2015 ኤፕሪል 23, ሐሙስ

ተዋሕዶ-በደም

ሚያዝያ 14ቀን 2007ዓ.ም
መምህር ሳሙኤል ተስፋዬ
0000000000በደም ተመሥርተሽ
በደም ተገንብተሸ
በደም ተዋሕደሽ
በደም ተሰራጭተሸ
ደሙ ብርሃን ሆነን ከጨለማም ወጣን ፡፡
ተዋሕዶ
በደም አጥምቀሽን
በደም አጽንተሸን
ከጌታችን ጋራ አንድ አካል አረግሽን፡:
ተዋሕዶ
በደሙ አክብረሽን
በደሙ አስታርቀሽን
ደሙን ከካሰልን
የደሙን ማኅተም ኃይሉን ተጎናጸፍን፡፡

ተዋሕዶ
በደም ተገዝቼ
በደሙም ነጽቼ
በደሙ ጸንቼ
ኖርኩኝ ረክቼ ደሙን ጠጥቼ ፡፡

ተዋሕዶ
ለዓለም በፈሰሰው ደሙ
ምልክት ዓርማዬ ሲሆን ማኅተሙ
ነብር ዝንጉርጉርነቱን መለወጥ እንዳይችል መልኩን
እንዴት በመከራ አላውቀውም ልበል?

ተዋሕዶ
ደሙ ይጠራኛል ጽና በርታ እያለ
ምልከት በልቤ ታትሞ ስላለ፡፡
እንዴት ልበጥሰው አላውቅም ልበለው?
መንፈሱ አጽንቶ መንፈሱ ካገዘኝ፡፡
የቀድሞ ማንነት በደሌን ሳያየው
በማተቤ አጸናኝ ለመንግሥቱ አበቃኝ፡፡

ለሰማእታቱ በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ጸሎተ ፍትሐት ተካሔደ፡፡


ሚያዝያ 15 ቀን 2007 ዓ.ም.
001tselote fitat002tselote fitat004tselote fitat003tselote fitat
ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በሊቢያ ለተሰዉት ክርስቲያኖች ቀኖናው በሚፈቅደው መሠረት በቅርቡ የሰማእትነትን ክብር እንደምትሰጥ አሰታወቀች
ቅዱስ ጳትርያርኩ፤ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፤ የመንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣናትና የግብጽ አምባሰደር፤ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፤ የሰማእታቱ ቤተሰቦችና ምእመናን በተገኙበት ጸሎተ ፍትሐቱ ተከናውኗል፡
በጸሎተ ፍትሐቱ ላይ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፤ የሰንበት ትምህርት ቤቶች መዘምራን ሰማእታቱን አስመልከቶ ያሬዳዊ ዝማሬ አቅርበዋል፡፡

ቅዱስ ፓትርያርኩ ያስተላለፉትን መልእክት ቀጥሎ እናቀርባለን፡፡

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፡፡ አሜን!
ዘሰ አምነኒ በቅድመ ሰብእ አነኒ አአምኖ በቅድመ አቡነ ዘበሰማያት
በሰው ፊት ያመነኝን ሰው እኔም በሰማያዊ አባቴ ፊት አምነዋለሁ
የቅዱስ ማቴዎስ ወንጌል 10*32
ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት 
የተከበራችሁ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፣ 
የሰንበት ትምህርት ቤቶች አባላት ወጣቶች
ምእመናንና ምእመናት
ቤተ ክርስቲያን ከተመሠረተችበት ጊዜ ጀምሮ መሥዋዕትነት አብሯት የኖረ ታሪክ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንም በልዩ ልዩ ዘመናት ልጆቿ በግፍ ተገድለው ሰማዕትነትን ተቀብለዋል፡፡

በስድስተኛው ክፍለ ዘመን በናግራን፣ በዘጠነኛው ክፍለ ዘመን በዮዲት ጉዲት፣ በዐሥራ አምስተኛው ክፍለ ዘመን በግራኝ አሕመድ፣ በዐሥራ ዘጠነኛውና ሃያኛው ክፍለ ዘመን በውጭ ወራሪ ኃይሎች በርካታ የሰማዕትነት ታሪኮች አልፈዋል፡፡

ይሁን እንጂ በሁሉም ዘመን የተነሡባት አሳዳዶችና ገዳዮች ከነታሪካቸው ሲጠሩ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በአምላኳ ጥበቃና በልጆቿ ጽናት ሰማዕታቷን አክብራ ለሰው ልጅ መንፈሳዊ ሀብትን እያደለች አሁንም አለች ወደፊትም ትኖራለች፡፡

ዛሬ እነዚህ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ወጣቶች በጠባቡ በር ተጉዘው በደማቸው ማሕተም ወደ መንግሥተ ሰማያት የገቡ የሃያ አንደኛው ክፍለ ዘመን የክርስትና እምነት ጽኑ ምስክሮች ናቸው፡፡

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስም ለእነዚህ ልጆቻችን ቀኖና ቤተ ክርስቲያን በሚፈቅደው መሠረት የሚገባውን የሰማዕትነት ቀኖና ሥነ ሥርዓት በቅርቡ በማከናወን ለመላው ዓለም ያሳውቃል፡፡

ስለዚህ የክርስቶስ ቤተሰቦች የሆናችሁ ክርስቲያኖች ሁሉ በዚህ አረመኔያዊ ወንጀል ሳትደናገጡ አሸባሪነትን በአንድነት ሆናችሁ በማውገዝና በመከላከል የተጀመረውን ተቃውሞ ትርጉም ባለውና አፋጣኝ በሆነ መንገድ ልንፈጽመው እንደሚገባ ማሳሰብ እንወዳለን፡፡

005tselote fitat006tselote fitat007tselote fitat10tselote fitat
የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን
አሸባሪነት ሃይማናት የለውም፣ በዕውቀትና በበሳል አእምሮ የሚከናወን ተግባርም አይደለም፣ የድርጊቱ ፈጻሚዎችም የተረጋጋ ሥነ ልቦና ያላቸው ሊሆኑ አይችሉም፡፡ ብሶት ያለባቸው ሰዎች እንደሚያደርጉት ያለ የነፃነት ትግልም አይደለም፡፡

