆቿ ናቸው፡፡ እነርሱም ይህን ዐውቀው ክብሯን ጠብቀው ይኖራሉ፡፡
የጾመ ፍልሰታን መታሰቢያ ለመፈጸም ልጆችም ወላጆችም ይተባበራሉ፤ ጾሙ በፍትሕ ነገሥት በአንቀጽ ፲፭ ከተዘረዘሩት አጽዋም አንዱ ነው፡፡ ጾሙ ከፍቅር ጋራ የሚፈጸም ስለሆነ ልጆችም ወላጆችም የሚጾሙት በጉጉት ነው፡፡ ወላጆችም ከባድ ምክንያት ካላጋጠማቸው በስተቀር ከአልጋው ወርደው፣ ከመሬት ላይ ተኝተው ወይም ከቤታቸው ወጥተው በቤተ እግዚአብሔር ዙሪያ ማረፊያ አሰናድተው ከነሐሴ ፩ – ፲፮ ድረስ ውዳሴ ማርያም፣ ቅዳሴ ማርያም በመስማት፣ በምጽዋት፣ ቅዳሴ በማስቀደስ በከፍተኛ ሥነ ሥርዓት ይጾሙታል፡፡
ልጆችም ረኀብ ሳይሰማቸው፣ ውኃ ጥም ሳያሸንፋቸው ከሰባት ዓመት ዕድሜ ጀምሮ ያሉ ወንዶችና ሴቶች ሕፃናት እየጾሙ ይቆርባሉ፤ በመጨረሻም ነሐሴ ፲፮ ቀን ወላጆች በዓሉን በሥነ ሥርዓት ሲያከብሩ ልጆችም በልዩ ሥነ ሥርዓት ያከብሩታል፡፡
‹‹አሸንዳ›› የሚባል ሣር ዓይነት ቅጠል አለ፤ ኹኔታው ቀጭን ቢኾንም ቁመቱ ረዘም ያለ ኾኖ ቅርፁ ፊላ ዓይነት ነው፤ ሲነቅሉት ሥሩ ነጭ ነው፡፡ ዛጎል ይመስላል፡፡ በልዩ አሠራር ሠርተው በቀሚሳቸው ላይ ይታጠቁታል፤ እንደ ዘርፍ ኾኖ ወደ ታች ይወርዳል፤ በሚጫወቱበት ጊዜ ዙሪያውን ሲነሣ ክንፍ ይመስላል፡፡ በዚኽ ዓይነት ሥርዓት በዓሉን ሲያከብሩ ይውላሉ፤ በተለይ በገጠር ላሉ ሴቶች ሕፃናት ቆነጃጅት ልዩ በዓላቸው ነው፡፡
Ashenda Ashendaye
አሸንዳ
ከሚባለው ሣር ዓይነት ቅጠል በልዩ አሠራር ሠርተው የሚታጠቁትና ሲጫወቱ ዙሪያውን የመነሣቱ ኹኔታም መላእክት እመቤታችንን ክንፍ ለክንፍ ገጥመው እያመሰገኑ ማሳረጋቸውን ያሳስባል፡፡ ነቢዩ ኢሳይያስ በትንቢቱ ምዕራፍ ፮ ላይ ባየው ራእይ÷ ሱራፊ መልአክ በኹለት ክንፍ ፊቱን፣ በኹለት ክንፍ እግሩን ሲሸፍን፣ ኹለት ክንፉን በግራ በቀኝ ዘርግቶ ረብቦ ይታያል የሚለውን ያመለክታል፤ በዓሉንም የአሸንድዬ በዓል ይሉታል፡፡ በእውነት፤ ‹‹ደናግልን ለንጉሥ በኋላዋ ይወስዳሉ፤›› ሲል ቅዱስ ዳዊት የተናገረው ቃል ልጆች በእመቤታችን ፍቅር እየተኮተኮቱ አድገው ለእግዚአብሔር ቤተሰብ መኾናቸውን ያሳያል፡፡ በዚህ ሥርዓት ያደጉ ልጆችን እስከ ሕይወታቸው ፍጻሜ ከእመቤታችን ፍቅር የሚለያቸው የለም፡፡

በኢትዮጵያ እመቤታችንን መውደድ በልማድ እንደ ተረት በማይታይ ዓይነት ኹኔታ ተስፋፍቶ የኖረ አይደለም፡፡ ወንድም ሴትም ቢኾኑ እንዳላቸው የእምነት መጠን በእመቤታችን ስም ጸሎት ጸልየው፣ ስእለት ተስለው፣ ምጽዋት አድርገው፣ ዝክርዋን ዘክረው፣ ስምዋን ጠርተው፣ በአማላጅነትዋ ተማፅነው ዐሳባቸው እየተፈጸመላቸው፣ የጎደለው እየሞላላቸው፣ የጠመመው እየተቃናላቸው፣ ድውያን ፈውስ በማግኘት፣ ሠራተኞች ለሥራቸው የተቃና መንገድ በማግኘት፣ መምህራን በሚያስተምሩበት፣ ቅዱሳን ገድላቸውን በሚፈጽሙበት ጊዜና ምክንያት ኹሉ የእመቤታችንን ረድኤት እያገኙ ስለሔዱና ዛሬም ያው ያልተቋረጠ ስለኾነ ነው፡፡
በረድኤት ከሚያገኙት ተስፋ ሌላ በራሳቸውም ኾነ በሌላ ሰው በኩል በራእይ፣ በሕልም፣ በገሃድ እየተገለጸች የምታደርግላቸው ማጽናናት ልባቸውን የፍቅርዋ ምርኮኛ፣ የረድኤትዋ እስረኛ አድርጎት ይኖራል፡፡ ይህም ለአባቶቻችን ብቻ የተደረገ አይደለም፡፡ ስለ እውነት ምስክርነት ሲባል ይህ ለኹላችንም እንኳ የደረሰ ተስፋ መኾኑን ላረጋግጥላችኹ እወዳለኹ፡፡ ስለዚህ ነው ኢትዮጵያውያት ቆነጃጅትና ኢትዮጵያውያን ጎልማሶች ለእመቤታችን በየዓመቱ ከነሐሴ ፩ – ፲፮ ቀን የሚያደርጉትን ጾምና በዓል የበለጠ ያደርገዋል ያልኹት፡፡
በዮሐንስ ራእይ ምዕ. ፲፱ ፥ ፯-፰ ላይ፤ ‹‹የበጉ ሠርግ ደርሷልና ደስ ይበለን፤ ሴቲቱም ተዘጋጅታለች፤ እንድትለብስም ንጹሕ የብርሃን ልብስ ተሰጣት፤ ይኸውም ልብስ የቅዱሳን ክብር ነው፡፡ መጽሐፍ ወደ በጉ ሠርግ የተጠሩ ብፁዓን ናቸው፤ ይህ የእውነት ቃል የእግዚአብሔር ነውና አለኝ፤›› የሚል ተጽፏል፡፡
Aleqa Ayalew Tamiru
አለቃ አያሌው ታምሩ (፲፱፻፲፭ – ፲፱፻፺፱ ዓ.ም.)
ቅዱስ ጳውሎስ ወደ ተሰሎንቄ በላከው መልእክቱ ምዕ. ፬ ፥ ፲፯ ላይ፤ ‹‹ጌታን ለመቀበል በደመና ወደ አየር እንነጠቃለን፤ ከእንግዲህ ወዲህም ከጌታ ጋራ ለዘለዓለም እንኖራለን፤›› በማለት የገለጠው ተስፋ ለቅዱሳን በመታደሉ ዮሐንስ በራእዩ ምዕ.፳ ፥ ፱-፲፪ የገለጠው የሰው ኹሉ ትንሣኤ ከመድረሱ አስቀድሞ ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም የቅድስናን ክብር እንድትጎናጸፍ ልጅዋ እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ ፈቀደ በእናትነትዋ በመንፈስ ቅዱስ መቀደስን በቅድሚያ እንዳገኘች፤ ዛሬም÷ ኋላም ሞቶ ተነሥቶ በዐዲስ ሕይወት ከጌታ ጋራ መኖርን አግኝታለችና ይህን የሚያምን ልብ ሕያውነትዋን፣ በሕይወት መኖርዋን አምኖ፤ ‹‹በእግዚአብሔር ዘንድ ሞገስ ያገኘሽ እናታችን፣ እመቤታችን ወላዲተ አምላክ ቅድስት ድንግል ማርያም ሆይ! ከልጅሽ ለምኚልኝ፤ አማልጂኝ፤ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ መንበር ፊት በምታቀርቢው ጸሎትሽ፣ አማላጅነትሽ አስቢኝ፤›› እያለ ሊጸልይ ይገባዋል፡፡
ምንጭ፡- ወላዲተ አምላክ በኢትዮጵያ፤ ፲፱፻፸፱ ዓ.ም.


