2014 ዲሴምበር 24, ረቡዕ

የገና ዛፍ የነጮች የባዕድ አምልኮ መገለጫ መሆኑን ያውቃሉ? የገና ዛፍ ታሪክና አመጣጡ




የገናን ዛፍ የት መጣውን /ምንጩን/ ስናጤነው ቅዱሳት መጻሕፍት እንዲህ ይነግሩናል። በዞራስተርን የሁለት አማልክት ዕምነት የሚያምኑት ምዕራባውያን አዲሱን ዓመታቸውን /2015/ ለመቀበል ዝግጀት ላይ ይገኛሉ። በዞራስተርን የሁለት አማልክት ዕምነት መሠረት ክፉውና ደጉ የተባሉ ሁለት አማልክቶች አሉ። እንደ ዕምነቱ አስተሳሰብ ከሆነ እዚህ ምድር ላይ የሆነው እየሆነው ያለውና የሚሆነውም ማንኛውም ነገር በሙሉ የሚከናወነው በእነዚህ በሁለቱ አማልክቶች ፉክክር ነው። ክፉው አምላክ ከሰለጠነ /የበላይ ከሆነ/ በምድር ላይ ክፉ የሆኑ ብዙ ነገሮች ይከሰታሉ። በተቃራኒው ደግሞ ደጉ አምላክ ከሰለጠነ በጎ ነገሮች ይከሰታሉ ማለት ነው። ምዕራባውያኑ ታዲያ ደጉን አምላካቸውን ማለትም ጣዖታቸውን ሳተርን ብለው ይጠሩታል።
በምዕራቡ ዓለም የክረምቱ ወቅት በጣም አስቸጋሪ ነው። ዛፎች ሁሉ ቅጠሎቻቸው ይረግፋሉ። ልምላሜ አይታይባቸውም። ፅድ ግን በተፈጥሮው ይህን አስቸጋሪ ወቅት ተቋቁሞ የማለፍ ኃይል አለው። በመሆኑም ፅድ ክፉውን ዘመን /ክረምቱን/ ተቋቁሞ መልካሙ ዘመናቸው እስኪመጣላቸው ድረስ በልምላሜ ይቆይላቸዋል። ይህም ሳተርን /ደጉ አምላካቸው/ ከክፉው አምላክ ለመሸሸግ በፅድ ውስጥ ተደብቆ ይኖራል ብለው ያመናሉ ምዕራባውያኑ። እናም ብራ ሲሆን /በእኛ መስከረም ጠባ እንደምንለው ነው/ የደጉን አምላክ ‹‹የእንኳን ደህና መጣህ›› በዓልን በድምቀት ያከብራሉ።
ምስጋና ለፅዱ ይሁንና ደጉ አምላካቸውን ደብቆ ስላቆየላቸው ባለውለታ ስለሆነ የደጉን አምላክ የእንኳን ደህና መጣህ በዓል ሲያከብሩ ታዲያ ፅድን ለበዓላቸው ማድመቂያነት ይጠቀሙበት ነበር። ይኸው ትውፊታቸው ዛሬም ድረስ አለ። በአጭሩ ከጥንት ጀምሮ እነርሱ ይኽን በዓል የሚያከብሩት ሳተርን ለተባለው ጣዖት /ደጉ አምላክ/ ያደርጉት የነበረው ሥርዓት ነው። በዚህ ዓይነት ሁኔታ ታላቁ ንጉሥ ቆስጠንጢኖስ ክርስትናን በአዋጅ ካስፋፋበት ጊዜ ጀምሮ በውጭው ዓለም ጥንት የነበሩ ብዙ ጣዖታዊ በዓላት ክርስቲያናዊ በዓል ሆነው አሁንም ድረስ በብዙ ሀገራት እየተከበሩ ይገኛሉ። /ነገር ግን ልደትንና ትንሣኤን ጨምሮ ሌሎችም በዓላት ቢሆኑ ሥርዓታቸውን በጠበቁ መልኩ የሚከበርባቸው አንዳንድ ሀገራት እንዳሉ የዚህ ጽሑፍ አዘጋጅ ለማስገንዘብ ይወዳል።/
በአንድም ይሁን በሌላ ምክንያት በማወቅም ይሁን ባለማወቅ ይኸው እስከዛሬ እኛም ይኽንኑ የባዕድና የጣኦት አምልኮ በዓላቸውን በእነሱው ልማድ መሠረት የፅድ የገና ዛፍ እየሠራን ስናከብርላቸው ኖረናል። አሁንም ትንሽ ቀን ብቻ የቀረውን የገናን በዓል በእንዲሁ ዓይነት ሁኔታ ለማክበር ሽር ጉድ እያልን ነው። አባቶቻችን ሲናገሩ ‹‹እግዚአብሔር ዓለሙን ከፈጠረበት ጥበቡ ይልቅ ሰው ሆኖ ዓለሙን ያዳነበት ጥበቡ እጅግ ረቂቅና ጥልቅ ነው›› ይላሉ። እንዴት ደስ የሚል አገላለፅ ነው!!! ታዲያ ምን ዋጋ አለው? አለመታደል ሆኖ ይሁን አሊያም አለማወቃችን ለስም አጠራሩ ክብር ምስጋን ይግባውና እጅግ ድንቅ የሆነውን የጌታችንን የአምላካችንን የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን የልደት በዓል ከእንደዚህ ዓይነቱ ምዕራባዊ የጣዖት በዓል ጋር ቀላቅለን እናከብራለን። ይህ እጅግ አሳዘኝ ነገር ነው በእውነት!
በአንድ ወቅት በምዕራባውያን የገና በዓል ሰሞን ‹‹BBC channel 4›› ላይ የበዓል መርሀ ግብር /program/ ቀርቦ ነበር። በመርሀ ግብሩ ላይ የተለያዩ የዕምነት ድርጅቶች የበዓል አከባበር፣ የጸሎትና የመዝሙር ሥርዓትና ሌሎችንም ሃይማኖታዊ ሥርዓቶች ከቀረቡ በኋላ የመርሀ ግብሩ መሪ በመጨረሻ እንዲህ ነው ያለው፡- “now let us see the real Christianity” ማለትምአሁን እውነተኛውን የክርስትና ሃይማኖት እንመልከትበሚል መሸጋገሪያ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን የበዓል አከባበር ስነ-ሥርዓት ማስተላለፍ ጀመረ። ካህናት አባቶች ወረብ ሲያቀርቡ፣ የቅዳሴውን ሥርዓት፣ መዝሙሩ ሲዘመር፤ ጧፉ እየበራ ወንጌሉ ሲነበብ፣ እጣኑ እየጤሰ ስብሐተ እግዚአብሔር ሲቀርብ...... ሁሉንም በየተራ ማቅረብ ጀመረ። እናም እነርሱ ማለት ምዕራባውያን ስለ ዕምነት ጉዳይ እውነት የሆነውን ነገር ፍለጋ ፊታቸውን ወደ እኛ ባዞሩበት ወቅት እኛ ደግሞ እውነተናውን ማንነታችንን ባንጥልና የአጉል ባህል ተገዢዎች ባንሆን ብሎም በአምልኮ ጣኦታቸው ተሳታፊዎች ባንሆን መልካም ነው። መልካም ነው ብቻም ሳይሆን መንፈሳዊና ሞራላዊ ግዴታዎችም አሉብን። በእርግጥ እኛ የዚህ ዘመን ትውልዶች የግሎባላይዜሽን ጎርፍ ጠራርጎ የወሰደን ስለሆንንና ‹‹በጣም ስልጡኖችና ዘመናውያንም›› ስለሆንን ይህ ምን ማለት እንደሆነ ላይገባን ይችላል፤ እንዲገባንም አንፈልግም፡፡ 
የእነርሱን ጥሩውንና መጥፎውን ነገር እንኳን ለይተን መውሰድ ስላልቻልንና ሁሉንም ነገር ከነ አሠስ ገሠሱ ስለምንቀበል ይህንን ደካማ ጎናችንን ያወቁ ‹‹ዘመናዊ ቅኝ ገዢዎቻችን›› ለሁሉም ነገር ምቹ ሆነንላቸው አግኝተውናል። የሴቶቻችን እርቃን መሄድ፣ አካሎቻቸውን መነቀስና መበሳት፣ የወንዶች አለባበስና ፀጉር አቆራረጥእነዚህና ሌሎቹም ነገሮች በዘመናዊነት ሰበብ የመጡብን የዘመናዊ ቅኝ ግዛት ውጤቶች ናቸው፡፡ በግል አዳኝ ‹‹ኢየሱሴ›› ስም ብዙኃኑን ሕዝባችንን ፈጣሪውን አስክደው አምላክ የለሽ አደረጉትና ለግሎባላይዜሽናቸው የተመቸ ዝርው ትውልድ ፈጠሩ፡፡ አሁንማ ጭራሽ ለይቶላቸው ‹‹church of Satan›› በማለትየሰይጣን ቤተክርስቲያንከፍተው አባሎቻቸው በሆኑ ‹‹ታዋቂ የሂፖፕ›› አቀንቃኞቻቸው አማካኝነት የአባላቶቻቸውን ቁጥር ለመጨመር እኛም ሀገር ብቅ ብለውልናል፡፡ ግብረ ሰዶማዊነት እንደግለሰብ ነፃነት አድርጋችሁ ካልተቀበላችሁ እርዳታ አንሰጣችሁምም ተባልን፡፡ እሺ እነዚህና ሌሎቹም አስከፊ ኃጢአቶቻቸውን በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ እንድንቀበል ቢያስገድዱንም ቢያንስ እኛ በራሳችን ጊዜ ለምን የራሳችንን ባሕል ድምጥማጡን በማጥፋት የእነርሱን ባሕል እንከተላለን? የዘመናዊነት መገለጫው የራስን ባሕልና እምነት በሌሎች መተካት ሆነ እንዴ? ድሮ ቅኝ ቅዛት ተገዝተን ቢሆን ኖሮ ምንድን ነበር የምናጣው? ቀላል ነው መልሱ፡- የራስ ማንነት፣ እምነት፣ ባሕል፣ ታሪክአይኖረንም ነበር፡፡ አሁን ታዲያ በዘመናዊው ቅኝ አገዛዝ ሥርዓት ምክንያት እነዚህን ነገሮች አላጣናቸውም ይሆን? እንዲያው በመድኃኔዓለም! እባካችሁ ከፊት ለፊታችን በታላቅ ጉጉትና ተስፋ የምንጠብቀውን ከድቅድቅ ጨለማ ወጥተን ብርሃን ያገኘንበትን የአማኑኤልን የልደት በዓል የገናን ዛፍ በመጠቀም ከነጮቹ ባዕድና ጣኦት አምልኮ ጋር አንቀላቅለው፡፡ ልደቱን ቅድስት ቤተክርስቲያን እንደሚገባው አድርጋ ታከብረዋለችና እኛም ልጆቿ እንደሚገባው መጠን ልደቱን እናክብር፡፡ የገና ዛፍ የባዕድ አምልኮ መገለጫ ነው፡፡ ማህቶተ ቤተክርስቲያን ብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ ምንድን ነበር ያለው! ‹‹ከማያምኑ ጋር በማይመች አካሄድ አትጠመዱ፤ ጽድቅ ከዓመፅ ጋር ምን ተካፋይነት አለውና? ብርሃንም ከጨለማ ጋር ምን ኅብረት አለው? ክርስቶስስ ከቤልሆር ጋር ምን መስማማት አለው? ወይስ የሚያምን ከማያምን ጋር ምን ክፍል አለው? የእግዚአብሔርን ታቦት በጣዖት ቤት ውስጥ የሚያኖር ማነው? 2 ቆሮ 614-16፡፡
በሃይማኖት ብትኖሩ ራሳችሁን መርምሩ” 2 ቆሮ 135፡፡ 
ተዘጋጀ በጀማል ሀሰን ዓሊ (ስመ ጥምቀቱ ገብረሥላሴ) 
የአባቶቻችን አምላክ ልዑል እግዚአብሔር በሃይማኖታችንና በኦርቶዶክሳዊ ማንነታችን ያፅናን አሜን።
(
የጽሑፉ ምንጮች፡- አናቆጸ ሲኦል በብርሃኑ ጐበና፤ ሐመር 5 ዓመት 1 1989 .