ነገር ግን በፍጹም ራስ ወዳድነትና ጭካኔ ላይ የተመሠረተ አስነዋሪ ወንጀል ነው፡፡ የአይ ኤስ አሸባሪዎች የፈጸሙት ወንጀል የሃያ አንደኛው ክፍለ ዘመን ትውልድ አስተሳሰብን የማይወክልና የሰውን ልጅ ተፈጥሮአዊ ባህርይ የጣሰ ተግባር ነው፡፡

ይህንን አስነዋሪ ግፍ ክርስቲያኖችና የሌላ እምነት ተከታዮች ብቻ ሳይሆኑ ሰው የሆነ ፍጡር ሁሉ ሊያወግዘውና ሊጸየፈው የሚገባ ተግባር ነው፡፡ እነዚህ ሰዎች የፈጸሙት ተግባር በራሳቸው ላይ ቢፈጸምና በጤናማ ሥነ ልቦና ቢያዩት ኖሮ በወጣቶቻችን ላይ በፈጸሙት ተግባር ልክ እንኳ ቢከፈላቸው እንደማይበቃ አድርገው በራሳቸው ላይ ይፈርዱ ነበር፡፡

ዛሬ የሰው ልጅ በተፈጥሮ ለሚመስሉት ወገኖቹ ሕይወት፣ ምቾትና ሰላም ደፋ ቀና በሚልበት ዓለም ከሰው የተፈጠሩ የማይመስሉ አረመኔዎች ክቡር የሆነ የሰውን ልጅ ነፍስ ኢሰብኣዊ በሆነ መንገድ ሲቀጥፉ መታየት ምን የሚሉት እምነት ነው?

ይህን አስነዋሪና ከሰው ተራ የሚያወጣቸውን ተግባርስ የወጣቶቹ ወላጆች ሳይቀሩ ዓለም ሁሉ በሚመለከተው ሚዲያ ማሳየት ምን የሚሉት ጭካኔ ነው?

የሰውን ልጅ የቀድሞ ታሪክ አጥፈቶ አዲስ የግፍና የኢሰብኣዊነት ታሪክ ለመሥራት መጣጣርስ ምን የሚሉት አስተሳሰብ ነው?

ስለዚህ አይ ኤስን ጨምሮ በሰብአዊ ፍጡር ሉዓላዊ ክብር ላይ የተቃጣ የአሸባሪነት ወንጀል ያልምንም ቅድመ ሁኔታ ከምድራችን ሊወገድ የሚገባው እኩይ ግብር ነው፡፡ ከዚህ አንጻር ራሳቸውን አይ ኤስ ብለው የሚጠሩት አሸባሪዎች ከዕውቀትና ከሃይማናት የወጡ፣ የልማትና የሰው ልጅ ሰላማዊ ሕይወት ሥጋቶች የሆኑ ቡድኖች በመሆናቸው ዓለም በአንድነት ተባብሮ ሊያቆማቸው ይገባል፣

ምናልባት ቡድኑን በገንዘብና በልዩ ልዩ መንገድ ድጋፍ የሚያደርጉ ግለሰቦችና ተቋማት ካሉም የጥፋት ተባባሪ ከመሆን ሊታቀቡ ይገባል፣

ቅድስት ቤተ ክርስቲያንም ለፈጸሙት ወንጀል በነፍሳቸውና በኅሊናቸው ከሚመጣባቸው ዘለዓለማዊ ፍርድ ይድኑ ዘንድ ንሥሓ እንዲገቡ ጥሪዋን ታስተላልፋለች፡፡

የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት
ቀደም ሲል እንደገለጽነው በመንፈሳዊ ሕይወት ከምናገኘው ዋጋ ሁሉ የሰማዕትነት ዋጋ ተወዳዳሪ የለውም፣

በፍትሕ መንፈሳዊ ወሰማእታትሰ እሉ እሙንቱ ዘይቤ ክርስቶስ በእንቲሆሙ ዘሰ አምነኒ በቅድመ ሰብእ አነኒ አእምኖ በቅድመ አቡነ ዘበሰማያት፣ ወለእመተሳተፍክምዎሙ በጊዜ ኅዘናቲሆሙ ይከውን ለክሙ ስምዕ በእንተ ጻሕቀ ኅሊናክሙ፡፡

ሰማዕታት ማለት እኔን በሰው ፊት ያመነኝን ሰው እኔም በሰማያዊ አባቴ ፊት አምነዋለሁ ብሎ ክርስቶስ ስለእነርሱ የተናገረላቸው ናቸው፡፡ እነዚህን በመከራቸው ጊዜ ብትመስሏቸው ስለ ቁርጥ ሓሳባችሁ ሰማዕትነት ይቆጠርላችኋል፡፡ የተባለላቸው ናቸው፤

ሰማዕታት ለሃይማኖታቸው ታማኞች ለመድኅኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ስም ደማቅ ምስክሮች ናቸው፤

ሰማዕታት በቅዱሳት መጻሕፍት ሥጋን የሚገድሉትን ነፍስን ግን መግደል የማይቻላቸውን አትፍሩ፤ ይልቁንስ ነፍስንም ሥጋንም በገሃነም ሊያጠፋ የሚቻለውን ፍሩ፤(ማቴ 10*28) የሚለውን ቃል ተቀብለው ምርጫቸው እግዚአብሔር መሆኑን በአደባባይ ያሳዩ ክርስቲያኖች ናቸው፡፡

ሰማዕታት የጥበብ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ነው በተባለው መሠረት የመንግሥተ ሰማያትን የክብር አክሊል በጥበብ ጀምረው በደማቸው ምስክርነት የተቀዳጁ ናቸው፡፡

ክብራቸውም አቡቀለምሲስ ዮሐንስ በራእዩ ምዕ 20 ቁጥር 4 ዙፋኖችንም አየሁ፤ በእርሱ ላይ ለተቀመጡትም ዳኝነት ተሰጣቸው፣ ስለኢየሱስም ምስክርና ስለ እግዚአብሔር ቃል ራሶቻቸው የተቆረጡባቸውን ሰዎችአየሁ ብሎ እንደተናገረው በእግዚአብሔር መንግሥት የማያልፍ አክሊልና የፍርድ ዙፋን የተዘጋጀላቸው ናቸው፡፡