2014 ኦገስት 3, እሑድ

አቡነ ጴጥሮስ ሰማዕት


አቡነ ዼጥሮስ ምንም እንኩዋ ለሃገራቸውና ሃይማኖታቸው የከፈሉት ዋጋ ትልቅ ቢሆንም ትውልዱም: መንግስቱም: ራሷ ቤተክርስቲያናችንም ተገቢውን ክብር ሰጥተው እያሰቧቸው አይደለም
ታሪካቸውም ባጭሩ........................
በ1875 ዓ.ም. በሰሜን ሸዋ አገረ ስብከት ሰላሌ አውራጃ ፍቼ ከተማ ተወለዱ። ወላጆቻቸው ዕድሜያቸው ገና በወግ ለትምህርት ሳይደርስ ወደ ደብረ ሊባኖስ ገዳም በመውሰድ ባሕታዊ ተድላ ለተባሉ መምህር አደራ ሰጧቸው። በዚያው ገዳም የንባብ ቤቱንና የዜማውን የትምህርት ደረጃዎች በሚያስገርም ሁኔታ በአጭር ጊዜ አቀላጥፈው በመጨረስ ገና በልጅነት የዕድሜ ደረጃቸው ሦስተኛውን የቅኔ ትምህርት ጀምረው በአጭር ጊዜ ሙሉ ቤት ተቀኙ። ይህንኑ የቅኔ ትምህርት ለማስፋፋት በምዕራብ ጎጃም አገረ ስብከት ወደሚገኘው የቅኔ ትምህርት ማዕከል ዋሸራ ተሻግረው ለመምህርነት የሚያበቃውን ትምህርት ፈጽመው አስመሰከሩ።
ከዚያም ከቅኔው ዐውድማ ጎጃም ወደ ዜማው አዝመራ ጎንደር ተሻገሩ። በዚያም እንደ ቅኔው ሁሉ እስከ ማስመስከር ባይደርሱም የዜማውን ትምህርት በአጥጋቢ ሁኔታ ቀጸሉ። ከጎንደርም በወቅቱ ወሎ ቦሩ ሜዳ ከተባለው ቦታ ላይ ወንበር ዘርግተው የመጻሕፍትን ምሥጢር በየዓይነቱ ሲመግቡ ወደ ነበሩት ስመ ጥሩው መምህር አካለ ወልድ ዘንድ በመሔድ ዋና ዋናዎቹን የመጻሕፍት ትርጓሜ ትምህርቶች ማለትም ብሉያትን፣ ሐዲሳትንና ሊቃውንትን በብቃት አሔዱ።
ከዚህ በኋላ ልክ በ1900 ዓ.ም. እዚያው ወሎ አማራ ሳይንት በተባለው ቦታ ወደሚገኘው ምስካበ ቅዱሳን ገዳም በመሔድ ወንበር ዘረጉ። በዚያው ቦታ ለዘጠኝ ዓመታት ያህል ቅኔንና መጻሕፍትን አስተማሩ።
በዚህ ዓይነት በመማርና በማስተማር ራሳቸውን በእግዚአብሔር ቃል በሚገባ ከጐሰሙ በኋላ በ1909 ዓ.ም. ወደ ደብረ ሊባኖስ ገዳም በመሔድ ሥርዓተ ምንኩስናን ፈጸሙ። ብዙም ሳይቆዩ ማዕረገ ቅስናን ተቀብለው ከወንበሩ አገልግሎት ጋር የቤተ መቅደሱን ተልእኮም ደርበው ያዙ።
በ1910 ዓ.ም. መምህር ኃይለ ማርያም ተብለው በወላይታ ሶዶ በሚገኘው ደብረ መንክራት ምሁር ኢየሱስ ገዳም ተሾሙ። በ1916 ዓ.ም. እንደገና በዝዋይ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም በመምህርነት ተሾሙ። በ1919 ዓ.ም. ወደ አዲስ አበባ በመምጣት የመንበረ መንግሥት ቅዱስ ማርቆስ መምህርና በቤተ መንግሥት የግርማዊ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ አበ ንስሐ ሆኑ።
የግብፅ ቤተ ክርስቲያን ከአንድ ሺ ስድስት መቶ ዓመታት በኋላ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በዕውቀት መንፈሳዊ ከእርሷ ተወልደው በእቅፏ ውስጥ ባደጉ ኢትዮጵያውያን ጳጳሳት እንድትመራ ፈቃዷን ስትገልጽ ከተመረጡት አባቶች አንዱ በመሆን ግንቦት 18 ቀን 1921 ዓ.ም. በእስክንድርያው መንበረ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን ማዕረገ ጵጵስናን ተቀበሉ። ከዓመት በኋላም “አቡነ ጴጥሮስ ጳጳስ ዘምሥራቅ ኢትዮጵያ ተላዌ አሠሩ ለአቡነ ኢየሱስ ሞዓ” ተብለው በያኔው መንዝና ወሎ አገረ ስብከት ተሾሙ።
ሐምሌ 22 ቀን 1928 ስምንት ወታደሮች በስተጀርባቸው ሃያ እርምጃ ርቀው ተንበርክከው በተንጠቀቅ ቆሙ። ወዲያው አዛዡ «ተኩስ» በማለት ትእዛዝ ሲሰጥ ስምንቱም ተኩሰው መቷቸው። ግን በስምንት ጥይት ሳይሞቱ ቀሩ። መሞታቸውንና አለመሞታቸውን ለማረጋገጥ ዶክተር ተጠራ። ዶክተሩም እንዳልሞቱ አረጋገጠ። ከዚያም ሌላ ወታደር በሦስት የሽጉጥ ጥይት ራስ ቅላቸውን መትቶ ገደላቸው።
« እኔ ግን ኢትዮጵየዊ ነኝ፡፡ ሓላፊነትም ያለብኝ የቤተክርስቲያን አባት ነኝ፡፡ ስለዚህ ስለ ሀገሬና ስለ ቤተ ክርስቲያኔ እቆረቆራለሁ፡፡. . . እኔን ለመግደል እንደወሰናችሁ አውቃለሁ፡፡ ስለዚህ በእኔ ላይ የፈለጋችሁትን አድርጉ፡፡ ግን ተከታዮቼን አትንኩ» ሰማዕተ ጽድቅ በሆነ ደማቸው አተሙ፡፡ አኩሪ በሆነ አባታዊ ሓላፊነታቸው ለአገር፣ ለቤተክርስቲያን፣ ለወገን ሁሉ አለኝታነታቸው አረጋግጠው ሐምሌ 22 ቀን 1928 ዓ.ም. በሰማዕትነት አለፉ፡፡
"ብፁዕነታቸው በፍርድ ችሎት ላይ እንዳሉ ሕዝቡ ሁሉ ስለእርሳቸው እያዘነ ሳለ መስቀላቸውን አውጥተው እየጸለዩ ሕዝቡን ባረኩ። ወዲያው የሞታቸው ሰዓት መድረሱን ዐውቀው ሰዓታቸውን ከኪሳቸው አውጥተው ተመለከቱ። በዚህ ጊዜ ሁሉ ምንም ፍርሃት አይታይባቸውም ነበር። የሞታቸውን ፍርድ ያነብ የነበረው ኢጣልያዊ ዳኛ ግን ይንቀጠቀጥ ነበር። ታላቅ ፍርሃትም በፊቱ ይታይ ነበር።"
የኢጣሊያ ፋሺስት በ1928 ዓ.ም. በኢትዮጵያ ላይ የግፍ ጦርነትን ባነሣ ጊዜ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ከጦር ስፍራ ለመለየት ስላልሆነላቸው፣ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴን ተከትለው ወደ ሰሜን ጦር ግንባር ዘምተዋል፡፡ ፋሺስቱ በማይጨው የመርዝ ጦርነት ከማድረጉ የተነሣ፣ የኢትዮጵያ ሠራዊት ሲበታተንም ከንጉሠ ነገሥቱ ጋር የተመለሱት አቡነ ጴጥሮስ ወደ ደብረ ሊባኖስ ሄደው ለአገርና ለነፃነት መሞት ቅዱስ ተግባር መሆኑን ለሥላሴ አርበኞች በመስበክም ይታወቃሉ፡፡
አርበኞች አዲስ አበባን በሁለት አቅጣጫዎች ከሰሜናዊ ምዕራብ እና በደቡባዊ ምሥራቅ አቅጣጫ ለመቆጣጠር ውጊያ በከፈቱበት ጊዜ የተማረኩት አቡነ ጴጥሮስ፣ ለፋሺሽት እንዲገዙ የኢጣሊያ መንግሥት ገዢነትንም አምነው አሜን ብለው እንዲቀበሉ ግፊት ቢያደርጉባቸውም፤ እምቢኝ ለሀገሬና ለሃይማኖቴ ብለው ለሰማዕትነት ያበቃቸውን የሞት ጽዋ ተቀብለዋል፡፡