2014 ዲሴምበር 23, ማክሰኞ

የሐዊረ ሕይወት መርሐ ግብር በደብረ ሊባኖስ አንድነት ገዳም





ታኅሣሥ 13 ቀን 2007 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
dscn3853ማኅበረ ቅዱሳን 7ኛውን የሐዊረ ሕይወት መርሐ ግብር በደብረ ሊባኖስ ጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት አንድነት ገዳም ታኅሣሥ 12 ቀን 2007 ዓ.ም. አካሔደ፡፡

መነሻውን አዲስ አበባ ከሚገኘው ዋናው ማእከል ያድረገው ጉዞ ከለሊቱ 12፡00 ሰዓት ጀምሮ ከ80 በላይ በሚሆኑ አንደኛ ደረጃ አገር አቋራጭ አውቶቡሶች ከ5000 በላይ ምእመናንን በመያዝ ተንቀሳቅሰዋል፡፡

dscn3547መርሐ ግብሩ በገዳሙ አባቶች በጸሎተ ወንጌል ከረፋዱ 4፡30 ተጀምሯል፡፡ ብፁዕ አቡነ ቀውስጦስ የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤ ብፁዕ አቡነ ማትያስ የካናዳ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤ የገዳሙ 12ቱ ንቡራነ እድ፤ እንዲሁም የአድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች በተገኙበት “ቅንነት ግን ፊቱን ታየዋለች” መዝ. 11፡7 የሚለውን ጥቅስ መነሻ በማድረግ የተዘጋጀው 7ኛው የሐዊረ ሕይወት መርሐ ግብር በመዝሙራቱ፤ እንዲሁም በስብከተ ወንጌል አገልግሎቱ ሲቀርብ ውሏል፡፡dscn3525

በዚህም መሠረት በጠዋቱ መርሐ ግብር ክፍል አንድ የወንጌል ትምህርት የማኅበረ ቅዱሳን መደበኛ ሰባኬ ወንጌል በሆኑት በመምህር ምሥጢረ ሥላሴ ማናዬ “በቅንነት የሚሄድ ይድናል” ምሳ.28፡18 በሚል ርእስ ትምህርተ ወንጌል ሰጥተዋል፡፡