ስለዚህ የእነዚህ ወጣቶች ልጆቻችን ቤተሰቦች የሰማዕታት ቤተሰቦች በመሆናችሁ ልትጽናኑ ይገባል፡፡
ቅድስት ቤተ ክርስቲያንም በደሙ የመሠረታት ወልደ እግዚአብሔር የልጆቿን ነፍስ በክብር እንዲቀበል ትጸልያለች፡፡
ልዑል እግዚአብሔር አምላካችን የልጆቻችንን ነፍስ በክብር ያሳርፍልን፣ ለመላው ዓለም ሰላምና መረጋጋትን ለቤተ ክርስቲያንና ለሰማዕታቱ ቤተሰቦች መጽናናትና ልዑል እግዚአብሔር አምላካችን የልጆቻችንን ነፍስ በክብር ያሳርፍልን፣ ለመላው ዓለም ሰላምንና መረጋጋትን ለቤተ ክርስቲያንና ለሰማዕታቱ ቤተሰቦች መጽናናትና ብርታትን ይስጥልን፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ!

አባ ማትያስ ቀዳማዊ 
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት
ሚያዝያ 15 ቀን 2007 ዓ.ም
አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ

‹‹ልጆቻችን፣ ማዕተቤን አልበጥስም፤ ወደ ሌላ አንለወጥም አሉ፤ በሰማዕትነታቸው ልንጽናናባቸው ልንማርባቸው እና ልናወድሳቸው ይገባል›› – የብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የማጽናኛ ቃለ ምዕዳን