ቅዱስ ጳውሎስ ደቀ መዝሙሩ የሆነው ጢሞቴዎስን የተሰጠውን አደራ በመጠበቅ ሓላፊነቱንና ግዴታውን መወጣት እንደ ሚገባው ሲገልጽ «እቀብ ማህጸንተከ፤ አደራህን ጠብቅ» በማለት ነው፡፡ 1ኛጢሞ.6 .2፡፡ ጢሞቴዎስ በመምህሩ የተጣለበትን አደራ ለመወጣት የዚህ ዓለም ፈቃድ ሳያሸንፈው ተወጥቷል፡፡ የዓላውያን ነገሥታት ማዋከብ፣ ድብደባ አደራውን እንዳይወጣ አላደረገውም፡፡ የአቡነ ጴጥሮስ የሰማዕትነትም ጉዞ መነሻውም መድረሻውም የእነዚህ አባቶች አርአያ ፍኖት ነው፡፡
ለሀገራቸውና ለወገናቸው እስከ መጨረሻዋ ሰዓት ድረስ እውነቱን ከሐሰት በመለየት ለሕዝባቸው የሰጡት ምስክርነት የተጣለባቸውን አደራ ከመወጣት ነው፡፡ አለቃ ተጠምቀ የተባሉ ቅድስናን ከሊቅነት ጋራ አስተባብረው የያዙ የቅኔ መምህራቸው አንድ ቀን ብፁዕነታቸውን ጠርተው የሚከተለውን የአደራ ቃል ያስተላልፋሉ፡፡ «ኀይለማርያም አንተ ወደፊት ጳጳስ ትሆናለህ፤ በወቅቱም አረመኔ በዚህች ሀገር ይሠለጥናል፡፡ ታዲያ ያኔ አንተ ለነፍስህ ሳትሳቀቅ በሰማዕትነት እለፍ፤ ሰማዕትነት ክፍልህ ነው፡፡ አደራ፡፡» /መርሻ አለኸኝ /ዲያቆን/፣ 1986 ዓ.ም፣ ዜና ጳጳሳት ኢትዮጵያውያን፣ ገጽ.80/
ሐዋርያው ቅዱስ ጢሞቴዎስ የመምህሩን የአደራ ቃል በመያዝ እስከ መጨረሻው እንደጸናው ብፁዕነታቸውም የመምህራቸውን የአደራ ቃል በሰማዕትነት አትመው ጠበቁ፡፡ አንዲትም ቀንና ሰዓት ከሞት ሳይሸሹ እና ሳይደበቁ ለአገራቸው ፣ለቤተ ክርስቲያናቸው እና ለሕዝባቸው ሲሉ ሞትን ተጋፈጡ፡፡ የሰማዕትነትን ጽዋ ተጎነጩ፡፡ የዚህ ምንጩ አደራ ነው፡፡ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ቤተክርስቲያን በአደራ የሰጠቻቸውን ሓላፊነት ለመወጣት ሕዝበ ክርስቲያኑን በጸሎታቸው እየደገፉ፣ በትምህርታቸው እያበረቱ አስተዳድረዋል፡፡
ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ሕዝብ ቀስቅሰዋል፤ ራስዎም አምጸዋል፣ ሌሎችንም እንዲያምጹ አድርገዋል በሚል የወንጀል ክስ ፍርድ ቤት ቀረቡ፡፡ ችሎቱ ተሰይሞ ሲቀርቡ ዳኛው «ካህናቱም ሆኑ የቤተክህነት ባለሥልጣናት ጳጳሱ አቡነ ቄርሎስም የጣሊያንን መንግሥት ገዥነት አምነው አሜን ብለው ሲቀበሉ እርስዎ ለምን ዐመፁ) ለምን ብቻዎን አፈንጋጭ ሆኑ)» ሲል ጠየቃቸው፡፡ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ በቆራጥነት «አቡነ ቄርሎስ ግብጻዊ ናቸው፤ ስለ ኢትዮጵያና ስለ ኢትዮጵያውያን የሚገዳቸው ነገር የለም፡፡ እኔ ግን ኢትዮጵየዊ ነኝ፡፡ ሓላፊነትም ያለብኝ የቤተክርስቲያን አባት ነኝ፡፡ ስለዚህ ስለ ሀገሬና ስለ ቤተ ክርስቲያኔ እቆረቆራለሁ፡፡. . . እኔን ለመግደል እንደወሰናችሁ አውቃለሁ፡፡ ስለዚህ በእኔ ላይ የፈለጋችሁትን አድርጉ፡፡ ግን ተከታዮቼን አትንኩ» በማለት ሕያው በሆነ ቃላቸው መለሱ፡፡ ሰማዕተ ጽድቅ በሆነ ደማቸው አተሙ፡፡ አኩሪ በሆነ አባታዊ ሓላፊነታቸው ለአገር፣ ለቤተክርስቲያን፣ ለወገን ሁሉ አለኝታነታቸው አረጋግጠው በሰማዕትነት አለፉ፡፡ / መርሻ አለኸኝ/ዲያቆን/፣ 1996ዓ.ም፣ዜና ጳጳሳት ኢትዮጵያውያን፣ገጽ.77/
ፋሺስት ጣሊያን የእርሱ አቋም የራሳቸው አቋም፤ የእርሱ የጭቆና አገዛዝ የእርሳቸው አገዛዝ፣ የእርሱ ተራ ፕሮፓጋንዳ የእርሳቸው እውነት አድርገው እንዲቀበሉ መደለያ /ገንዘብ፣ መኪና በዘመኑ ዘመናዊ የሚባል ቤት/ ልስጦት ሳይላቸው ቀርቶ ነውን) ለሕዝባቸው፣ ለሀገራቸውና ለቤተክርስቲያናቸው ሰማዕት የሆኑት) እርሳቸው ግን መንኖ ጥሪትን ገንዘብ ያደረጉ አባት በመሆናቸው ሌሎቹ የቤተ ክህነቱ ባለሥልጣናት ለፋሺስት ጣሊያን ሲያድሩ መደለያው ሳያንበረክካቸው በመንፈሳዊ ወኔ ሰማዕት ሆነዋል፡፡
የፋሺስት ኢጣሊያ ወራሪ ኃይል በሐምሌ 22 ቀን 1928 ዓ.ም. ሰማዕቱን ገድሎ አስክሬናቸው አደባባይ ላይ ጥሎ ከዋለ በኋላ፣ ቀብራቸው በምስጢር መፈጸሙ መዛግብት እንደሚያስረዱ እና የእኚህን ታላቅ አባት ቀብር በምስጢር የተፈጸመበት ቦታ ለማግኘት የተለያዩ ምሁራን በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ ያሉ የታሪክ ሰነዶችን ሲመረምሩ ቢቆዩም፣ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ “ከአዲስ አበባ በስተደቡብ በምስጢር ቀበሯቸው” ከሚል ጠቅላላ ፍንጭ ያለፈ ምንም ዓይነት የተረጋገጠ ማስረጃ ሳይገኝ ቆይቶ ነበር ፡፡
ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ግን ከአዲስ አበባ ከተማ መስፋፋት ጋር ተያይዞ “ለቡ” ተብሎ በሚታወቀው አካባቢ የሰፈሩ ምዕመናን በአካባቢው ተወልደው ካደጉ አረጋውያን ጋር ባደረጉት ማኅበራዊ ግንኙነት ሰማዕቱ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ፋሽስቶች በመኖርያነትና በእስር ቤትነት ይጠቀሙበት በነበረው “ሙኒሳ ጉብታ” ላይ መቀበራቸውን ከወላጆቻቸው ሲሰሙ እንዳደጉ በእርግጠኝነት አስረድተዋቸዋል፡፡
በዚህም በፋሺስት ኢጣሊያ ከ76 ዓመት በፊት ሰማዕት የሆኑት አቡነ ጴጥሮስ የተቀበሩበት ቦታ በአዲስ አበባ በስተደቡብ በለቡ አካባቢ መገኘቱን የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን አረጋግጣለች፡፡
« እኔ ግን ኢትዮጵየዊ ነኝ፡፡ ሓላፊነትም ያለብኝ የቤተክርስቲያን አባት ነኝ፡፡ ስለዚህ ስለ ሀገሬና ስለ ቤተ ክርስቲያኔ እቆረቆራለሁ፡፡. . . እኔን ለመግደል እንደወሰናችሁ አውቃለሁ፡፡ ስለዚህ በእኔ ላይ የፈለጋችሁትን አድርጉ፡፡ ግን ተከታዮቼን አትንኩ» ሰማዕተ ጽድቅ በሆነ ደማቸው አተሙ፡፡ አኩሪ በሆነ አባታዊ ሓላፊነታቸው ለአገር፣ ለቤተክርስቲያን፣ ለወገን ሁሉ አለኝታነታቸው አረጋግጠው ሐምሌ 22 ቀን 1928 ዓ.ም. በሰማዕትነት አለፉ፡፡
ከሰማዕቱ በረከት ረድኤት ምልጃ አምላክ ያሳትፈን::
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ::