የደብረ ሊባኖስ ገዳም ገዳማዊ ሥርዓቱ እንደተጠበቀ ቢሆንም የጎርፍ አደጋ፤ የብዝኅ ሕይወት መመናመን፤ የሕገ ወጥ የመሬት ወረራና ሌሎችም ችግሮች እየተፈታተኑት ይገኛል፡፡ ይህንን ችግር ለመቅረፍና ዘላቂ መፍትሔ ለማምጣት በገዳሙና በማኅበረ ቅዱሳን ባለሙያዎች ፕሮጀክቶች ተቀርጸው ወደ ሥራ ተገብቷል፡፡ ፕሮጀክቱን አስመልከቶ የተዋቀረው ኮሚቴ ተወካይ በዲያቆን ቱሉ ስለ ጥናቱ ገለጻ ተደርጓል፡፡

በቀረበው ጥናትም የገዳሙ የወደፊት አቅጣጫና ዕጣ ፈንታ ያሳሰባቸው የገዳሙ አባቶች በ2003 ዓ.ም. ለማኅበረ ቅዱሳን በደብዳቤ በማሳወቃቸው ጥናቱን ለማጥናት እንደተቻለ ገልጸዋል፡፡

የተቀረጹት 11 ፕሮጀክቶች በሦስት ዙር በመክፈል እጅግ አንገብጋቢ የሆኑትን፣ የመጸዳጃና የአካባቢ ንጽሕና፤ የመሬት መንሸራተርትና የጎርፍ አደጋ፤ የመነኮሳት በዓት ችግር፤ የአብነት ትምህርት ቤት አደጋ ላይ መሆኑ፤ መቃብር ቦታ ችግር ቅድሚያ ተሰጥቷቸው እንደሚሰሩ የጠቀሱት ዲያቆን ቱሉ በሁለተኛው ዙር የአብነት ትምህርት ቤትና የሥልጠና ማእከል ግንባታ፤ መኪና ማቆሚ ቦታ ዝግጅት፤ መቃብር ሥፍራ ዝገጅት ፕሮጀክች እንዲሁም በሦስተኛው ዙር የጤና ጣቢያ ግንባታ፤ የሁለገብ ሕንፃ ግንባታ፤ የአስኳላ ትምህርት ቤት ግንባታ ፕሮጀክቶች ይተገበራሉ ብለዋል፡፡

በቅድሚያ ሊሰሩ ከታቀዱት ውስጥ 24 ክፍል ያለው መጸዳጃ ቤት ግንባታ ተጠናቆ አገልግሎት መሥጠት መጀመሩን፤ 8 ክፍሎችን የያዘ የገላ መታጠቢያና መጸዳጃ ቤት መጠናቀቁን፤ የሕንፃ ቤተ ክርስቲያኑ መሠረት /ቤዝመንት/ እየገፋ ያለውን ጎርፍ ለመከላከል 100 ሜትር ርዝመት እና 10 ሜትር ቁመት ያለው የጎርፍ መከለያ ግንባታ በመጠናቀቅ ላይ እንደሚገኝ፤ በቅርቡም 2500 ሰው ማስተናገድ የሚችል የእንግዳ ማረፊያና ሁለገብ አዳራሽ ለመሥራት ዲዛይኑ አልቆ ቦታው በዝግጅት ላይ እንደሚገኝ ተጠቅሷል፡፡

dscn3668ከሰዓት በኋላ የተካሔደውን መርሐ ግብር በማኅበረ ሰላም መዘምራንና በሊቀ ዲያቆን ምንዳዬ ብርሃኑ ያሬዳዊ ዝማሬ በማቅረብ ተጀምሯል፡፡

ሁለተኛው የወንጌል ትምህርት በደብረ ገነት ሞጣ ቅዱስ ጊዮርጊስ የሐዲሳትና የፍትሐ ነገሥት ጉባኤ ቤት መምህር በሆኑት መምህር ወልደ ትንሣኤ “ቸልተንነት” በሚል ርእስትምህርት ተሰጥቷል፡

dscn3740ብፁዕ አቡነ ቀውስጦስ የሰላሌና ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ባስተላለፉት መልእክት “ዛሬ ባየሁት ነገር በጣም ተደስቻለሁ፤ በእንደዚህ ያለ ሰፊ ጉባኤ ተገኝቼ አላውቅም፡፡ ሊቁ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ `በጉባኤ መካከል እያለን ብቻችንን የቆምን ይመስለናል` ይላል፡፡ እኔም ምንድነው ነገሩ፤ የት ነው ያለሁት እስክል ድረስ በመንፈሳዊ ተመስጦ ውስጥ ገብቼ ነበር፡፡ ማኅበረ ቅዱሳን በዚህ ታላቅ ገዳም ይህንን ታላቅ ጉባኤ በማድረጉ ምእመናን እምነታችሁን በሥራ እየተረጎማችሁት መሆኑን ያየሁበት ነው. . . ክርስቲያናዊ ሥራ እየሠራ ያለ ክርስቲያን መሥጋት የለበትም፡፡ ፈቃዱን እየፈጸሙ የሚያገለግሉ ሁሉ ነፍሳቸው በአደራ ጠባቂው በእግዚአብሔር እጅ ላይ ነው፡፡ ራሳችሁን ለእግዚአብሔር አደራ ሰጥታችሁ ክርስቲናዊ አገልግሎታችሁን እስከ መጨረሻው ድረስ እንድትፈጽሙ አደራ እላለሁ” ብለዋል፡፡

ብፁዕ አቡነ ማትያስ በሰጡት ቃለ ምእዳን “ልጅ አባቱ አይዞህ ካለው ካሰበው ሁሉ ነገር ላይ መድረስ ይችላል፡፡ በእግዚአብሔር ትእዛዝና ሕግ የሚጓዝ ብፁዕ ነው እንዳለው ቅዱስ ዳዊት የምንመካውም ኃይላችንም እግዚአብሔር ስለሆነ በርትታችሁ አገልግሎታችሁን ፈጽሙ” ብለዋል፡፡

“ወኩኑ ታቦተ መንፈሳዌ ለክህነት ቅድስት ወንጽሕት፤ ቅዱሳን ካህናት እንድትሆኑ መንፈሳዊ ቤት ለመሆን ተሠሩ” /፩ኛ ጴጥ. ፪፥፭/





ታኅሣሥ 14ቀን 2007 ዓ.ም.
መምህር ኅሩይ ባዬ
የዲያቆናት አለቃ የመጀመሪያው ሰማዕት ቅዱስ እስጢፋኖስ በሠላሳ አምስት ዓመተ ምሕረት በድንጋይ ተወግሮ ሰማዕትነትን ተቀበለ፡፡ ያን ጊዜም በክርስቶስ የባሕርይ አምላክነት አምነው ክርስቲያን የሆኑ የአይሁድ ወገኖች ተበተኑ፡፡

ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስም መከራ ውን ሳይሠቀቁ እምነታቸውን ጠብቀው በሃይ ማኖት እንዲጸኑ በስድሳ ዓመተ ምሕረት መጀ መሪያይቱን መልእክት ለተበተኑ ምእመናን ጽፎላ ቸዋል፡፡

ወኩኑ ታቦተ መንፈሳዌ ለክህነት ቅድስት ወንጽሕት፤ ቅዱሳን ካህናት እንድትሆኑ መንፈ ሳዊ ቤት ለመሆን ተሠሩ ሲል ሰማያዊ ጥቅም ከማያሰጥ ከክህነተ ኦሪት በተለየ ለክህነተ ወን ጌል መንፈሳዊ ማደሪያ ለመሆን ተዘጋጁ ማለቱ ነው፡፡ ቅድስት ማለቱም ምሳሌያዊ ከሆነው የኦ ሪት ክህነት ተለይቶ አማናዊ ክህነትን ለመ ያዝ የእግዚአብሔር ማደሪያ መንፈሳዊ ቤት ሆኖ መሠራት ስለሚያስፈልግ “ቅዱሳን ካህናት እንድትሆኑ መንፈሳዊ ቤት ለመሆን ተሠሩ” እያለ ይጽፋል፡፡