the martyr daniel hadush
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፤ አሜን
፡፡
‹‹ኢትዮጵያዊ መልኩን ነብር ዝንጉርጉርነቱን ሊለውጥ ይችላልን? ልጆቻችን የምንኮራባቸው መጻሕፍቶቻችን፣ የምንማርባቸው ዩኒቨርስቲዎቻችን ናቸው፤ አስተምረውናል፤ አኩርተውናል፤ አስከብረውናል››
(ብፁዕ አቡነ ሉቃስ፤ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፤ የሰቲት ሑመራ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ)His Grace Abune Lukas
የልጆቻን የኃይለ ሚካኤል(ኢያሱ ይኵኖ አምላክ) እና የኃይለ ኢየሱስን(ባልቻ በለጠ) ነፍስ ይማርልን፡፡ እግዚአብሔር አምላካችን የሐዘን ዳርቻ ያድርግልን፡፡ እግዚአብሔር አምላካችን የቤተሰቡን ሕይወት፣ የቤተሰቡን ሐዘን በመልካም ነገር፣ በፍቅር ነገር ይለውጥልን፡፡ ቤተሰቡን ያለምልምልን፡፡ ቤተሰቡን ያጽናልን፡፡ ደግ ያልኾኑ ሰዎችን ወደ ደግነት፣ ወደ ምሕረት፣ ወደ ቸርነት ይመልስልን፡፡ ለዓለሙ ኹሉ ሰላም መረጋጋትን ያድልልን፡፡ አገራችን ኢትዮጵያን በክብር በረድኤት ይጠብቅልን፡፡
ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፤
የውድ ልጆቻችን የሰማዕታቱ፣ የታማኝ ልጆቻችን፣ የጀግኖች ልጆቻችን፣ በኢትዮጵያዊ ባህላቸው፣ በኢትዮጵያዊ ትውፊታቸው፣ በእምነታቸው፣ በሥርዐታቸው፣ በወጋቸው ጸንተው፣ ለማንም ሳይበገሩ እና ለማንም ሳይደለሉ፣ ለሌላ እጃቸውን ሳይሰጡ፣ ሳይቀለበሱ ጀግንነትን ያስተማሩ ልጆቻችን፣ መጻሕፍት የኾኑ ልጆቻችን ወላጆች እና እዚኽ የተሰበሰባችኹ ውድ ወገኖቼ፤
ከክርስቶስ ልደት በፊት ሰባት መቶ ዓመታት ቀድሞ የነበረው ነቢዩ ኤርሚያስ፣ በዚያን ጊዜዋ ባቢሎን በዛሬዋ ኢራቅ፤ በዚያን ጊዜዋ ፋርስ በዛሬዋ ኢራን እየዘዋወረ ባስተማረበት ዘመን ስለ ኢትዮጵያውን አድናቆት፣ ክብር፣ ጀግንነት፣ አይበገሬነት በትንቢቱ ምዕራፍ 13 ቁጥር 23 ላይ እንዲኽ ብሏል፡- ‹‹ኢትዮጵያዊ መልኩን ነብር ዝንጉርጉርነቱን ሊለውጥ ይችላልን?››
ኢትዮጵያዊ ባህሉን፣ ኢትዮጵያዊ እምነቱን፣ ኢትዮጵያዊ አንድነቱን፣ ኢትዮጵያዊ ጀግንነቱን፣ ኢትዮጵያዊ ትውፊቱን በሌላ ሊቀይር ይችላልን? አይቀየርም፡፡ ነቢዩ ሠቆቃው ኤርሚያስ በተባለ መጽሐፉም ይህን በስፋት እየገለጸ ይናገራል፡፡
libyan martyrs compiledውድ ወገኖቼ፤ ልጆቻችን እኮ ጀግኖች ናቸው፤ ልጆቻችን እኮ እጃቸውን አልሰጡም፤ ልጆቻችን እኮ አልተንበረከኩም፤ ልጆቻችን እኮ መጻሕፍቶቻችን ናቸው፤ ልጆቻችን እኮ አርበኞቻችን ናቸው፤ አልተማረኩም፤ የጀግና እናት አታለቅስም እንደተባለው ኹሉ፣ እናንተም የጀግኖች እናቶች ናችኹ፤ ልትኮሩ ይገባችኋል፤ ስማቸውን ለውጠው፣ ሃይማኖታቸውን ለውጠው፣ ሥርዐታቸውን ለውጠው፣ ተማርከው ቢኾን ኖሮ ነበር ማልቀስ የሚገባን፡፡
ውድ ወገኖቼ፤ የጀግኖች ወላጆች ናችኹና ልትኮሩ፣ ልትጽናኑ ይገባችኋል፡፡ እሰይ ልጄ፤ ተባረክ ልጄ፤ ለመንግሥተ ሰማያት ያብቃኽ ብላችኹ ልትመርቁ፣ ልትጸልዩ፣ ልትጽናኑ ይገባል፡፡ የመጽናኛ ዕለት ነው፤ ልጆቻችን አስተምረውናል፤ ልጆቻችን አኩርተውናል፤ ልጆቻችን አስከብረውናል፤ አስወድደውናል፤ በዓለም ደረጃ አገራችንን አስተዋውቀዋል፡፡
ውድ ወገኖቼ፤ እንዲኽ ላሉት ነው እንዴ የሚለቀሰው? አገር አጥፍቶ ለሔደ፣ በሙስና ተዘፍቆ ለሔደ፣ ሰክሮ ለሔደ፣ አመንዝሮ ለሔደ፣ ቀምቶ ለሔደ÷ ‹‹በምድር ኑሮው ተበላሽቶ፣ በሰማይ እንዴት ይኾን ከቶ›› ተብሎ የሚለቀስለት ለዚኽ ነው፡፡ ብዙ ልጆቻችን በየመልኩ ኸሉም አርበኛ ነው፡፡ አካሉን፣ ሕይወቱን፣ ወላጁን፣ ልጁን፣ ዘመኑን፣ ንብረቱን የሰጠ ስንት አለውድ ወገኖቼ፤ እንዴ፣ እነዚኽማ ልጆቻችን የምንኮራባቸው መጻሕፍቶቻችን ናቸው!! የምንማርባቸው ዩኒቨርስቲዎቻችን ናቸው ልጆቻችን!! ብርሃናችን ናቸው ልጆቻችን!! ማዕተቤን አልበጥስም፤ ወደ ሌላ አንለወጥም፤ አንበገርም አሉ፤ ይኼ ነው ወይ የሚያስለቅሰው? የሚለቀስበትን ነገር እንወቅ እንጂ!
ውድ ወገኖቼ፤ ስለዚኽ ልጆቻችንን በሰማዕትነታቸው፣ በጀግንነታቸው ልናከብራቸው፣ ልንማርባቸው፣ ምሳሌአቸውን ልንወስድ፣ ልናወድሳቸው ይገባል፡፡ ስለዚኽ ይኼ የመረጋጋት፣ የሰላም‹ የፍቅር ቦታ ነው፡፡ ልጆቻችን የአገር ፍቅር፣ የአገር ሰላም፣ የአገር አንድነት አስተምረውናል፡፡ በልጆቻችን ተምረናል፤ ጠግበናል፤ ረክተናል፤ ኮርተናል፡፡
የልጆቻችንን ነፍስ በገነት በመንግሥተ ሰማያት ያሳርፍልን፤ ይማርልን፤ ወላጆቻቸውን ይጠብቅልን፤ ከክፉ ነገር ይሰውረን፤ መልካሙን ነገር ያምጣልን፤ ልጆቻችንና ወገኖቻችንን በሰላም ወደ ቤታቸው ይመልስልን፡፡   ኹላችንም ተጽናንተን የሚያኮራ ሥራ እንድንሠራ ቅዱስ ፈቃዱ ይኹንልን፡፡ ነፍሰ ገብሩ ኃይለ ኢየሱስ፣ ኃይለ ሚካኤል ሀገረ ሕይወትን መንግሥተ ሰማያትን ያውርስልን፡፡
*       *       *
‹‹ወገኖቻችን ሰማዕታት፣ ታሪክ አትርፈው ስለሔዱ ለዘላለም ስማቸውና ሥራቸው ሲወሳ ይኖራል››
(ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ፤ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጅ፤ የወላይታ ኮንታ እና ዳውሮ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ)
His Grace Abune Mathewosአኹን ያለንበት አካባቢ ቤተ መቅደሱ [ደብረ ፍሥሓ መካነ ሰማዕት]ቂርቆስ ነው፡፡ እንደምታውቁት ቂርቆስ ሕፃን ነው፡፡ በምን መልክ እንደ ዐረፈ ታውቃላችኹ፡፡ ሕፃኑ ቂርቆስ፣ ዓላውያን ነገሥታት በእኛ እምነት እመን፤ እኛ የምናዝዝኽን ፈጽም ባሉት ሰዓት አልተቀበላቸውም፡፡ እሳት ነደደ፤ በበርሜል ውስጥ ውኃ ፈላ፡፡ በዚኽ ሰዓት እናቱ ደንግጣ ወደ ፈላው ውኃ ለመግባት ስትፈራ ሕፃኑ ቂርቆስ፣ ‹‹እናቴ ጨክኚ፤ ዛሬ መንግሥተ ሰማያት የምንገባበት ቀን ነው፡፡ አባቶቻችን በሰጡን፣ ባወረሱን፣ ባስተማሩን እምነት ጸንተን ወደ መንግሥተ ሰማያት የምንገባበት ነውና ከዓላዊው ንጉሥ አትፍሪ›› ብሎ እናቱን ወደ እሳት የጋበዘ ነው፡፡ እስከ መጨረሻው እስከ ዘላለሙ ሰማዕቱ ቂርቆስ ሲባል ይኖራል፤ ታሪክ ሲዘክረው ይኖራል፤ ታሪክ አይደመሰስም፡፡
አኹንም እነዚኽ ወንድሞቻችን፣ ወገኖቻችን ሰማዕታት የታሪክ ባለቤቶች ስለኾኑ፣ ታሪክ አትርፈው ስለሔዱ ከእነርሱ በፊት እንደነበሩት ኹሉ ለዘላለም ስማቸው፣ ሥራቸው ሲወሳ ይኖራል፡፡ ሐዘን ኹልጊዜ ሲያነሡት ልብ ይሠቀጥጣል፡፡ ይኼን እያነሡ መናገር በጣም ይከብዳል፡፡ ጭንቅላት ሊሸከመው አይችልም፡፡ እናም እዚኽ ያሉትን እያጽናናችኹ፣ እዚያ የቀሩት ደግሞ በሰላም እንዲወጡ ምሕላ እያደረግን ልንጸልይ ይገባል፡፡ እኛ እዚኽ ፀሐይ እየሞቅን፣ እየተነጋገርን እናዝለን፤ እዚያ እነርሱ ከወጡበት ሰውነታቸው አልቆ ነፍሳቸው የምትጨነቅ አለችና በሰላም እንዲያወጣቸው ላለፉት ብቻ ሳይኾን ለቀሩትም ጸሎት እያደረጋችኹ በዚኽ እንድትጽናኑ ነው አደራ የምንለው፡፡
ወላጆች ወለዱ እንጂ የኹላችን ልጆች ናቸው፤ ሐዘኑ የኢትዮጵያ ነው፤ እግዚአብሔር ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ጽናቱን ይስጥልን፡፡ እዚያ የቀሩትንም በሰላም ያውጣልን፡፡
their graces the archbishops condoling the mournersስድስት ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት÷ ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ፣ ብፁዕ አቡነ ማትያስ ዘካናዳ፣ ብፁዕ አቡነ ሉቃስ፣ ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ፣ ብፁዕ አቡነ እንጦንስ፣ ብፁዕ አቡነ ኄኖክ፤ ሚያዝያ ፲፫ ቀን ፳፻፯ ዓ.ም. በደብረ ፍሥሓ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ሰበካ ተገኝተው የመስተጋድላን ሰማዕታትን ኢያሱ ይኵኖ አምላክ እና ባልቻ በለጠ ቤተ ሰዎች እና ወዳጆች ያጽናኑበት ቃለ ምዕዳን