አቡነ ጴጥሮስ ሰማዕት


አቡነ ዼጥሮስ ምንም እንኩዋ ለሃገራቸውና ሃይማኖታቸው የከፈሉት ዋጋ ትልቅ ቢሆንም ትውልዱም: መንግስቱም: ራሷ ቤተክርስቲያናችንም ተገቢውን ክብር ሰጥተው እያሰቧቸው አይደለም
ታሪካቸውም ባጭሩ........................
በ1875 ዓ.ም. በሰሜን ሸዋ አገረ ስብከት ሰላሌ አውራጃ ፍቼ ከተማ ተወለዱ። ወላጆቻቸው ዕድሜያቸው ገና በወግ ለትምህርት ሳይደርስ ወደ ደብረ ሊባኖስ ገዳም በመውሰድ ባሕታዊ ተድላ ለተባሉ መምህር አደራ ሰጧቸው። በዚያው ገዳም የንባብ ቤቱንና የዜማውን የትምህርት ደረጃዎች በሚያስገርም ሁኔታ በአጭር ጊዜ አቀላጥፈው በመጨረስ ገና በልጅነት የዕድሜ ደረጃቸው ሦስተኛውን የቅኔ ትምህርት ጀምረው በአጭር ጊዜ ሙሉ ቤት ተቀኙ። ይህንኑ የቅኔ ትምህርት ለማስፋፋት በምዕራብ ጎጃም አገረ ስብከት ወደሚገኘው የቅኔ ትምህርት ማዕከል ዋሸራ ተሻግረው ለመምህርነት የሚያበቃውን ትምህርት ፈጽመው አስመሰከሩ።
ከዚያም ከቅኔው ዐውድማ ጎጃም ወደ ዜማው አዝመራ ጎንደር ተሻገሩ። በዚያም እንደ ቅኔው ሁሉ እስከ ማስመስከር ባይደርሱም የዜማውን ትምህርት በአጥጋቢ ሁኔታ ቀጸሉ። ከጎንደርም በወቅቱ ወሎ ቦሩ ሜዳ ከተባለው ቦታ ላይ ወንበር ዘርግተው የመጻሕፍትን ምሥጢር በየዓይነቱ ሲመግቡ ወደ ነበሩት ስመ ጥሩው መምህር አካለ ወልድ ዘንድ በመሔድ ዋና ዋናዎቹን የመጻሕፍት ትርጓሜ ትምህርቶች ማለትም ብሉያትን፣ ሐዲሳትንና ሊቃውንትን በብቃት አሔዱ።
ከዚህ በኋላ ልክ በ1900 ዓ.ም. እዚያው ወሎ አማራ ሳይንት በተባለው ቦታ ወደሚገኘው ምስካበ ቅዱሳን ገዳም በመሔድ ወንበር ዘረጉ። በዚያው ቦታ ለዘጠኝ ዓመታት ያህል ቅኔንና መጻሕፍትን አስተማሩ።
በዚህ ዓይነት በመማርና በማስተማር ራሳቸውን በእግዚአብሔር ቃል በሚገባ ከጐሰሙ በኋላ በ1909 ዓ.ም. ወደ ደብረ ሊባኖስ ገዳም በመሔድ ሥርዓተ ምንኩስናን ፈጸሙ። ብዙም ሳይቆዩ ማዕረገ ቅስናን ተቀብለው ከወንበሩ አገልግሎት ጋር የቤተ መቅደሱን ተልእኮም ደርበው ያዙ።
በ1910 ዓ.ም. መምህር ኃይለ ማርያም ተብለው በወላይታ ሶዶ በሚገኘው ደብረ መንክራት ምሁር ኢየሱስ ገዳም ተሾሙ። በ1916 ዓ.ም. እንደገና በዝዋይ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም በመምህርነት ተሾሙ። በ1919 ዓ.ም. ወደ አዲስ አበባ በመምጣት የመንበረ መንግሥት ቅዱስ ማርቆስ መምህርና በቤተ መንግሥት የግርማዊ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ አበ ንስሐ ሆኑ።
የግብፅ ቤተ ክርስቲያን ከአንድ ሺ ስድስት መቶ ዓመታት በኋላ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በዕውቀት መንፈሳዊ ከእርሷ ተወልደው በእቅፏ ውስጥ ባደጉ ኢትዮጵያውያን ጳጳሳት እንድትመራ ፈቃዷን ስትገልጽ ከተመረጡት አባቶች አንዱ በመሆን ግንቦት 18 ቀን 1921 ዓ.ም. በእስክንድርያው መንበረ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን ማዕረገ ጵጵስናን ተቀበሉ። ከዓመት በኋላም “አቡነ ጴጥሮስ ጳጳስ ዘምሥራቅ ኢትዮጵያ ተላዌ አሠሩ ለአቡነ ኢየሱስ ሞዓ” ተብለው በያኔው መንዝና ወሎ አገረ ስብከት ተሾሙ።
ሐምሌ 22 ቀን 1928 ስምንት ወታደሮች በስተጀርባቸው ሃያ እርምጃ ርቀው ተንበርክከው በተንጠቀቅ ቆሙ። ወዲያው አዛዡ «ተኩስ» በማለት ትእዛዝ ሲሰጥ ስምንቱም ተኩሰው መቷቸው። ግን በስምንት ጥይት ሳይሞቱ ቀሩ። መሞታቸውንና አለመሞታቸውን ለማረጋገጥ ዶክተር ተጠራ። ዶክተሩም እንዳልሞቱ አረጋገጠ። ከዚያም ሌላ ወታደር በሦስት የሽጉጥ ጥይት ራስ ቅላቸውን መትቶ ገደላቸው።
« እኔ ግን ኢትዮጵየዊ ነኝ፡፡ ሓላፊነትም ያለብኝ የቤተክርስቲያን አባት ነኝ፡፡ ስለዚህ ስለ ሀገሬና ስለ ቤተ ክርስቲያኔ እቆረቆራለሁ፡፡. . . እኔን ለመግደል እንደወሰናችሁ አውቃለሁ፡፡ ስለዚህ በእኔ ላይ የፈለጋችሁትን አድርጉ፡፡ ግን ተከታዮቼን አትንኩ» ሰማዕተ ጽድቅ በሆነ ደማቸው አተሙ፡፡ አኩሪ በሆነ አባታዊ ሓላፊነታቸው ለአገር፣ ለቤተክርስቲያን፣ ለወገን ሁሉ አለኝታነታቸው አረጋግጠው ሐምሌ 22 ቀን 1928 ዓ.ም. በሰማዕትነት አለፉ፡፡
"ብፁዕነታቸው በፍርድ ችሎት ላይ እንዳሉ ሕዝቡ ሁሉ ስለእርሳቸው እያዘነ ሳለ መስቀላቸውን አውጥተው እየጸለዩ ሕዝቡን ባረኩ። ወዲያው የሞታቸው ሰዓት መድረሱን ዐውቀው ሰዓታቸውን ከኪሳቸው አውጥተው ተመለከቱ። በዚህ ጊዜ ሁሉ ምንም ፍርሃት አይታይባቸውም ነበር። የሞታቸውን ፍርድ ያነብ የነበረው ኢጣልያዊ ዳኛ ግን ይንቀጠቀጥ ነበር። ታላቅ ፍርሃትም በፊቱ ይታይ ነበር።"
የኢጣሊያ ፋሺስት በ1928 ዓ.ም. በኢትዮጵያ ላይ የግፍ ጦርነትን ባነሣ ጊዜ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ከጦር ስፍራ ለመለየት ስላልሆነላቸው፣ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴን ተከትለው ወደ ሰሜን ጦር ግንባር ዘምተዋል፡፡ ፋሺስቱ በማይጨው የመርዝ ጦርነት ከማድረጉ የተነሣ፣ የኢትዮጵያ ሠራዊት ሲበታተንም ከንጉሠ ነገሥቱ ጋር የተመለሱት አቡነ ጴጥሮስ ወደ ደብረ ሊባኖስ ሄደው ለአገርና ለነፃነት መሞት ቅዱስ ተግባር መሆኑን ለሥላሴ አርበኞች በመስበክም ይታወቃሉ፡፡
አርበኞች አዲስ አበባን በሁለት አቅጣጫዎች ከሰሜናዊ ምዕራብ እና በደቡባዊ ምሥራቅ አቅጣጫ ለመቆጣጠር ውጊያ በከፈቱበት ጊዜ የተማረኩት አቡነ ጴጥሮስ፣ ለፋሺሽት እንዲገዙ የኢጣሊያ መንግሥት ገዢነትንም አምነው አሜን ብለው እንዲቀበሉ ግፊት ቢያደርጉባቸውም፤ እምቢኝ ለሀገሬና ለሃይማኖቴ ብለው ለሰማዕትነት ያበቃቸውን የሞት ጽዋ ተቀብለዋል፡፡
ቅዱስ ጳውሎስ ደቀ መዝሙሩ የሆነው ጢሞቴዎስን የተሰጠውን አደራ በመጠበቅ ሓላፊነቱንና ግዴታውን መወጣት እንደ ሚገባው ሲገልጽ «እቀብ ማህጸንተከ፤ አደራህን ጠብቅ» በማለት ነው፡፡ 1ኛጢሞ.6 .2፡፡ ጢሞቴዎስ በመምህሩ የተጣለበትን አደራ ለመወጣት የዚህ ዓለም ፈቃድ ሳያሸንፈው ተወጥቷል፡፡ የዓላውያን ነገሥታት ማዋከብ፣ ድብደባ አደራውን እንዳይወጣ አላደረገውም፡፡ የአቡነ ጴጥሮስ የሰማዕትነትም ጉዞ መነሻውም መድረሻውም የእነዚህ አባቶች አርአያ ፍኖት ነው፡፡
ለሀገራቸውና ለወገናቸው እስከ መጨረሻዋ ሰዓት ድረስ እውነቱን ከሐሰት በመለየት ለሕዝባቸው የሰጡት ምስክርነት የተጣለባቸውን አደራ ከመወጣት ነው፡፡ አለቃ ተጠምቀ የተባሉ ቅድስናን ከሊቅነት ጋራ አስተባብረው የያዙ የቅኔ መምህራቸው አንድ ቀን ብፁዕነታቸውን ጠርተው የሚከተለውን የአደራ ቃል ያስተላልፋሉ፡፡ «ኀይለማርያም አንተ ወደፊት ጳጳስ ትሆናለህ፤ በወቅቱም አረመኔ በዚህች ሀገር ይሠለጥናል፡፡ ታዲያ ያኔ አንተ ለነፍስህ ሳትሳቀቅ በሰማዕትነት እለፍ፤ ሰማዕትነት ክፍልህ ነው፡፡ አደራ፡፡» /መርሻ አለኸኝ /ዲያቆን/፣ 1986 ዓ.ም፣ ዜና ጳጳሳት ኢትዮጵያውያን፣ ገጽ.80/
ሐዋርያው ቅዱስ ጢሞቴዎስ የመምህሩን የአደራ ቃል በመያዝ እስከ መጨረሻው እንደጸናው ብፁዕነታቸውም የመምህራቸውን የአደራ ቃል በሰማዕትነት አትመው ጠበቁ፡፡ አንዲትም ቀንና ሰዓት ከሞት ሳይሸሹ እና ሳይደበቁ ለአገራቸው ፣ለቤተ ክርስቲያናቸው እና ለሕዝባቸው ሲሉ ሞትን ተጋፈጡ፡፡ የሰማዕትነትን ጽዋ ተጎነጩ፡፡ የዚህ ምንጩ አደራ ነው፡፡ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ቤተክርስቲያን በአደራ የሰጠቻቸውን ሓላፊነት ለመወጣት ሕዝበ ክርስቲያኑን በጸሎታቸው እየደገፉ፣ በትምህርታቸው እያበረቱ አስተዳድረዋል፡፡
ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ሕዝብ ቀስቅሰዋል፤ ራስዎም አምጸዋል፣ ሌሎችንም እንዲያምጹ አድርገዋል በሚል የወንጀል ክስ ፍርድ ቤት ቀረቡ፡፡ ችሎቱ ተሰይሞ ሲቀርቡ ዳኛው «ካህናቱም ሆኑ የቤተክህነት ባለሥልጣናት ጳጳሱ አቡነ ቄርሎስም የጣሊያንን መንግሥት ገዥነት አምነው አሜን ብለው ሲቀበሉ እርስዎ ለምን ዐመፁ) ለምን ብቻዎን አፈንጋጭ ሆኑ)» ሲል ጠየቃቸው፡፡ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ በቆራጥነት «አቡነ ቄርሎስ ግብጻዊ ናቸው፤ ስለ ኢትዮጵያና ስለ ኢትዮጵያውያን የሚገዳቸው ነገር የለም፡፡ እኔ ግን ኢትዮጵየዊ ነኝ፡፡ ሓላፊነትም ያለብኝ የቤተክርስቲያን አባት ነኝ፡፡ ስለዚህ ስለ ሀገሬና ስለ ቤተ ክርስቲያኔ እቆረቆራለሁ፡፡. . . እኔን ለመግደል እንደወሰናችሁ አውቃለሁ፡፡ ስለዚህ በእኔ ላይ የፈለጋችሁትን አድርጉ፡፡ ግን ተከታዮቼን አትንኩ» በማለት ሕያው በሆነ ቃላቸው መለሱ፡፡ ሰማዕተ ጽድቅ በሆነ ደማቸው አተሙ፡፡ አኩሪ በሆነ አባታዊ ሓላፊነታቸው ለአገር፣ ለቤተክርስቲያን፣ ለወገን ሁሉ አለኝታነታቸው አረጋግጠው በሰማዕትነት አለፉ፡፡ / መርሻ አለኸኝ/ዲያቆን/፣ 1996ዓ.ም፣ዜና ጳጳሳት ኢትዮጵያውያን፣ገጽ.77/
ፋሺስት ጣሊያን የእርሱ አቋም የራሳቸው አቋም፤ የእርሱ የጭቆና አገዛዝ የእርሳቸው አገዛዝ፣ የእርሱ ተራ ፕሮፓጋንዳ የእርሳቸው እውነት አድርገው እንዲቀበሉ መደለያ /ገንዘብ፣ መኪና በዘመኑ ዘመናዊ የሚባል ቤት/ ልስጦት ሳይላቸው ቀርቶ ነውን) ለሕዝባቸው፣ ለሀገራቸውና ለቤተክርስቲያናቸው ሰማዕት የሆኑት) እርሳቸው ግን መንኖ ጥሪትን ገንዘብ ያደረጉ አባት በመሆናቸው ሌሎቹ የቤተ ክህነቱ ባለሥልጣናት ለፋሺስት ጣሊያን ሲያድሩ መደለያው ሳያንበረክካቸው በመንፈሳዊ ወኔ ሰማዕት ሆነዋል፡፡
የፋሺስት ኢጣሊያ ወራሪ ኃይል በሐምሌ 22 ቀን 1928 ዓ.ም. ሰማዕቱን ገድሎ አስክሬናቸው አደባባይ ላይ ጥሎ ከዋለ በኋላ፣ ቀብራቸው በምስጢር መፈጸሙ መዛግብት እንደሚያስረዱ እና የእኚህን ታላቅ አባት ቀብር በምስጢር የተፈጸመበት ቦታ ለማግኘት የተለያዩ ምሁራን በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ ያሉ የታሪክ ሰነዶችን ሲመረምሩ ቢቆዩም፣ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ “ከአዲስ አበባ በስተደቡብ በምስጢር ቀበሯቸው” ከሚል ጠቅላላ ፍንጭ ያለፈ ምንም ዓይነት የተረጋገጠ ማስረጃ ሳይገኝ ቆይቶ ነበር ፡፡
ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ግን ከአዲስ አበባ ከተማ መስፋፋት ጋር ተያይዞ “ለቡ” ተብሎ በሚታወቀው አካባቢ የሰፈሩ ምዕመናን በአካባቢው ተወልደው ካደጉ አረጋውያን ጋር ባደረጉት ማኅበራዊ ግንኙነት ሰማዕቱ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ፋሽስቶች በመኖርያነትና በእስር ቤትነት ይጠቀሙበት በነበረው “ሙኒሳ ጉብታ” ላይ መቀበራቸውን ከወላጆቻቸው ሲሰሙ እንዳደጉ በእርግጠኝነት አስረድተዋቸዋል፡፡
በዚህም በፋሺስት ኢጣሊያ ከ76 ዓመት በፊት ሰማዕት የሆኑት አቡነ ጴጥሮስ የተቀበሩበት ቦታ በአዲስ አበባ በስተደቡብ በለቡ አካባቢ መገኘቱን የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን አረጋግጣለች፡፡
« እኔ ግን ኢትዮጵየዊ ነኝ፡፡ ሓላፊነትም ያለብኝ የቤተክርስቲያን አባት ነኝ፡፡ ስለዚህ ስለ ሀገሬና ስለ ቤተ ክርስቲያኔ እቆረቆራለሁ፡፡. . . እኔን ለመግደል እንደወሰናችሁ አውቃለሁ፡፡ ስለዚህ በእኔ ላይ የፈለጋችሁትን አድርጉ፡፡ ግን ተከታዮቼን አትንኩ» ሰማዕተ ጽድቅ በሆነ ደማቸው አተሙ፡፡ አኩሪ በሆነ አባታዊ ሓላፊነታቸው ለአገር፣ ለቤተክርስቲያን፣ ለወገን ሁሉ አለኝታነታቸው አረጋግጠው ሐምሌ 22 ቀን 1928 ዓ.ም. በሰማዕትነት አለፉ፡፡
ከሰማዕቱ በረከት ረድኤት ምልጃ አምላክ ያሳትፈን::
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ::