በዚህ ትምህርታዊ ስብከት ካህን የሚለውን ቃል በመተርጐም የካህናትን ተልእኮ በማመልከት የሓላፊነቱን ታላቅነትና ክቡርነት እንመለከታለን፡፡ በሁለተኛው ክፍልም ክህነት ከእግዚአብሔር የተቀበልነው፣ የታደልንለት እና የተጠራንለት አደራ በመሆኑ ሥልጣነ ክህነታችንን ጠብቀን ራሳችንን፣ ቤተ ክርስቲያናችንን፣ እምነታችንን፣ እና ምእመናንን እንዴት መጠበቅ እንዳለብን እንማራለን፡፡

“ተክህነ” የሚለው ቃል ተካነ አገለገለ ክህነትን ተሾመ /ተቀበለ/፤ በእግዚአብሔርና በሰዎች መካከል ቆሞ ለማገልገል ካህን ተባለ የሚለውን ትርጓሜ ያመለክታል፡፡ “ክሂን” ከሹመት በኋላ ማገልገልን፤ “ተክህኖ” ከማገልገል በፊት መሾምን የሹመትን ጊዜ የተቀበሉበትን ዕለትና ሰዓት ያሳያል፡፡

ክህነት ቢልም መካን ማስካን ካህንነት ተክኖ ማገልገልን ያሳያል፡፡ ካህን የሚለውን ቃል ሶርያ ውያን “ኮሄን”፣ ዕብራውያን “ካህን”፣ ሲሉት ዐረ ቦች ደግሞ ካህና በማለት ይጠሩታል፡፡ ካህን የሚ ለውን ቃል በቁሙ ቄስ ጳጳስ የእግዚአብሔር አገልጋይ የሕዝብ መሪ አስተማሪ መንፈሳዊ ሀብት ብለው አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ ይተረጉሙ ታል፡፡

እነዚህን የመዝገበ ቃላት ትርጓሜዎች እንደ ዋልታ አቁመን ጠቅላላ ትርጓሜ መስጠት ይቻ ላል፡፡ ክህነት “ተክህነ” አገለገለ ከሚለው የግእዝ ግስ ይወጣል፡፡ ክህነት የሥልጣኑ ስም ሲሆን አገልጋዮቹ ካህናት ይባላሉ፡፡ ክህነቱ የሚገኝበት መንፈሳዊ ምሥጢርም ምሥጢረ ክህነት ይባላል፡፡ በሚታይ የአንብሮተ እድ አገልግሎት የማይታይ የሥልጣነ ክህነት ሐብት ይገኝበታልና ምሥጢር የተባለበት ምክን ያትም በሚታይ አገልግሎት የማይታይ ጸጋ መንፈስ ቅዱስ ስለሚገኝበት ሲሆን ምሥጢረ ክህነትን የጀመረው /የመሠረተው/ ባለቤቱ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡

በክቡር ደሙ የዋጃትንና የመሠረታትን ቤተ ክርስቲያን እንዲያገለግሉ ካህናትን የለየ፣ የጠራና የሰየመ አምላካችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡ ቅዱሳን ሐዋርያት ከትንሣኤው በኋላ የመነሣቱን አዋጅ ለማብሰር ወደ ዓለም ሲላኩ በክህነታቸው ታላላቅ ተአምራትን አድርገዋል፡፡ /ማር. ፲፮፥፲፮/ ያስሩም ይፈቱም ነበር፡፡ /ማቴ. ፲፰፥፲፰/ ይህ የማሰርና የመፍታት ሥልጣን እስከ ኅልፈተ ዓለም የሚቀጥል መሆኑን አምላካችን በቅዱስ ወንጌል አስተም ሯል፡፡ /ማቴ. ፳፰፥፳/

ክህነት በቤተ ክርስቲያናችን አስተምህሮ ሦስት ደረጃዎች አሉት፡፡ እነርሱም ዲያቆን፣ ቄስ፣ ኤጲስ ቆጶስ በመባል ይታወቃሉ፡፡ የአንጾኪያው ሊቀ ጳጳስ ቅዱስ አግናጥዮስ እነዚህን ሦስት የክህነት ደረጃ ዎች እንዲህ በማለት ገልጿቸዋል፤ “ለእግዚአብሔር የሚገባችሁን ሁሉ ለማድረግ ፍጠኑ፤ የሚመ ራችሁ ኤጲስ ቆጶስ የእግዚአብሔር እንደራሴ ነው፡፡ ቄሱም እንደሐዋርያት ዲያቆናትም ለክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ባለአደራዎች ናቸውና”

በሌላ አገላለጥ ከሦስቱ ጾታ ምእመናን /ወንዶች፣ ሴቶችና ካህናት/ አንዱ ካህን ነው፡፡ ካህን ከወንዶችና ከሴቶች ምእመናን በተለየ ከፍ ያለ ሓላፊነት አለው፡፡ ይህ ሓላፊነት ምድ ራዊ ሳይሆን ሰማያዊ፤ ሥጋዊ ሳይሆን መንፈ ሳዊ ሓላፊነት ነው፡፡ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ አንድ ወጣት ቅስና ለመቀበል ፈልጐ ወደ እርሳ ቸው ሔደ፡፡ ቅዱስነታቸውም አሁን የምሰጥህ የክ ህነት ሥልጣን ሹመት ሳይሆን ሓላፊነት ነው በማለት ተናግረዋል፡፡

ሹመት ደረት ያቀላል፤ ሆድን ይሞላል፤ ሓላ ፊነት ግን ያሳስባል፣ ያስጨንቃል፣ እንቅልፍ ያሳ ጣል፣ ክህነት ሓላፊነት በመሆኑ አንድ ካህን ሳይ ታክትና ሳይሰለች በጸሎት በጾምና በስግደት ስለ ራሱ ኃጢአት እና ስለ መንፈሳዊ ልጆቹ ክርስቲ ያናዊ ሕይወት ስለሚጨነቅ ምንጊዜም ቢሆን ዕረ ፍት የለውም፡፡ አምላካችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ “ግልገሎቼን አሠማራ፣ ጠቦቶቼን ጠብቅ፣ በጎቼን አሠማራ” /ዮሐ. ፳፩፥፲፮/ ብሎ ለካህናት የኖላዊነትን ሓላፊነት የሰጠበት የአደራ ቃልም እንደዋዛ የሚታይ አይደለም፡፡


ካህን ካህን ከመሆኑ አስቀድሞ ምእመናንን የማስተማር ብቃቱ፣ ቤተሰቡን የመምራት ችሎ ታው፣ የአንድ ሴት ባል መሆኑ፣ ቤተሰባዊ ሓላፊ ነቱን የመወጣት አቅሙ፣ ልጆቹን የማስተዳደር ክሂሎቱ እና ከሰዎች ጋር ያለው የሠመረ ግንኙ ነቱ ጤናማ ሊሆን እንደሚገባ ቅዱሳት መጻሕ ፍት ያስረዳሉ፡፡