2015 ኤፕሪል 22, ረቡዕ

ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት በሐዘንተኞቹ ቤት ተገኝተው በማጽናናት ላይ ይገኛሉ


ሚያዝያ 13 ቀን 2007 ዓ.ም.
001 papasat 002በዛሬው ዕለት ከቀኑ ዐሥር ሰዓት ጀምሮ ከስድስት በላይ ሊቃነ ጳጳሳት ሰማእቱ ቅዱስ ቂርቆስ ቤተ ክርስቲያን አካባቢ በሚገኘው በሊቢያ በግፍ በአሰቃቂ ሁኔታ የተገደሉትን ወጣቶች ቤተሰቦችን ለማጽናናት በመኖሪያ ቤታቸው ተገኝተዋል፡፡

ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳቱ በጥልቅ ሐዘን ላይ ለሚገኙት የሰማእታቱ ቤተሰቦችን፤ ዘመድ ወዳጆቻቸውን እንዲሁም ምእመናንን በቃለ እግዚአብሔር በማጽናናት ላይ ይገኛሉ፡፡

ብፁዕ አቡነ ሉቃስ፤ ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ፤ ብፁዕ አቡነ ማትያስ፤ ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ፤ ብፁዕ አቡነ እንጦንስ፤ ብፁዕ አቡነ ሔኖክ ተገኝተዋል፡፡

ብፁዕ አቡነ ሉቃስ በሰጡት የወንጌል ትምህርት €œልጆቻችን ብርሃን፤ መጻሕፍቶቻችንና ጀግኖቻችን፤ እንዲሁም የሃማኖትም የሀገርም አርበኞች ናቸው፡፡€ ብለዋል፡፡

ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ በበኩላቸው የሰማእቱ ቅዱስ ቂርቆስንና የእናቱን የቅድስት ኢየሉጣን ታሪክ መነሻ በማድረግ ሰፊ የማጽናኛ ትምህርት ሰጥተዋል፡፡

የማኅበረ ቅዱሳን ሚዲያ ክፍል አባላትም በቦታው ተገኝተዋል፡፡

እስመ በእንቲኣሁ ይቀትሉነ ኲሎ አሚረ፡፡ ወኮነ ከመ አባግዕ ዘይጠብሑ ስለ አንተ ቀኑን ሁሉ እንገደላለን፤እንደሚታረዱ በጎች ተቆጠርን:: መዝ.43፡22

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን ጽ/ቤት የተሰጠ የሐዘን መግለጫአትምኢሜይል
              
                                                                                ሚያዝያ 14 ቀን 2007 ዓ.ም.
         

ቤተ ክርስቲያን የተመሠረተችው በክርስቶስ ሞት እና ትንሣኤ ነው፡፡ ይህንንም ስንል ለስም አጠራሩ ክብር ምስጋና ይግባውና ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርሰቶስ ምንም በደል ሳይገኝበት በአይሁድ ተከስሶ በግፍ የሞት ፍርድም ተፈርዶበት በዕለተ ዓርብ በመልዕልተ መስቀል ተሰቅሎ ደሙን አፍስሶ የሰው ልጆችን ዕዳ በደል ደምስሶ ነጻ እንዳወጣንና ዘለዓለማዊ ሕይወትን እንዳደለን በማመን እኔ ቅዱስ ነኝና እናንተም ቅዱሳን ሁኑ በማለት በሰጠው አምላካዊ ትእዛዝ መሠረት ትመራለች ማለታችን ነው፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምእመናንም ይህንኑ የቤተ ክርስቲያን ትምህርት አምነው በሥራ ሲገልጡ ኑረዋል፤ ዛሬም በዚሁ እውነታ ይገኛሉ፡፡

ስለእውነት መሥዋዕትነት መክፈል ለቤተ ክርስቲያን እንግዳ ነገር አይደለም፡፡ በየዘመናቱ እግዚአብሔር ለዚህ ክብር ያደላቸው ቅዱሳን ሰዎች የጌታን ፈለግ ተከትለው ስለክርስትናቸው ወይም በጌታችን በመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የማዳን ሥራ በማመናቸውና ይህንንም በይፋ በመመስከራቸው ብቻ በክፉዎች ሰዎች እጅ በሥጋቸው መከራ እየደረሰባቸው ለሞት በመብቃታቸው ሰማዕት እየሆኑ አልፈዋል፡፡

ቤተ ክርስቲያናችንም እነዚህን ለክርስቶስ ያላቸውን ፍቅር እሰከ ሞት ድረስ በመታመን የገለጹትን ልጆቿን በታላቅ መንፈሳዊ ክብር ታዘክራቸዋለች፤ ምእመናንም በእነርሱ የሕይወት ጎዳና እንዲማሩና በኑሮአቸውም እንዲጽናኑ እያደረገች ትገኛለች፡፡ በዚህ ሂደትም የክርስቲያኖችን ሕይወት የቀጠፉትን ዓላውያንን ድርጊታቸውን እያወገዘች አድራጊዎቹ ግን በክፉ መንፈስ የተመሩ ሰዎች በመሆናቸው ለእነርሱም ልቡና እንዲሰጣቸውና ምህረትን እንዲያገኙ ከእግዚአብሔር መለመንን አላቋረጠችም፡፡ ይህም ጌታችን ኢየሱስ ክርሰቶስ በመሰቀል ላይ ሳለ አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁምና ቅር በላቸው በማለት የበደሉንን እንኳ ይቅርታ እንድናደርግላቸው ባስተማረን ትምህርት መሠረት ነው፡፡