2014 ጁላይ 24, ሐሙስ

ፈቃደ እግዚአብሔርን ለማወቅ ምን ማድረግ ያስፈልጋል?




ባለፈው ጽሁፋችን ፈቃደ እግዚአብሔርን እንዳናውቅ ያደረጉንን ነገሮች ምን ምን እንደሆኑ ለማየት ሞክረናል ከዚህ ቀጥለን ደግሞ ፈቃደ እግዚአብሔርን ማወቅ እንድንችል ምን ማድረግ እንዳለብን እንመለከታለን፡፡
1.   በሃይማኖት  ትምህርት መብሰል
የሰው ልጅ በተፈጥሮ የተሰጠውን የማሰብ የማገናዘብ ፀጋውን በእውቀት የማዳበር  የማስፋፋት የማጣጣም ሓላፊነት አለበት  ይህ ካልሆነ በሁሉ ነገር ጥሬ ይሆንና  በነፍሱ እና በሥጋውም ሲቸገር ይኖራል እንኳዋን ከእግዚአብሔር ጋር ይቅርና ከሰው ጋርም መኖር ይቸገራል፡፡ በሃይማኖት ትምህርት የበሰለ ሰው ደግሞ እግዚአብሔር የሚወደውን  ሁሉ ለመረዳት አቅም ይኖረዋል፡፡ የእግዚአብሔር ፈቃድ እንዴት እንደሚገለጥ  መረዳት ይችላል ::  ጥበብ ወደ ልብህ ትገባለችና ዕውቀትም ነፍስህን ደስ ታሰኛለች  ምሳ 2፤ 10  የብዙ ሰው ችግር  ሆኖ የሚታየው በአብዛኛው የሃይማኖት ትምህርት እውቀት ማጣት ነው ፡፡ እንደሚታወቀው  ሕዝበ ክርስቲያኑ መሠረታዊ  የሃይማኖት ትምህርትን  እንደ አስኮላው ትምህርት በየአጥቢያቸው መርሃግብር  ወጥቶ መማር እስካሁን አልተለመደም ይሁን እንጂ አሁን ዘመኑ የግድ ይህንን ማድረግ እንደሚገባ  ያስገድዳል፡፡ ሁሉም ሰው ስለሃማኖቱ ጠንቅቆ ማውቅ ሲችል ነው እግዚብሔር የሚወደውን ማውቅና ማሳወቅ የሚችለው ይህ ካልሆነ ግን  ወደ ስህተት መንገድ ተያይዞ መጥፋቱ አይቀሬ ነው፡፡ለዚህ ነው ነቢዩ ፤ ሕዝቤ እውቀት ከማጣቱ የተነሳ ጠፍቶአልአንተም እውቀትን ጠልተሃልና…. በማለት የተናገረው፡፡ ሆሴ 4፤ 6
ይህ ዘመናችን እጅግ በጣም የተወሳሰበ ከመሆኑ የተነሳ ተአምራት ሚመስሉ ግን ያልሆኑ እውነት  የሚመስሉ ሐሰት የሆኑ  በሃይማኖት ትምህርት በስለናል አውቀናል የሚሉትን እንኳን ሳይቀር የማረኩ ነገሮች የሚታዩበት ዘመን ነው  እንዲህ ያለውን ዘመን ደግሞ በሃማኖት ትምህርት የበሰለ ሰው ካልሆነ በስተቀር ሊቋቋመው አይችልም :: ሥር ሰዳችሁ በእርሱ ታነጹ  እንደተማራችሁም በሃይማኖት ጽኑ፡፡ ተብሎ እንደተጻፋ ቆላስይስ 2፤7
2.ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንን ማማከር
    ሌላው እጅግ በጣም ሊተኮርበት የሚገባ  ነገር ግን እስካሁን በአብዛኛው ኢየተዘነጋ የመጣው ነገር  በቤተ ክርስቲያን  የሚታወቁ  ሊቃውንትን የማማከር ተግባር ሊተኮርበት ይገባል፡፡ ምክንያቱም  ብዙ ጊዜ ምእመናን መንፈሳዊ ሕይወታቸውን በዘፈቀደ ሲመሩት ይስተዋላል ወደ ተለያዩ ገዳማትም ሲገጓዙ ከጉዞው በፊት  ማማከርን መልመድ ያስፈልጋል፡፡ ጻድቁ ኢዮብ ፤ የቀደመውን ትውልድ ጠይቅ አባቶቻቸውም ለመረመሩት ነገር ትጋ ፡፡ ኢዮ 8፤8 በማለት የተናገረው ለዚሁ ነው፡፡ አባትህን ጠይቅ ያስታውቅህማል ሽማግሌዎችን ጠይቅ  ይነግሩህማል ዘዳ 32፤7
አንድ በሓላፊነት ላይ ያለ ሰው የሚሰራው ስራ ውጤታማ እንዲሆን የግድ አማካሪ እንደሚያስፈልገው ሁሉ በመንፈሳዊ ሕይወቱም ውጤታማ ሊሆን የሚፈልግ ሰውም አማካሪ ያስፈልገዋል፡፡ ነገር ግን ከፉ ምክርም እንዳለ መጠንቀቅ  እንደሚገባ መዘንጋት የለበትም እውነተኞቹ  የቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት ብዙ ጊዜ በየ ካፍቴርያውና በመሳሉት ቦታም ስለማይገኙ ምእመናን መቀላሉ ስለማያገኗቸው ለክፉ መካሪዎች እንዳይጋለጡ  መጠንቀቅ ያስፈልጋል ፡፡
3.ከኃጢአት መንጻት     
ኃጢአት ሰው መልካም ሆነውን ነገር ተግባራዊ እንዳያደርግ የሚያደርግ የሰው ልጆች የመንፈሳዊ ሕይወት ማነቆ ነው፡፡ የሚጠጋውም ርኩስ መንፈስ ብቻ ነው ከዚህ የተነሳ መንፈሳዊ ነገር ማሰብም ሆነ መሥራት አይችልም ፡፡መልካም ባታደርግ ግን ኃጢአት በደጅ ታደባለች ፈቃድዋም ወደ አንተ ነው፡ ዘፍ 4፤7  /  ሰው በኃጢአት በኖረ ቁጥር መልካም አስተሳሰቡ ቀናነቱ ሌሎችም መንፈሳዊ ተግባራትና ሐሳብ እየመነመኑ ይሄዳሉ ብሎም ይጠፋሉ ለዚህ ሁሉ መነሻው ኃጢአት ነው፡፡የኃጢአተኛ መብራት ይጠፋል፡ የእሳቱም ነበልባል ብልጭ አይልም፡ኢዮ 18፤5 / ተብሎ እንደተጻፈው ፡፡ ስለዚህ ሰው ከኃጢአት ሳይነጻ ፈቃደ እግዚብሔርን ማውቅ መረዳት አይችልም፡፡ እግዚአብሔር በሰው በጎ ሥራ ከተደሰተ ለሰው ሁሉ የሚያስፈልገውን የሚያውቅ አምላክ ነውና በጊዜውና በሰዓቱ ሁሉንም ያከናውናል፡፡ እግዚአብሔር የሚያደርገው ሁሉ በጎ ነውና፡፡