ካህን ከሕይወቱ ሊያስወግዳቸው የሚገቡ ክፉ የሆኑ ጠባያትም በመጽሐፍ ተዘርዝረዋል፡፡ ካህን ለብዙ የወይን ጠጅ የማይጎመጅ /የማይ ሰክር/፣ በሁለት ቃል የማይናገር፣ ከፍቅረ ንዋይ የራቀ፣ አጥብቆ ገንዘብን የማይወድ፣ በንጹሕ ሕሊና የሃይማኖትን ምሥጢር የሚጠብቅ፣ ግልፍተኛ ያልሆነ፤ ሊሆን ይገባዋል፡፡ በአንጻሩም ትሑት፣ የማይጋጭ፣ ይቅር የሚል፣ ትዕግሥተኛ የሆነ እንደሆነ ለሚመራቸው ምእመናን ትክክለኛ አርአያ መሆን ይችላል፡፡

ካህናት በሐዋርያት መንበር ተቀምጠው የማሠርና የመፍታትን ሓላፊነት ይወጣሉ፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንደጻፈልን “ካህናት በምድር የፈጸሙትን ጌታ በሰማይ ያጸናላቸ ዋል፤ የባሮቹን /የካህናትን/ አሳብ ጌታ ይቀበለ ዋል” በመሆኑም ካህናት በምድር ላይ የሚፈጽሙአ ቸውን ምሥጢራት እግዚአብሔር በሰማያዊ ምሥ ጢር ተቀብሎ ያከብራቸዋል፡፡
ኤጲስ ቆጶሳት መዓርገ ክህነቱን ለሚመለከ ታቸው ወገኖች ከመስጠታቸው በፊት የቅድ ሚያ ጥንቃቄ ሊያደርጉ እንደሚገባ፤ ምእመናንም በጉዳዩ ላይ አሳብና አስተያየታቸውን ለኤጲስ ቆጶሱ ቢናገሩ መልካም እንደሆኑ የሚደነግጉ መጻ ሕፍት አሉ፡፡ ስለሆነም

ካህኑ ከመሾሙ በፊት፡-

1. የሃይማኖትን ምሥጢር ጠንቅቆ የሚያውቅ መሆን እንዳለበት ሐዋርያት በጉባኤ ኒቅያ ደንግገዋል፡፡ /ጉባኤ ኒቅያ ፫፻፳፭ ቀኖና ፲፱/
2. አዲስ አማኒ ያልሆነ /ጉባኤ ኒቅያ ፫፻፳፭ ቀኖና ፪-፱/
3. የመንፈስ ጤንነት ያለው /የሐዋ. ቀኖና ፸፰/
4. ዕድሜው ከሠላሳ ዓመት ያላነሰ፤ ሊሆን እንደ ሚገባ /ስድስተኛው ሲኖዶስ ቀኖና ፲፫/ በግልጥ ያስቀምጣል፡፡

የካህናት ተልእኮ

የኤጲስ ቆጶሳት ተልእኮ ቀሳውስትን እና ዲያቆናትን ይሾማሉ፣ ያስተምራሉ፣ ያጠምቃሉ፣ ያቆርባሉ፡፡ በሀገረ ስብከታቸው ያሉት ምእመናን ማኅበራዊና መንፈሳዊ ችግር ሲደርስባቸው ይመክ ራሉ፣ ያጽናናሉ “ሕዝቡን ጠዋትና ማታ ለነግህና ለሠርክ ጸሎት በቤተ ክርስቲያን ይገኙ ዘንድ” ያዝዟቸዋል፡፡

የቀሳውስት ተልእኮ፡- እንደ ኤጲስ ቆጶሱ ያስተ ምራሉ፤ ያጠምቃሉ፣ ያቆርባሉ፡፡

የዲያቆናት ተልእኮ፡- ለኤጲስ ቆጶሱና ለካህኑ ይላላካሉ፤ ምሥጢራትን ግን የመፈጸም ሓላፊነት የላቸውም፡፡
ከእነዚህ መሠረታዊ የክህነት ደረጃዎች ሌላ በቤተ ክርስቲያን የሚታወቁ መዓርጋት አሉ፡፡ እነርሱም ንፍቅ ዲያቆን፣ አንባቢ /አናጉንስጢስ/ መዘምር፣ ኀፃዌ ኆኅት /በረኛ/ በመባል ይታወቃሉ፡፡ ንፍቅ ዲያቆን ዋናውን ዲያቆን ይረዳል፡፡ አንባቢ /

አናጉንስጢስ/ በቅዳሴ ጊዜ መልእክታትን ያነብ ባል፡፡ መዘምር ደግሞ የመዝሙር አገልግሎት ይሰጣል፡፡ ኀፃዌ ኆኅት ቤተ ክርስቲያንን ይጠር ጋል፣ ያጸዳል፣ ያነጥፋል፣ ደወል ይደውላል፣ በጸሎት ጊዜ ቤተ ክርስቲያንን ይከፍታል ይዘጋል፡፡
ከእነዚህ የተቀብዖ ስያሜዎች ውስጥ ፓትር ያርክ የሚባለው መዓርግ ከሊቃነ ጳጳሳት መካከል ለአንዱ በፈቃደ እግዚብሔር በምርጫ ይሰየ ማል፡፡

ይህ የመዓርግ ስም የተጀመረው በአምስተ ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ሲሆን በዚህ የመዓርግ ስም ይጠሩ የነበሩት የሮም፣ የእስክንድርያና የአን ጾኪያ ታላላቅ ከተሞች አባቶች /መጥሮ ፖሊሶች/ ነበሩ፡፡ በኋላ ግን ራሳቸውን ችለው የሚተዳደሩ አገሮች ሁሉ የየራሳቸውን ፓትርያርክ ሹመዋል፡፡ ፓትርያርክ ማለት በግሪኩ ቋንቋ ርእሰ አበው /አባት/ ማለት ነው፡፡

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስ ቲያን ሥርዐት ሦስቱ ዐበይት የክህነት መዓርጋት ዲቁና ቅስና ኤጲስ ቆጶስ ናቸው፡፡ ንፍቀ ዲቁና አንባቢ፣ መዘምርና ኀጻዌ ኆኅት በመባል የሚታ ወቁት አራቱ ንኡሳን መዓርጋት በአገልግሎት ውስጥ በግልጽ የሚታዩና በዲቁና ወስጥ የሚጠ ቃለሉ መዓርጋት ናቸው፡፡
ሥልጣነ ክህነት የነፍስ ሕክምና አገልግሎት በመሆኑ ልዩ ጥንቃቄና ክብካቤ ያሻዋል፡፡ ሥልጣነ ክህነት በዘመድ፣ በዘር፣ በአገር ልጅነት በገንዘብ አይሰጥም፡፡ ለመሾም ተብሎም እጅ መንሻ መስ ጠትና መቀበል ፈጽሞ የቤተ ክርስቲያን ትው ፊት፣ ሥርዐትና ቀኖና አይደለም፡፡

የካህናትን ክብር ካስተማሩን አበው መካከል አንዱ ቅዱስ አትናቴዎስ በቅዳሴው “ኦ ካህናት አንትሙ ውእቱ አዕይንተ እግዚአብሔር ብሩሃት ተናጸሩ በበይናቲክሙ አሐዱ ምስለ ካልዑ፤ ካህ ናት ሆይ ብሩሃን የእግዚአብሔር ዓይኖች እናንተ ናችሁ እርስ በርሳችሁ አንዱ ካንዱ ጋራ /ተያዩ/ ተመለካከቱ” ይላል፡፡ ይህም በችግሮቻችን ዙርያ መወያየት፤ መነጋገርና መደማመጥ የሚያስፈልግ መሆኑን ያስረዳናል፡፡