የክርስትና ተግባር እንደየዘመኑ ሁኔታ የሚቀያየር ሳይሆን ከእግዚአብሔር አንድ ጊዜ የተሰጠና የጸና ዘላለማዊ እውነታ ነው፡፡ ስለሆነም ይህ የቤተ ክርስቲያን ትምህርት ዛሬም በምእመናን ሁሉ ዘንድ ህልው ሆኖ ይኖራል፤ በሥራም ይገለጣል፡፡

በሰሞኑ ራሱን እስላማዊ መንግሥት (IS) እያለ በሚጠራው ዓለም አቀፋዊው አሸባሪ ድርጅት በተለያየ ምክንያት ወደ ሊቢያ የገቡ ክርስቲያን ወንድሞቻችንን እና እኅቶቻችንን ይዞ በማሰር በውስጣቸውም 30 የሚያህሉትን ወንድሞቻችንን በሁለት የተለያዩ ቦታዎች በአሰቃቂ ሁኔታ እንደገደላቸው በይፋ በኢንተርኔት ባሰራጨው የቪዲዮ መረጃ አሳውቋል፡፡ በዚሁ መረጃው ላይም የተገደሉት ወንድሞቻችን የተገኘባቸው አበሳ ወይም ወንጀል ክርስቲያን ሁነው መገኘታቸው (በተለይም እነርሱ ጠላታችን ያሏት የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን አባል መሆናቸው) እና ሃማኖታቸውንም አንቀይርም ማለታቸው እንደሆነ በግልጽ አሳውቋል፡፡ ይህም ሳይበቃው የገደለበትን አሰቃቂ መንገድ በቪዲዮ ቀርጾ በማስፈራሪያ ቃላት በማጀብ ለዓለም ሁሉ አስራጭቶታል፡፡ ይህ ሁኔታ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርሰቶስ ዋጋ የከፈለለትን የሰው ልጅ አንገቱን በካራ ቀልቶ ደሙን ማፍሰስ እና ሕይወቱን ማጥፋት እጅግ የሚዘገንን ሰይጣናዊ ተግባር ነው፡፡

የቤተ ክርስቲያናችንም ቅዱስ ሲኖዶስ ይህ አሳዛኝ ዜና እንደተሰማ ድርጊቱን አውግዞ በቤተ ክርስቲያኒቱ ደረጃ የጸሎት ጊዜ ማወጁና ምእመናን ሁሉ በየአሉበት አካባቢ ሁነው እንዲሳተፉ ጥሪ ማሳለፉ ይታወቃል፡፡ ስለዚህም ምእመናን ሁላችንም በዚህ የአንድነት መገለጫ በሆነው መንፈሳዊ ተግባር ላይ ልንሳተፍ ያስፈልጋል፡፡

እነዚህ በበረኻው ላይ ደማቸው የፈሰሰው ወንድሞቻችን ለሃይማኖታቸው ያሳዩት ጥብዓት ለሁላችንም ትልቅ ትምህርት የሚሆንና አክብሮት የሚገባው ተግባር ነው፡፡ እነርሱ ወደጠራቸው ወደ እግዚአብሔር በክብር ተጉዘዋል፡፡ በወንጌል ለእናንተም ለወዳጆቼ እላችኋለሁ ሥጋን የሚገድሉትን በኋላም አንድ ስንኳ የሚበልጥ ሊያደርጉ የማይችሉትን አትፍሩâ€Ãƒ‚ºÃƒÃ‚¢€Ãƒ‚º በማለት የተጻፈውን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ቃል በሥራ በመተርጎም ምስክር ሁነዋል፡፡ ሉቃ.12.4 የተማሩትን የክርስትና ትምህርት በትክክል በሥራ በማሳየታቸው እጅግ የሚያኮራ ተግባር ፈጽመዋልና ሁላችንም እንኰራባቸዋለን፡፡

በርግጥ በሥጋ ስለተለዩን እንደ ሰውነታችን ልናዝንና ልናለቅስ እንችላለን፡፡ በተለይም ቤተሰዎቻቸው እና የቅርብ ወዳጆቻቸው የደረሰባቸው ኀዘንና ጉዳት ከፍትኛ እንደሚሆን ጥርጥር የለውም፡፡ ስለዚህም የልብ ስብራትን የሚጠግነው እግዚአብሔር አምላካችን መጽናናትን እንዲሰጣቸው እንጸልያለን፡፡ ሆኖም ግን እነዚህ ወንድሞቻችን የተጓዙት ሁላችን ወደምንናፍቀው ወደ እግዚአብሔር መንግሥት በመሆኑ ልናዝን አይገባም፤ በእግዚአብሔር መንግሥት ምስክር ያገኙ በመሆናቸው ደስ ሊለን እንጂ፡፡ በሰው ፊት ለሚመሰክርልኝ ሁሉ እኔ ደግሞ በሰማያት ባለው በአባቴ ፊት እመሰክርለታለሁ ባለው አምላካዊ ቃል መሠረት በክፉዎች ሰዎች ፊት ያለፍርሃትና ያለኀፍረት ስለርሱ መስክረው በዐደባባይ መከራ ተቀብለዋል፡፡ ማቴ.10.32፡፡ እንዲሁም ድል የነሣው እንዲሁ በነጭ ልብስ ይጎናጸፋል፣ ስሙንም ከሕይወት መጽሐፍ አልደመስስም፤ በአባቴና በመላእክቱም ፊት ለስሙ እመሰክርለታለሁ በማለት እንደተናገረው ቃሉ የታመነ የሆነው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዋጋቸውን እንደሚከፍላቸው ፍጹም እምነታችን ነውና በዚህ ደስ ሊለን ይገባል፡፡ ራእ.ዮሐ.3.5፡፡ እንዲህ ዓይነቱን ጸጋና ክብር አግኝተው ወደ አምላካቸው ለሔዱት የሃይማኖት ጀግኖች የክብር አሸኛኘት ማድረግና አኩሪ ተግባራቸውን ማዘከር ግን ያስፈልገናል፡፡ በዚህ ዘመን ላለነው ክርስቲያኖች ሁሉ ለሃይማኖታቸው ሕይወታቸውን አሳልፎ እስከመስጠት ድረስ መሥዋዕት በመሆን አብነት ሁነውናልና፡፡