 

“መላእክት ሁሉ ረቂቃን አይደሉምን የዘላለም ሕይወትን ይወርሱ ዘንድ ላላቸው ለአገልግሎት ይላኩ የለምን” ዕብ.1፡14



አትም ኢሜይል
 ሐምሌ 17 ቀን 2006 ዓ.ም.
kedus kerkos eyeleta
መላእክት እግዚአብሔር ሰማይንና ምድርን የሰማይንም ሠራዊት ፈጠረ በሚለው አንቀጽ እንደተጠቀሰው፤በመጀመሪያው ቀን በዕለተ እሑድ በእግዚአብሔር ቃል ተፈጥረዋል፡፡ እግዚአብሔር አፈጣጠሩ ድንቅ ነውና መላእክትን እንደ እሳትና ነፋስ የማይዳሰሱ የማይታዩ አድርጎ ፈጥሯቸው ያመሰግኑታል፡፡ ዘፍ.1፡1 መዝ.108፡4፣ ዕብ.1፡12

እግዚአብሔር የፈጠራቸው 20 ዓለማት ሲኖሩ ሦስቱ፤ ኢዮር፣ ራማ፣ ኤረር የመላእክት ከተሞች ናቸው፡፡

መላእክት በ30 ነገድ በ10 አለቃ ተከፋፍለው እግዚአብሔርን የሚያመሰግኑ ለፍጥረታት ሁሉ ምሕረትን የሚለምኑ ናቸው፡፡ 10ሩ ነገድ መኳንንት ይባላሉ፡፡ እነዚህ መላእክት ዓለትን ተራራን ሠንጥቀው የሚሄዱ፣ ቀስት መሳይ ምልክት ያላቸው፣ በትንሣኤ ዘጉባኤ ጊዜ ነፍስና ሥጋን የሚያዋሕዱ መላእክት ሲሆኑ አለቃቸው ሰዳክያል ይባላል፡፡

10ሩ ነገድ ሊቃናት ሲባሉ የእሳት ሠረገላ ያላቸው፣ ኤልያስን በሰረገላ የወሰዱት መላእክት ሲሆኑ አለቃቸው ሰላትያል ይባላል፡፡ 10ሩ ነገድ መላእክት ይባላሉ፡፡ ሕይወት የሌለውን ነገር ሁሉ በሥርዓት እንዲቆዩ የሚጠብቁ ሲሆኑ አለቃቸው አናንያል ይባላል፡፡ የኃይላት አለቃቸው ቅዱስ ሚካኤል ሲሆን የአርባብ አለቃቸው ደግሞ ቅዱስ ገብርኤል ነው፡፡

መላእክት ብርሃናዊ መልአክ ስለሆኑ የሚያግዳቸው የለም፡፡ አለት ተራራን ሰንጥቀው የመግባት አንዱ በአንዱ የማለፍ ችሎታ አላቸው፡፡ እንደ መብረቅ እንደ እሳት የመሆን ባሕርይ አላቸው፡፡

መላእክት ትጉኃን ናቸው፡፡
“መላእክት ሁሉ ረቂቃን አይደሉምን የዘላለም ሕይወትን ይወርሱ ዘንድ ላላቸው ለአገልግሎት ይላኩ የለምን” ዕብ.1፡14 እንዳለ እረፍታቸው ምስጋና ምስጋናቸው እረፍት ሆኖ ሌት ተቀን ይተጋሉ፡፡

መላእክት በእግዚአብሐር ፊት ይቆማሉ፡፡
መላእክት ለምሕረት በእግዚአብሐር ፊት ይቆማሉ፡፡ “በእግዚአብሔር ፊት የቆሙ ሰባት መላእክት አየሁ፡፡” ራዕ.8፡2፡፡እኔ በእግዚአብሔር ፊት የምቆመው ገብርኤል ነኝ ሉቃ.1፡19፣ ዘካ.1፡12 ፡፡
መላእክት ተራዳኢ ናቸው፡፡

ቅዱስ ዳዊት “የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራሉ ያድናቸውማል” መዝ.33፡7፡፡ ሲል በዘፍ.48፡16 “ከክፉ ነገር የዳነን የእግዚአብሔር መልአክ እርሱ እኒህን ሕፃናት ይባርክ” በማለት ተራዳኢነታቸውንና በረከትን የሚያሳድሩ መሆናቸውን ያስረዳል፡፡ “ያን ጊዜም የጴጥሮስ ልቡና ተመልከትና እግዚአብሔር በዕውነት መልአኩን ልኮ ከሄሮድስ እጅና ከአይሁድ ሕዝብ ምኞት ሁሉ እንዳዳነኝ አወቅሁ አለ ሐዋ.12፡16፡፡ እነሆ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ ዳን.10፡13 ማቴ.18፡10 የመላእክትን ተራዳኢነት ያስረዳል፡፡

ጠባቂዎቻቸው ዘወትር የአባቴን ፊት ያያሉ፡፡

መላእክት ይጠብቁናል

በመንገድህ ሁሉ ይጠብቁን ዘንድ መላእክቱን ስላንተ ያዛቸዋልና እግርህም በድንጋይ እንዳትሰናከል በእጆቻቸው ያነሡናል” መዝ.90፡11-12፡፡ “ከነዚህ ከታናናሾቹ አንዱን እንዳትንቁ ተጠንቀቁ፤ መላእክቶቻቸው በሰማያት ዘወትር በሰማያት ያለውን የአባቴን ፊት ያያሉ እላችኋለሁና። ማቴ18፡10

“በመንገድህ ይጠብቅህ ዘንድ ወዳዘጋጀ ቤት ሥፍራ ያገንህ ዘንድ እነሆ አኔ መልአኩን በፊትህ እሰዳለሁ በፊቱ ተጠንቀቁ ቃሉንም አድምጡ ስሜም በእርሱ ስለሆነ ኃጢአት አትሥሩ ይቅር አይልምና አታስመርሩት ዘፀ.23፡20-22 መላእክት ዕጣንን ያሳርጋሉ፣ ራዕይ.5፡8፣ 8፣3 ፡፡ መላእክት የጸጋ ስግደት ይሰገድላቸዋል ዳን.5፡፡ኢያ.5፡13፣ ነገ.19፡6 15፣ ዘፍ.22፡3 መላእክት የምንመገበውን ይሰጡናል/ይመሩናል/ ት.ዳ.3 መላእክት ከእስር ያስፈታሉ ሐዋ.12፡6፡፡ መላእክት ይፈውሳሉ “እግዚአብሔር የበለዓምን ዐይን ከፈተ ዘሁ.22፡31

የመላእክትን አፈጣጠራቸውን፣አገልግሎታቸውን በመጠኑ ከተረዳን ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት አንዱ የሆነው ቅዱስ ገብርኤል ሐምሌ 19 ቀን ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስና እናቱ ኢየሉጣን ያዳነበት፣የጸናናበት ለክብር ያበቃበትን ቀን በድርሳነ ገብርኤል የተገለጸውን እንዲህ አቅርበነዋል፡፡