“የኩነኔ አገልግሎት ክብር ከሆነ ይልቅ የጽድቅ አገልግሎት በክብር አብዝቶ ይበልጣልና” /፪ኛ ቆሮ. ፫፥፱/ እንዳለው ሐዋርያው የክህነት አገልግሎት የተለየ እና ክቡር መሆኑን መገንዘብ ይገባል፡፡ ክህ ነት ከእግዚአብሔር የተገኘ መሆኑ ብቻ ሳይሆን ወደ እግዚአብሔርም የሚያደርስ ታላቅ መሰላል ነው፡፡

የሥርዐተ ጥምቀት፤ የሥርዐተ ቁርባን፤ የሥርዐተ ተክሊልና የምሥጢረ ንስሐ መፈጸሚያና ማስፈጸሚያ መንፈሳዊ መሣሪያ ሥልጣነ ክህነት መሆኑን ስንረዳ የምንሰጠው ክብርም የተለየ መሆኑ አያጠራጥርም፡፡ “ወወሀቦሙ ሥልጣነ ዘከማሁ ይእስሩ ወይፍትሑ ኲሎ ማእሠረ አመጻ፤ እንደ እርሱ የኃጢአትን ማሠሪያ ያሥሩና ይፈቱ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው” /ዮሐ. ፳፥፳፪-፳፫/ መዓርጉ ክቡር በመሆኑ አምላካችን ልዑል እግዚአብሔር ክቡር የሆነውን ክህነት አክብረን እንድንከብርበት መለኮ ታዊ ኃይሉ ይርዳን፡፡

2014 ዲሴምበር 11, ሐሙስ

ወእሙሰ ተአቅብ ኩሎ ዘንተ ነገረ ወትወድዮ ውስተ ልባ /እመቤታችን ግን ይህን ሁሉ ነገር ታስተውለው፤ በልቡናዋም ትጠብቀው ነበር፡፡/ሉቃ 2፡51/


ዲ/ን ታደለ ፈንታው
 መግቢያ
አስቀድመን መሪ ኃይለ ቃል አድርገን የተነሣንበት አንቀጽ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ በወንጌላዊው ቅዱስ ሉቃስ ላይ አድሮ የተናገው ቃል ነው፡፡  የእመቤታችን ፍቅር በውስጡ ጥልቅ መሆኑ፣ ነገረ ማርያም የገባው መሆኑ የተገለጠበት ፍካሬ ቃል ነው፡፡ የእርሷስ ፍቅር በሌሎች ሐዋርያትም ላይ አለ፤ በጎላው በተረዳው ለመናገር ያህል ነው እንጂ፡፡

በድርሳነ ኡራኤል ላይ እንደተገለጠው እመቤታችን በቤተ ዮሐንስ ሳለች ወንጌላዊው ከሚያስተምርበት ውሎ ሲመለስ እንደምን ዋልሽ አላት፤ እርሷ ግን አልመለሰችለትም፡፡ የጌታዬ እናት ለምን ዝም አለችኝ ብሎ አርባ ቀን ሱባዔ ያዘ፤ በአርባኛው ቀን መልአኩ ቅዱስ ኡራኤል ተገልጦ እመቤታችንን የልጅሽን ወዳጅ ዮሐንስን ለምን ዝም አልሺው አላት፤ እርስዋም ልጄ ወዳጄ ሰማያዊውን ምሥጢር እያሳየኝ አላየሁትም ነበር አለችው፡፡ የወንጌላውያን ነገር እጅግ ያስደንቃል፡፡

ቅዱስ ሉቃስ ከተነናገረው ገጸ ምንባብ አንዱን ቃል ብቻ ወስደን ብንመለከት ነገረ ማርያም ሊደረስበት የማይችል ሩቅ፣ ሊመረመር የማይችል ረቂቅ፣ ጥልቅ ሰማያዊ ምሥጢር የተቋጠረበት መሆኑን እንገነዘባለን፡፡ በሁለተኛው መቶ ክፍለ ዘመን የነበሩ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን የቅዱስ ሉቃስን ወንጌል ከተመለከቱ በኋላ የእመቤታችን የአሳብ ልዕልና  የተገለጠበት ወንጌል መሆኑን መስክረዋል፡፡ በዚህ ጽሑፍ አንዱን ሐረግ “ይህንን ሁሉ ነገር” የሚለውን እንመልከት፡፡

ነገር ምንድን ነው)
ነገር ብዙ ነገርን ያመለክታል፤ መጻሕፍት ነገር ሲሉ ልዩ ልዩ ምስጢራትን ያመለክታል፡፡ ለዓብነት ያህል የሚመለከተውን መመልከት ይገባል፡፡

1.    ነገር ምስጢር ነው፡፡
ለብዙ ሰው የማይነገር፣ አንድ ሰው በኅሊናው የሚይዘው፣ በልብ የሚደመጥ በአዕምሮ የሚነከር፣ ልመና፣ ርዳታ፣ ምሥጢር፣ ምሥክርነት፣ የርኅራኄ ሁሉ ቃል፣ ይህንና የመሳሰለው ሁሉ ነገር ይባላል፡፡ የአገራችን ሰው «አንድ ነገር አለኝ´ ሲል ሽምግልና ሊሆን ይችላል፤ ተግሳጽ ሊሆን ይችላል፤ ጥያቄ ሊሆን ይችላል፤ መልስ ሊሆን ይችላል፤ ቁጣ ሊሆን ይችላል፤ ምሕረት ሊሆን ይችላል፤ ቸርነት ሊሆን ይችላል፤ ይህንንና የመሳሰለው ሁሉ መደቡ ነገር ነው፡፡ ነገር ሰውየው በያዘው መጠን ይገለጣል፡፡ እግዚአብሔር በሰው ልቡና ውስጥ ያስቀመጠው ነገር ብዙ ነውና፡፡

2ኛ. ነገር በሰው ልቡና ውስጥ ያለ አሳብ ነው
የአገራችን ሰው አተያይን አይቶ፤ አካሄድን መርምሮ ይሄ ሰው ነገር ፈልጎኛል ይላል፡፡ ባለው ግንኙነት ላይ ተመሥርቶ ብቀላ ይሁን፣ ጥላቻ፣ መርገም ይሁን፣ ስጦታ፣ ወይም ሌላ፤ ባለው የፍቅር ግንኙነት ላይ ተመሥርቶም ይሁን ከዚህ ውጭ በአንድ ቋንቋ ተጠቃልሎ ነገር ብሎ ይጠራዋል፡፡