ይህ ጭካኔና ክፉ ድርጊት የፈጸሙት ፉከራቸውን በዐደባባይ የገለጹት ሰዎች ምናልባት ክርስቲያኖች በዚህ ፈርተውና ተሰቅቀው ከሃይማኖታቸው ፈቀቅ የሚሉ፣ ቤተ ክርስቲያንም የምትሸማቅቅ አድርገው ገምተው ይሆናል፡፡ ሆኖም ግን ሰማዕትነት ክርስትናን የሚያለመልምና የበለጠ የሚያጠናክር መሆኑን ከታሪክ ሊማሩት ይገባል፡፡ የመጀመሪያውን ክርስቲያናዊ ቤተሰብ ለመበተንና ክርስትናን በእንጭጩ ለማጥፋት አስበው አይሁድ ቅዱስ እስጢፋኖስን በዐደባባይ በድንጋይ ይወግረው ማስፈራሪያ እንዲሆን ገድለውት ነበር፡፡ ቢሆንም ግን ይህ ድርጊት ክርስቲያኖችን ከኢየሩሳሌም ከተማ ወጥተው ወደ ተለያዩ አካባቢዎች እንዲሔዱና ክርስትናን የበለጠ እንዲያስፋፉት አደረጋቸው እንጂ ቤተክርስቲያንን ማሸማቀቅ አልቻለም፡፡

በሮማውያን የኃያልነት ዘመንም እንዲሁ ነገሥታቱ ክርስትናን ለማጥፋት ብዙ ደክመዋል፡፡ ቢሆንም የነርሱ የጭካኔ ተግባር ክርስትና የበለጠ በቤተ መንግሥታቸው ጭምር እንዲሰበክና እንዲስፋፋ፣ የቤተ መንግሥቱ አባላት የነበሩ ሰዎችም ክርስትናን እየተቀበሉ ሰማዕታት እንዲሆኑ አደረጋቸው እንጂ ክርስትናን አላጠፋውም፡፡ በርግጥ ለአጭር ጊዜም ቢሆን ክርስቲያኖች ኑሮአቸውንም ሆነ መንፈሳዊ ተግባራቸውን በካታኮምብ ውስጥ እንዲያደርጉ አስገድዶ እንደነበር ግን አንዘነጋውም፡፡ አሁንም በአንዳንድ ቦታዎች በክፉ አሳብ በሚመሩ ሰዎች ምክንያት እንዲህ ዓይነቱ ሁኔታ ቢያጋጥም ከቤተ ክርስቲያን ታሪክ ተምረንና በእግዚአብሔር ኃይል ታምነን ፍጹም ክርስቲያናዊ በሆነ መንገድና ልናሳልፈው፣ ድል ልንነሣውም ይገባል፡፡

እኛ በክርስቶስ የደም ዋጋ የተገዛንና ዋጋም የተከፈለልን መሆኑን ሳንዘነጋ በክርስትናችን ምክንያት ዋጋ የሚያስከፍል ነገር ሲመጣ እንደነዚህ ወንድሞቻችን በጥብዐት ልንቆም ያስፈልጋል፡፡ እነርሱ ሕይወታቸውን ሰጥተው ለሃይማኖታቸው እንደተጋደሉ መደለያ የሆነው ጊዜያዊ ኑሮም እንዳላታለላቸው ሁሉ እኛም ሃይማኖታችንን ከሥጋዊ ፍላጎታችን በላይ ልናስቀድም እንደሚገባን የተማርንበት ክስተት በመሆኑ ሁላችንም እንዲህ ዓይነት ነገር ሲያጋጥመን ልንከተለው የሚገባንን የክርስትና አቅጣጫ ግልጽ በሆነ መንገድ በማሳየት ረገድ ለዚህ ዘመን ትውልድ መልካም አርአያ ሆነውናልና በዚህም ዘወትር ልናዘክራቸውና ልናመሰግናቸው ይገባናል፡፡

ክርስቲያኖች በዚህ ዓለም በሕይወተ ሥጋ ብንኖርም ከእግዚአብሔር ጋር በደስታ እንኖራለን በሥጋ ብንሞትም ወደ እግዚአብሔር እንሔዳለንና ሁሌም የእግዚአብሔር ነን፡፡ በመጽሐፍ በሕይወት ሆነን ብንኖር ለጌታ እንኖራለንና፣ ብንሞትም ለጌታ እንሞታለን፡፡ እንግዲህ በሕይወት ሆነን ብንኖር ወይም ብንሞት የጌታ ነን እንደተባለው በማንኛውም ሁኔታ በእግዚአብሔር ደስ ይለናል እንጂ በምንከፍለው ዋጋ ልንሳቀቅ አይገባንም፡፡ ሮሜ.14.8፡፡

ክርስትና ራስን ለሌላው አሳልፎ መስጠት ነውና አንዱ ወገናችን ሲያዝን በሐዘኑ ልንካፈል ጭንቀቱንም ተጋርተን ብንችል ልናቃልልለት ያስፈልጋል፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ደስ ከሚላቸው ጋር ደስ ይበላችሁ፣ ከሚያለቅሱት ጋር አልቅሱ ሮሜ.12.15፤ በማለት እንዳስተማረው በማኅበራዊ ሕይወታችን በፍቅር መንፈስ ልንረዳዳ ያስፈልጋል፡፡ በተለይም በዚህ በመከራ ጊዜ ሐዘንተኞችን ማጽናናት፣ እንዲሁም ደግሞ ገና በየእስር ቤቱ በችግርና በሰቆቃ ያሉትን ወገኖቻችንን በምትለው ዐቅም ሁሉ ልንረዳቸውና ከጎናቸው ልንቆም ያስፈልገናል፡፡