ድርሳነ ገብርኤል ዘሐምሌ
በአገዛዝና በቅድምና ትክክል የሆነ፣ ከመታሰቡ አስቀድሞ ሁሉን መርምሮ የሚያውቅ፣ ክረምትን በየዓመቱ የሚያመጣ፣ ሰማይን በደመና የሚጋርድ፣ ምድርን በልምላሜ የሚሸፍናት፣ የባሕርን ውኃ በእፍኙ የሚለካ፣ ምድርን በስንዝሩ የሚመጥናት ከኛ ዘንድ ለሱ ምስጋና የሚገባው፣ ለኛ ሕይወትን የሚሰጠን አንድ አምላክ በሚሆን በአብ፣ በወልድ፣ በመንፈስ ቅዱስ ስም አምነን በሐምሌ 19 ቀን የሚነበብ የሚጸለይ የሰማያውያን አለቃ የሚሆን የቅዱስ ገብርኤል ድርሳን ይህ ነው፡፡

እለ እስክንድሮስ የተባለ መኰንን በኢየሱስ ክርስቶስ ያመኑትን ክርስቲኖች ለመቀጣትና ሌሎችም ፈርተው ክርስትናን እንዳይፈልጉ ለማድረግ አስቦ ሰም፣ ጨው፣ ባሩድ፣ ሙጫ፣ የዶሮ ማር፣ እርሳስ፣ ብረት፣ ቅንጭብ፣ ቁልቋል አንድ ላይ ተቀላቅሎ በብረት ጋን እንዲፈላ አዝዞ ነበር፡፡ ጭፍሮቹም እለስክንድሮስ እንዳዘዛቸው ከአደረጉ በኋላ ያዘዝኸንን ሁሉ ፈጽመን እሳቱ ነዶ ፈልቷል፤ ድምፁ እንደነጐድጓድ ይጮሃል፤ ወላፈኑም እንደ ፀሐይ ነፀብራቅ በሩቅ ይጋረፋል፤ የፍላቱም ኀይል አሥራ ዐራት ክንድ ያህል ከፍታ ወደላይ ይዘላል፤ እንግዲህ በውስጡ የሚጣሉትን እዘዝ አሉት፡፡

በዚህ ጊዜ ሕፃን ቂርቆስና እናቱ ኢየሉጣ በክርስቶስ ስም ስለሚያምኑ አሥረዋቸው ነበርና ከፍላቱ ሊጨምሯቸው ከእሥር ቤት አወጧቸው፡፡ ፍላቱ ወደ ላይ በሚዘል ብረት ጋን ውስጥ ለመጨመር ሲወስዷቸው የእነዚህን ቅዱሳን አሟሟት ያዩ ዘንድ በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ሰዎች እንዲሰበሰቡ ታዘዘ፡፡

በዚህ ጊዜ ቅድስት ኢየሉጣ የፍላቱን ጩኸት በሰማችና ባየች ጊዜ ተሸበረች፤ ተዘጋጅቶላት ከነበረውም ክብር ልታፈገፍግ ሞከረች፡፡

ልጅዋ ቅዱስ ቂርቆስ ግን እናት ሆይ ከዚህ የብረት ጋር ግርማ የተነሣ አትፍሪ፤ ድንጋፄም አይደርብሽ፤ አናንያንና አዛርያን፣ ሚሳኤልንም እግዚአብሔር ከዕቶነ አሳት እንዳወጣቸው ሁሉ እኛንም ከዚህ ከብረት ጋን ሊያወጣን ችሎታ ያለው መሆኑን አትጠራጠሪ ፡፡ እናት ሆይ ከዚህ ከሚያልፈው ዓለም ጭንቅና መከራ ለማዳን ስትይ በማያልፈው በዘለዓለም እሳት ለመቀጣት ትመርጫለሸን? ይህስ አይሆንም፤ ይቅርብሽ፤ በአሁኑ ጊዜ እግዚአብሔር በመካከላችን አለና ይረዳናል፡፡ እናቴ ሆይ ሶስናን ከእደ ረበናት፣ /መምህራነ አይሁድ/ ዳንኤልን ከአፈ አናብስት ያዳነ እሱ እኛንም ከዚህ የጋን ፍላት ያወጣናል፡፡ ይልቁንም እግዚአብሔር በዚህ የብረት ጋን ውስጥ ግዳጃችንን ልንፈጽም ፈቅዶ ከሆነ ኢዮብ ንብረቱንና ገንዘቡን፣ ልጆቹንና ሚስቱን፣ በመጨረሻም የተፈጥሮ አካሉን ባጣ ጊዜ እግዚአብሔርን አመሰግነዋለሁ፤ እግዚአብሔር ሰጠ፤ እግዚአብሔር ነሣ፤ /ወሰደ/ እግዚአብሔርም እንደ ወደደ አደረገ፤ ከማለት በስተቀር ምንም የተናገረው ክፉ ነገር እንደሌለ ሁሉ እኛም የሱን ዓላማ በመከተል ይህን መከራ ልንታገሥ ይገባናል፤ አላት፡፡

ነገር ግን እናቱ ቅድስት ኢየሉጣ በዚህ ምክር ልትጽናና ባለመቻሏ ቅዱስ ቂርቆስ ዓይኑን ወደ ሰማይ አቅንቶ አቤቱ አምላኬ ሆይ ይህችን ባሪያህን ከርስትህ የምትለያት ከሆነ ከባለሟልነትህ መጽሐፍ ፋቀኝ፤ አቤቱ አዝመራውን አቃጥለህ ፍሬውን ልትባርክ ትወዳለህን ይህን እንዳታደርግ ግን ቸርነትህ ትከለክልሃለች፡፡

አቤቱ እንጨቱን ቆርጣችሁ አንድዱት፤ ቅጠሉን ግን ጠብቁት፤ ብለህ ልታዝ መለኮታዊ ባሕርይህ አይደለም፤ ነገር ግን እንጨቱንም ቅጠሉንም ባንድ ጠብቁት፤ ብለህ ታዝዛለህ እንጂ፤ እንግዲህ በዚህ ምክንያት ይህን ያየ ሁሉ ማዳን የሚችል አምላክ ቢኖራቸውስ ኖሮ ከዚህ ከእሳት ባልሸሹም ነበር ብሎ አይጠራጠር፡፡

አቤቱ ዲያብሎስም ከባለሥልጣኑ ይልቅ እኔ በረታሁ፤ ቅዱሳኖቹንም ድል ነሣኋቸው፤ ብሎ እንዳይመካ ከመንጋውም አንድ በግ ቀማሁ፤ በማለት እንዳይደነፋ ለናቴ ጽኑ የሆነ ኃይለ መንፈስ ቅዱስን ስጣት፤ ብሎ በጸለየ ጊዜ ዲያብሎስ ከኢየሉጣ አጠገብ ብን ብሎ ጠፋ፡፡

ከዚህ በኋላ ቅድስት እናቱ በሰማያዊ መንግሥት አባት የሆንከኝ ልጄ ሆይ ጌታህ ኃይልን ሰጥቶኛልና የሚጠብቀንን ገድላችንን ፈጽመን ድል እናድርግ፤ እነሆ በብረት ጋኑ ውስጥ የሚነደውን እሳት በማይበት ጊዜ በለምለም /በምንጭ/ ላይ እንደሚወርድ ጠል ሆኖ አይቼዋለሁና አለችው፡፡

እኒህም ቅዱሳን ይህን በሚነጋገሩበት ጊዜ በውስጡ አንገትን የሚቆለምም፣ ልብን የሚያቀልጥ፣ ሆድን የሚሠነጥቅ፣ ሥርን የሚበጣጥስ መሣሪያ ካለበት የብረት ጋን ውስጥ ጨመሯቸው፡፡ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል ከሰማይ ወረደና የብረቱን ጋን እሳት አጠፋው፤ ከቅዱሳኑም አንዳቸውንም ሳያቃጥላቸው የብረቱ ጋን ማቃጠሉና መፍላቱም ፀጥ አለ፡፡

ወንድሞቻችን ሆይ እንግዲህ በጭንቃቸው ጊዜ ገድላቸውን እስኪፈጽሙ ድረስ ይህ መልአክ ከሰማዕታትና ከጻድቃን ጎን እንደማይለይ እወቁ፡፡ ለኃጥአንም ኃጢአታቸውን ይቅር ይላቸው ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ይጸልይላቸዋል፡፡ እኛም የዚህን የሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል በዓሉን በየወሩ እያከበርን አማላጅና ወዳጅ እናድርገው፤ በዚህም በሚመጣውም ዓለም ሊረዳን ይችላልና፡፡

ዳግመኛም እለ እስክንድሮስ ሀሳቡ ሳይሳካለት ስለቀረ አሥራ አራት የሾሉና የጋሉ የብረት ችንካሮች አምጥተው ሰባቱን በእናቱ በኢየሉጣ አካል፣ ሰባቱን በቂርቆስ አካል ይቸነክሯቸው ዘንድ ጭፍሮቹን አዘዘ፡፡

ዳግመኛም የሕፃንን የእራስ ቆዳ ገፈው እሳት ውስጥ ይጨምሩት ዘንድ አዘዘ፡፡ አሁንም መልአኩ መጥቶ ይህን መከራ አራቀለት፡፡ ቀጥሎም በመቃን ውስጥ ጨምረው በገመድ እንዲጎትቱት አዘዘ፤ በዚህም ጊዜ መልአኩ አዳነው፡፡ ሕዝቡም ይህን ሁሉ ተአምር በአዩ ጊዜ እግዚአብሔርን አመሰገኑት፤ ቅዱስ ገብርኤልንም አከበሩት፡፡ እነዚህን ቅዱሳን ረድቶ ለክብር ያበቃ ቅዱስ ገብርኤል እኛንም በሃይማኖት ጸንተን ለክብር እንድንበቃ ይርዳን፡፡

የቅዱስ ገብርኤል፣የቅድስት ኢየሉጣና የቅዱስ ቂርቆስ በረከት አማላጅነት አይለየን፡፡

ሐምሌ 17 ነቢዩ ቅዱስ ዮናስ

በ ዲ.ዮርዳኖስ አበበ 
(ናታኒም ጡመራዊ መጽሔት ሐምሌ 17)"+እን  ለነቢዩ ቅዱስ ዮናስ እና ለእናታችን ቅድስት አፎምያ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ +"+