የቅዳሴ ማርያም ደራሲ አባ ሕርያቆስ ልቡናየ በጎ ነገርን አወጣ በማለት ድርሰቱን ይጀምራል፡፡ ያ በጎ ነገር በቅዳሴ ማርያም ውስጥ ተጠቃልሎ የቀረበ ነው፡፡ በዚያ ቅዳሴ ውስጥ ምን አለ) ወአነ አየድዕ ቅዳሴሃ ለማርያም አኮ በአብዝኆ አላ በአውኅዶ፡፡ ወአነ አየድዕ ውዳሴሃ ለድንግል አኮ በአንኆ በቃለ ዝንጋዔ አላ በአኅጽሮ ወአነ አየድዕ እበያቲሃ ለድንግል፡፡  እኔም የድንግልን ገናናነነቷን እናገራለሁ በማብዛት አይደለም በማሣነስ ቃል እንጂ ብሎ ነገረ ማርያምን፤ ወእቀውም ዮም በትሕትና  ወበፍቅር  በዛቲ ዕለት ቅድመ ዝንቱ ምስጢር  ብሎ ምስጢረ ቁርባንን፤ ኦ ማርያም በእንተዝ ናፈቅረኪ ወናዐብየኪ  እስመ ወለድኪ ለነ መብልዐ ጽድቅ ዘበአማን ወስቴ ሕይወት ዘበአማን፤ ማርያም ሆይ የሕይወት መብልን የሕይወት መጠጥን ወልደሽልናልና ከፍ ከፍ እናደርግሻለን በማለት /ምስጢረ ስጋዌን / ነገረ ቅዱሳንን፣ ተልእኮ ሐዋርያትን፣ ምልጃ ጳጳሳትን፣ ነገረ ሊቃውንትን፣ ሃይማኖተ ሠለስቱ ምእትን፣ ሃይማኖታቸው የቀና ቀሳውስትን፣ ዲያቆናትን፣ ደናግልን፣ መነኮሳትን ፣ መኳንንትን ፣ መሳፍንትን፣ በቀናች ሃይማኖት ያረፉ አበውንና እመውን፣ የሃይማኖት አርበኞችን አዳምን፣ አቤልን፣ ሴትን፣ ሄኖክን፣ ኖኅን ሴምን፣ አብርሃምን፣ ይስሐቅን፣ ያዕቆብን፣ ዮሴፍን፣ ሙሴን፣ አሮን ካህንን፣ ጌዴዎንን፣ ኢያሱ መስፍንን፣ እሴይን፣ አሚናዳብን፣ ሰሎሞን፣ ኤልያስን፣ ኤልሳዕ ነቢይን፣ ኢሳይያስን፣ ዳንኤልን፣ ዕንባቆምን፣ ሕዝቅኤልን፣ ሚክያስን፣ ሲሎንዲስን፣ ናሖምን፣ ዘካርያስን፣ ያነሣበትን ቃል በመጠቅለል ነገር በማለት ይጠራዋል፡፡ በዚህ የቅዳሴ ቃል ምስጢረ ሥላሴ አለ፡፡

ነቢየ እግዚአብሔር ዳዊትም አስቀድሞ ልቡናየ በጎ ነገርን አወጣ ብሎ ነበረ፡፡ በመዝሙረ ዳዊት ስለ ጽድቅ፣ ስለ ክብርና አሳር፣ ስለ ፍቅርና ጥላቻ፣ ስለ ዘላለም ጽድቅና ኩነኔ፣ ስለ ክፋትና በጎነት፣ ስለ መልካምነትና ክፋት፣  ስለ ምሥጢረ ሥላሴ፣ ምሥጢረ ሥጋዌ ፣ ምሥጢረ ጥምቀት፣ ምሥጢረ ቁርባን ፣ ምሥጢረ ትንሣዔ ሙታን፣ ሁሉ ተጠቅልሎ ቀርቧል ይህ ሁሉ ምሥጢር በአንድነት ተጠቃልሎ ነገር ይባላል፡፡

3ኛ. ነገር ታሪክ ነው፡፡
መጽሐፍት ነገር ሲሉ ታሪክ ማለታቸው ነው፡፡ ነገረ ማርያም፣ የእመቤታችን ታሪክ የተጠቀለለበት መጽሐፍ ነው፡፡ ነገረ ክርስቶስ የክርስቶስን ነገር የሚናገር፤ ነገረ ሥላሴ የሥላሴን ነገር የሚናገር፣ ነገረ መላእክት፣ እንዲህ እያልን የምንናገረው ነገር ታሪክን የሚናገር ነው፡፡

4ኛ. ነገር ምስጢር ነው
ምሥጢር ብዙ ወገን ነው፡፡ የሚነገርና የሚገለጥ አለ፤ የማይነገርና የማይገለጥ አለ በአንድነት ተጠቃልሎ ነገር በማለት ይጠራል፡፡ ምሥጢር ለሁሉም ወገን አይነገርም፤ ለምሳሌ የሃይማኖት ምሥጢር በእምነት ለተጠሩ፣ ሰማያዊውንና መንፈሳዊውን ነገር ለሚረዱ፣ ከሥጋ ፈቃድና አሳብ በላይ ለሆኑ እንደ መንፈስ ፈቃድ ለሚመላለሱ ወገኖች እንጂ ለሁሉ ሰው የሚነገር አይደለም፡፡ ምሥጢር የማይነገረው በሚከተሉት ዓበይት ምክንያቶች ነው፡፡

ሀ. የሚሰጠው ጥቅም ከሌለ አይነገርም፡፡
ለ. የሚቀበለው ሰው አቅም ከሌለው አይነገርም፡፡
ሐ. ተናጋሪውና ሰሚው በእርግጠኝነት የማይደርሱበት ከሆነ አይነገርም፡

ልደተ ወልድ እም አብ ምጽአተ መንፈስ ቅዱስ እም አብ ኢይትነገር አላ ይትነከር፡፡ የወልድ ከአብ መወለድ፤ የመንፈስ ቅዱስ ከአብ መሥረጽ ይደነቃል እንጂ አይነገርም፡፡ ይህ ሁኔታ በሊቃውንት ውስጥ የሚኖር ነው፡፡ ይሄንን የሚመስል ሌላም ነገር አለ፡- በሦስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን የነበረ  የቆጵሮስ  ሊቀጳጳስ ቅዱስ ኤጲፋንዮስ ሦስቱ በእግዚአብሔር የዝምታ ሸማ የተጠቀለሉ ድብቅና ጣፋጭ ምሥጢራት በማለት የሚገልጣቸው ነገሮች አሉ እነርሱም የሚከተሉት ናቸው፡፡

1.    የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዘላለማዊ ድንግልና
2.    አማኑኤል ጌታን መውለዷ
3.    የማይሞተው አምላክ ሞት ናቸው፡፡

አስቀድመን ካነሣነው ነገር ተነሥተን የምንደርስበት ድምዳሜ አለ እርሱም በመጠን የሚነገር ፣ በመጠን የማይነገርና ፈጽሞ የማይነገር፣ መኖሩን ነው፡፡ ፈጽሞ የማይነገረው ነገር ምክንያቱ መጠኑና ልኩ ስለማይታወቅ ነው፡፡ በመጠን የሚነገር ያልነው በሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤልና የጌታ እናት በምትሆን በቅድስት ድንግል ማርያም መካከል የነበረውን ዓይነት ነገር ነው፡፡ ቅድስት ድንግል መልአኩን ሴት ያለ ወንድ ምድር ያለ ዘር ታብቅል የሚለውን ጥያቄ ከየት አገኘኸው ብላ በጠየቀችው ጊዜ የቅዱስ ገብርኤል መልስ የተነገረው በመጠን ነው፡፡ እርሱም «ለእግዚአብሔር የሚሣነው ነገር የለም ´ የሚል ነው፡፡

መልአኩ ከዚህ በላይ መሄድ አልፈለገም፡፡ ሥጋዊ ባሕርይ ሌላ መለኮታዊ ባሕርይ ሌላ ነው፤ በሊቃውንት የሚተነተነው ነገር የሚደነቅ እንጂ የመለኮትን ባሕርይ የሚገልጥ አይደለም፡፡ የተሸፈነ ምሥጢር አለ ሰው ሊረዳው የማይችል፣ የማይገነዘበው ምሥጢር፣ እጹብ እጹብ በማለት የሚያደንቀው ምሥጢር፡፡ አሁን ወደ ዋናው ነገር እንምጣ፡-
እናቱም ይህን ነገር ሁሉ ትጠብቀው ነበር አለ ወንጌላዊው፡፡ ወንጌላዊው ይህን ሁሉ ነገር በማለት የተናገረው ነገር ምንድን ነው)

ይህን ሁሉ ነገር
    ከቤተ መቅደስ ይጀምራል፡፡ አስቀድሞ በቤተ እሥራኤል ደናግል በቤተ መቅደስ የሚቀመጡበት ልማድ አልነበረም፡፡ በርግጥ በኦሪቱ ነቢይት በቤተ መቅደሱ ታዛ ነበረች፡፡ የነቢይቱ በቤተ መቅደስ መኖርና የአምላክ እናት በቤተ መቅደስ መኖር ይለያያል፡፡ ነቢይቱ በቤተ መቅደስ የነበረችው በራሷ ምርጫ ስለ ራሷ ኃጢአት ተገብታ ነው፤ ቅድስት ድንግል ማርያም ግን በአምላክ ምርጫ ነው፡፡ ነቢይቱ በምናኔ ነው፤ እመቤታችን ግን ካህናቱ ተቀብለው መላእክት ምግቧን አቅርበው ነው፤ ስለዚህም ነው አባ ሕርያቆስ ኦ ድንግል አኮ ኅብስተ ምድራዌ ዘተሴሰየኪ አላ ኅብስተ ሰማያዌ እምሰማየ ሰማያት ዘበሰለ፡፡ ኦ ድንግል አኮ ስቴ ምድራዊ  ዘሰተይኪ፤ አላ ስቴ ሰማያዊ እምሰማየ ሰማያት ዘተቀድሐ፡፡ ድንግል ሆይ ምድራዊ ኅብስትን የተመገብሽ አይደለም ከሰማየ ሰማያት የተገኘ ነው እንጂ፡፡ ድንግል ሆይ ምድራዊ መጠጥን የጠጣሽ አይደለም ከሰማየ ሰማያት የተቀዳ ነው አንጂ፡፡ በማለት የሚያመሰግናት፡፡ ይህንን ሁሉ ነገር በልቡናዋ ትጠብቀው ነበር፡፡

     ዐሥራ አምስት ዐመት ሲሞላት አይሁድ በምቀኝነት ከቤተ መቅደሳችን ትውጣልን አሉ፡፤ ልማደ አንስት በእርሷ እንደሌለ እያወቀች ንጽሕናዋን አልተከላከለችም፤ አልተቃወመችም እኔ እንዲህ ነኝ፣ እንዲያ ነኝ አላለችም፡፡ ቤተ መቅደሱን ለቃላቸው ወጣች ይህን ሁኔታ የሚያውቀው ወንጌላው ጥቅልል አድርጎ ይህንን ሁሉ ነገር በማለት ገለጠው፡፡

    በድንግልና ተወስና አምላኳን ለማገልገል ቁርጥ ኅሊና ኖሯት ሳለ የዐሥራ ሁለቱ ነገደ እሥራኤል በትር ተሰብስቦ ተጸልዮ ዕጣው ለዮሴፍ ወጥቶ ወደ ዮሴፍ ቤት መሄዷን አልተቃወመችም፡፡  በኅሊናዋ ታሰላስለው ነበር፤ ጥያቄ አንስታ አታውቅም፤ ይህን ሁሉ ነገር  በአንክሮ ትከታተለው ነበር፡፡

    የመልአኩ ብስራት ትጸንሲ ሲላት  በድንግልና ለመኖር የወሰነች ስለነበረች ይህ አንዴት ዓይነት ሰላምታ ነው ብላ አሰበች፤ መልአኩ በድንግልና ጸንሳ በድንግልና እንደምትወልድ ሲነግራት እንደቃልህ ይደረግልኝ እኔ የእግዚአብሔር ባሪያው ነኝ ያለችውን ነገር ሁሉ በልቡናዋ ትጠብቀው ነበር፡፡

    ከጸነሰች በኋላ ዮሴፍ  መኑ ቀረጸ አክናፈ ድንግልናኪ ብሎ በጠየቃት ጊዜ መልአኩ ገብርኤል አክብሮ ከነገረኝ ነገር በስተቀር ሌላ እንደማላውቅ እግዚአብሔር ያውቃል  የሚለውን ነገር ሁሉ በልቡናዋ ትጠብቀው ነበር፡፡

    ከዚያም በኋላ በቤተልሔም አማኑኤል ጌታን ስትወልድ እንስሳት ሲያሟሙቁት፣ እረኞች ሲያገለግሉት፣ ነቢይቱ ሐና ስታመሰግነው፤ ስምዖን በቤተ መቅደስ ስለ ሕፃኑ ትንቢት ሲናገር ይህ ለብዙዎች ለመውደቃቸውና ለመነሣታቸው ምልክት ሆኖ ተሾሟል፤ በአንቺም በነፍስሽ ሰይፍ ያልፋል ሲላት ይህንን ሁሉ ነገር በልቡናዋ ትጠብቀው ነበር፡፡

    በስደቱ ጊዜ የደረሰበትን መከራ፣ ረሃቡን፣ ጽሙን፣ ድካሙን በመንገዷ ሁሉ የፈሰሰውን የሕፃናት ደም እየተራመደች ልጇን ይዛ መሰደዷን በልቡናዋ ትጠብቀው ነበር፡፡ ከዚህ ሁሉ ጉድ እንዴት እንዳወጣት በስደቷ ጊዜ የሽፍታ ባህታዊ አዘጋጅቶ እንዴት ልጇን ተቀብሎ እንዳሻገረላት፣ ደንጋዮች ታንኳ ሆነው እንዴት ባሕርን እንዳሻገሯት  ታስተለው ነበር፡፡ ልጇን ልተተ ሕፃናት ፈጽሞ እንዴት እንዳደገ፣ በነፋስ አውታር በደመና ዐይበት ውኃ ቋጥሮ እንዴት እንዳገለገላት፤ ልጇ በፀሐይ በነፋስ አውታር እንዴት እንደተራመደ እየተመለከተች ይህንን ሁሉ ነገር በልቡናዋ ትጠብቀው ነበር፡፡

     በዐሥራ ሁለት ዓመቱ በሊቃውንት መካከል ተገኝቶ ሲከራከር ሊቃውንቱን ሲያስደምም ታስተውለው ነበር፡፡

    ከሊቶስጥራ እስከ ጲላጦስ አደባባይ ከዚያም እስከ ቀራንዮ አደባባይ የተፈጸመበትን ነገር ሁሉ ታስተውለው ነበር፤ ይህ ሁሉ ተጠቅልሎ ለእርሷ ነገር ነበር፡፡ ይሄንንና የመሳሰለውን ነው ወንጌላዊው ቅዱስ ሉቃስ እናቱም ይሄንን ሁሉ ነገር በልቧ ትጠብቀው ነበር በማለት የገለጠልን፡፡ ልመናዋ ክብሯ የልጇም ቸርነት ይደርብን አሜን፡

                                   በአውሮጳ   የካህናት አንድነት ማኅበር ሊቋቋም መሆኑ ታወቀ በ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከመላዋ አውሮጳ   የተውጣጡ ካህናት፡” የ...