+" ቅዱስ ዮናስ ነቢይ "+

=>በቤተ ክርስቲያን አስተምሕሮ ከ12ቱ ደቂቀ ነቢያት አንዱ የሆነው ቅዱስ ዮናስ ከክርስቶስ ልደት 800 ዓመታት በፊት እንደ ነበረ ይታመናል:: ሊቃውንት እንዳስተማሩን ደግሞ እናቱ ቅዱስ ኤልያስን የመገበችው የሰራፕታዋ መበለት ናት:: ቅዱስ ዮናስ ገና ሕጻን ሳለ በእሥራኤል ምድር ዝናብ ለ3 ዓመታት ከ6 ወራት ተከልክሎ ነበር::

+ይሕንንም ያደረገው ደጉ ነቢይ ኤልያስ ለአምልኮተ እግዚአብሔር ቀንቶ ነው:: በወቅቱ ኤልያስ በሰራፕታ ሳለ ሕጻኑ ዮናስ ታሞ ሞተ:: ልጇ የሞተባት መበለትም ኤልያስን ለመነችው:: ኤልያስም ወደ ፈጣሪው ማልዶ ሕጻኑን ዮናስን ከሞት አስነስቶታል:: ትንሽ ከፍ ባለ ጊዜም ከጉዋደኞቹ (ከነቢያቱ) አብድዩና ኤልሳዕ ጋር ሆነው ታላቁን ነቢይ ኤልያስን ተከትለውታል::

+ኤልያስ ካረገ በሁዋላ ሁሉም በየተሰጣቸው አገልግሎት ተሠማርተዋል:: ቅዱስ ዮናስን እግዚአብሔር "ወደ ነነዌ ሒደሕ ንስሃን ስበክ" አለው:: ዮናስ ግን የፈጣሪውን መሐሪነት ጠንቅቆ ያውቃልና አልሔድም አለ:: (ተመልከቱ የየዋሕነት ብዛት)

+እግዚአብሔር እየደጋገመ እንዲሔድ ሲነግረው ነቢዩ "እንዲሕ የሚዘበዝበኝ ከፊቱ ብቀመጥ አይደል" ብሎ ሊኮበልል ወጣ:: ነገር ግን አልቀናውም:: በእርሱ ምክንያት ማዕበል ተነሳ:: ሕዝቡም ሊያልቁ ሆነ:: ከእንቅልፉ የነቃው ዮናስ ከመርከቡ ላሉት አሕዛብ አምልኮተ እግዚአብሔርን ሰብኮላቸው: በእርሱ ጠያቂነት ሐምሌ 15 ቀን ወደ ባሕር ጥለውታል::

+አሣ አንበሪም ተቀብሎታል:: በግዙፉ አሣ ውስጥም ያለ እንቅልፍ በጾም: በጸሎትና በምስጋና 3 ለቀን ቆይቷል:: ሙስና ሳያገኘውም በዚህች ቀን አሣ አንበሪው ነነዌ ዳር ላይ ተፍቶታል:: ቅዱስ ዮናስ እግዚአብሔር እንዳዘዘው "እስከ ሠሉስ ዕለት ትትገፈታእ ነነዌ ዓባይ ሃገር" /እስከ ሦስት ቀን ድረስ ነነዌ ትገለበጣለች (ዮናስ 3:4)/ ብሎ አሰምቶ ሰበከ::

+የነነዌ ሰዎችም በስብከተ ዮናስ አምነው: ንስሃም ገብተው ድነዋል:: በዚህም ጌታችን በወንጌል ላይ አመስግኗቸዋል:: ቅዱስ ዮናስ መኮብለሉ በሐዲስ ኪዳን ለሚደረገው ምስጢረ ትንሳኤ ጥላ (ምሳሌ) ነውና ይደነቃል:: (ማቴ. 12:38) ነቢዩ ግን በተረፈ ሕይወቱ ሕዝቡን ሲያስተምር: ፈጣሪውን ሲያገለግል ኑሮ በመልካም ሽምግልና ዐርፏል::

+" ቅድስት አውፎምያ ሰማዕት "+

=>እናታችን ቅድስት አውፎምያ (ስሟ አፎምያ አይደለም:: በስሕተት "ው" መካከል ላይ የገባች እንዳይመስልዎ:: እስመ ከመዝ ስማ-ስሟ እንዲሁ ነው የሚጠራው) በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን ከነበሩ ወጣት ክርስቲያኖች አንዷ ናት:: ገና ከልጅነቷ ልቧ በፍቅረ ክርስቶስ የተነደፈ ነበር::

+በዚህም ምክንያት ራሷን በጾምና በጸሎት ወስና ትኖር ነበር:: እድሜዋ ገና በአሥራዎቹ ቢሆንም በመንኖ ጥሪት መኖር ምርጫዋ ነበር:: ሊቃውንት አበው ከሰማዕትነቷ ደርበው "ጻድቅት አውፎምያ" እያሉም ይጠሯታል::

+አንድ ቀን ግን መንገድ ወጥታ ነበርና ክርስቲያኖች ሲሰቃዩ ተመለከተች:: ምንም ጥፋት ሳይገኝባቸው ክርስቶስን ስላመለኩ ብቻ ይሙት በቃ ተፈርዶባቸው ሊገደሉ እየተወሰዱ ነበር:: አሕዛብ ግብራቸው የአውሬ ነውና ርሕራሔ የላቸውም:: ሰማዕታቱ ደማቸው በየመንገዱ እየፈሰሰ: ጥቁር ሰንሰለት በአንገታቸው: በእጃቸውና በእግራቸው ላይ አድርገው ይጐትቷቸው ነበር::

+ቅድስት አውፎምያ የተደረገውን ሁሉ ተመልክታ አምርራ አለቀሰች:: ፈጠን ብላም ወደ መኮንኑ ቀርባ ገሰጸችው:: "አንተ አእምሮ የጎደለህ! እንዴት ክርስቲያኖችን እንዲህ ታሰቃያለህ? አምላካቸው ጌታ ክርስቶስ ታጋሽ ባይሆን ኑሮ በቅጽበት ከገጸ ምድር ባጠፋህ ነበር" አለችው::

+በድፍረቷ የተገረመው መኮንኑ "አንቺስ ማንን ታመልኪያለሽ?" ሲል ጠየቃት:: እርሷም "ሰማይና ምድርን የፈጠረውን: ስለ እኛ ሲል በቀራንዮ አንባ የተሠዋውን ኢየሱስ ክርስቶስን አመልካለሁ" ስትል መለሰችለት:: በዚያች ሰዓት የመኮንኑ ቁጣ በቅድስቷ ላይ ነደደ::

+ነገር ግን ቁጣውን ከቁም ነገር አልቆጠረችውምና እንዲያሰቃዩዋት አዘዘ:: ወታደሮቹ ሥጋዋን በብዙ አሰቃዩ:: ብላቴናዋ አውፎምያ ግን ጽንዕት ናትና አልቻሏትም:: በመጨረሻ በእሳት ተቃጥላ ትሞት ዘንድ ተፈረደባት::

+እሳቱ ከመሬት ከፍ ባለ ጊዜ ወደ ውስጥ ወረወሯት:: በእሳቱ መካከል ቁማ ለረዥም ጊዜ ጸለየች:: ከዚያም ነፍሷን አሳልፋ ሰጠች:: ምዕመናን በክብር ገንዘው ቀብረዋታል::

=>አምላካችን ከነቢዩና ከሰማዕቷ ወዳጆቹ በረከት ይክፈለን::

=>ሐምሌ 17 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱስ ዮናስ ነቢይ (ከአሣ አንበሪ ሆድ የወጣበት)
2.ቅድስት አውፎምያ (ጻድቅትና ሰማዕት)
3.ቅዱስ ዮስጦስ ሰማዕት (ታላቁ)
4.ቅዱስ ዘካርያስ

=>ወርኀዊ በዓላት1.ቅዱስ እስጢፋኖስ ሊቀ ዲያቆናት (ቀዳሜ ሰማዕት)
2.ቅዱስ ያዕቆብ ሐዋርያ (ወልደ ዘብዴዎስ)
3.ቅዱሳን አበው መክሲሞስና ዱማቴዎስ
4.አባ ገሪማ ዘመደራ
5.አባ ዸላሞን ፈላሢ
6.አባ ለትጹን የዋህ
7.ቅዱስ ኤዺፋንዮስ ሊቅ (ዘደሴተ ቆዽሮስ)

=>+"+ በዚያን ጊዜ ከጻፎችና ከፈሪሳውያን አንዳንዶቹ መለሱና:- 'መምሕር ሆይ! ከአንተ ምልክት እንድናይ እንወዳለን' አሉት:: እርሱ ግን መልሶ እንዲህ አላቸው:- 'ክፉና አመንዝራ ትውልድ ምልክት ይሻል:: ከነቢዩም ከዮናስ ምልክት በቀር ምልክት አይሰጠውም:: ዮናስ በአሣ አንበሪ ሆድ ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት እንደ ነበረ እንዲሁ የሰው ልጅ በምድር ልብ ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት ይኖራል:: የነነዌ ሰዎች በፍርድ ቀን ከዚህ ትውልድ ጋር ተነስተው ይፈርዱበታል:: በዮናስ ስብከት ንስሃ ገብተዋልና:: እነሆም ከዮናስ የሚበልጥ ከዚህ አለ:: +"+ (ማቴ. 12:38)

<ወስብሐት ለእግዚአብሔር>

                                   በአውሮጳ   የካህናት አንድነት ማኅበር ሊቋቋም መሆኑ ታወቀ በ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከመላዋ አውሮጳ   የተውጣጡ ካህናት፡” የ...