ከዚህ አንጻር ካህናት አባቶቻችንም ሆኑ መምህራነ ወንጌል ድርሻቸው የጎላ ነውና የተለመደ መንፈሳዊ አገልገሎታቸውን ፍጹም በሆነ ሓላፊነት እንደሚወጡ አንጠራጠርም፡፡ በተለይ የችግሩ ሰለባ የሆኑትን በመርዳቱ ረገድ ሁሉም ሰው በአፋጣኝ የድርሻውን እንደሚወጣ እምነታችን ነው፡፡ እዚህ ላይ በተለያየ ምክንያት ከሀገራቸው የወጡ፣ በተለያየ ችግር ውስጥ ያሉና ያለፉ ሁሉ አንዳቸው ሌላውን ወገናቸውን በመርዳት መንፈሳዊ ግዴታቸውን እንዲወጡ በዚህ አጋጣሚ ማሳሰቡ አስፈላጊ ነው፡፡

ከዚህ ክስተት የምንማረው ሰው በመልካም ትምህርት ከተቀረጸ ነፍሱን ለሌላው አሳልፎ እስከመስጠት ድረስ እንደሚታገስ ለሃይማኖቱም ፍጹም ዋጋ ሊከፍል የሚችል መሆኑን ነው፡፡ ስለዚህ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያናችን ምእመናኗን በትምህርተ ሃይማኖትና በሥነ ምግባር በመቅረጹ ረገድ የበለጠ በርትታ እንድትሠራበት የሚያመላክት ነው፡፡ እውነተኛው የክርስትና ትምህርት ሌላውን ወደማጥፋት ሳይሆን ወደ ርኅራኄና የራስን ሕይወት ወደመስጠት፣ በአጠቃላይም እንዲህ ወደ መልካም ጎዳና ይመራልና፡፡

በአንጻሩ ደግሞ ክፉ ትምህርት ሰውን ወደ አውሬነት ሊቀይር የሚችል መሆኑን ይህን ኢሰብአዊ ተግባር ያለምንም ርኅራኄ ሲፈጽሙ ከምናያቸው ሰዎች እንገነዘባለን፡፡ ስለዚህ ሰዎችን ከልጅነታቸው ጀምሮ በጥሩ መንገድ መምራት፣ ከጥላቻ ይልቅ ፍቅርን መስበክ፣ በአጠቃላይም መልካም የሆነውን ትምህርት ማስተማር ለሀገርም ሆነ ለዓለም የሚበጅ መሆኑን ተረድተን ሁላችንም የበኩላችንን እና የሚመለከተንን መወጣት እንደሚያስፈልገን ትምህርት ወስደንበታል ብለን እናምናለን፡፡

ይህ አሳዛኝ ሁኔታ ከተሰማ ጀምሮ የተለያዩ አካላት ድርጊቱን በማውገዝ ኃዘናቸውን በመግለጽ ረገድ የየራሳቸውን ድርሻ እየተወጡ ይገኛሉ፡፡ ይህ በራሱ የጋራ አንድነትንና መረዳዳትን የሚያመለክት በመሆኑ በእጅጉ የሚያስመሰግን ተግባር ነው፡፡ ሆኖም ግን ይህ የጭካኔ ሥራ በአጭር ጊዜ የተቀነባበረና የአንድ ወቅት ክስተት ሳይሆን በተደጋጋሚ እየተፈጸመ የብዙ ንጹሐን ሰዎችን ሕይወት እየቀጠፈ በመሆኑ የሚመለከታቸው አካላት ሁሉ ከማውገዝ ባለፈ ሥር ነቀል ለውጥ ሊያመጣና ችግሩን ሊፈታ የሚችል ሥራ በመተባበር ሊሠራ ይገባዋል ብለን እናምናለን፡፡ ለዚህም የተለያዩ የእምነት ድርጅቶችና ዓለም አቀፋዊ ተቋማት ግንባር ቀደም ድርሻ ሊኖራቸው ስለሚገባ ልዩነትን ከማጉላት ይልቅ ለሰው ልጅ ሕይወት የሚጠቅም ነገር በመሥራት ሓላፊነታቸውን ሊወጡ፤ መንግሥታትንም ሊያሳስቡ ይገባል፡፡

የቤተ ክርስቲያን ልጆች የሆንን ሁላችን ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሕይወት በሆነው ትምህርቱ እኔ ግን እላችኋለሁ፣ በሰማያት ላለ አባታችሁ ልጆች ትሆኑ ዘንድ ጠላቶቻችሁን ውደዱ፣ የሚረግሙአችሁንም መርቁ፣ ለሚጠሉአችሁም መልካም አድርጉ፣ ስለሚያሳድዱአችሁም ጸልዩ፤ እርሱ በክፉዎችና በበጎዎች ላይ ፀሐይን ያወጣልና፤ በጻድቃንና በኃጢአተኞችም ላይ ዝናቡን ያዘንባልና፡፡ ማቴ.5.44-45፡፡ በማለት እንዳስገነዘበን ክፉ አድራጊዎቹ ድርጊታቸው የሚወገዝና ማንም ሰው ቢሆን ሊጸየፈው የሚገባ ቢሆንም ይህን የፈጸሙት ሰዎችና የአስተሳሰባቸው ደጋፊዎች የሆኑ አካላት ግን ከክፉ መንገዳቸው እንዲመለሱ በማድረግ ረገድ እንደ ክርስትናችን ትልቅ ሓላፊነት አለብን፡፡ በክርስትና ጎዳና የተጓዙ አባቶቻችንና እናቶቻችን የጭካኔ ተግባር እየፈጸሙባቸው ያሉትን ሰዎች ሳይቀር ምሕረት እንዲያገኙ ወደ እግዚአብሔር ያመለክቱላቸው እንደነበር ከታሪካቸውና ከገድላቸው እንማራለን፡፡ ስለዚህ እኛም ለእነዚህ ክፉ አድራጊዎቹ ሰዎች ልንጸልይላቸው፣ እግዚአብሔር እንዲምራቸው ልቡናን እንዲሰጣቸው ልንለምንላቸው ይገባል፡፡ በውስጣቸው ያለው መንፈስ እጅግ ክፉ ነውና ጌታም በወንጌል ይህ ወገን በጸሎትና በጦም ካልሆነ በምንም ሊወጣ አይችልም ማር.9.29፡፡ በማለት እንዳስተማረው እንዲህ ዓይነቱ ክፉ መንፈስ ከሰዎች እንዲርቅ በጾምና በጸሎት ልንተጋ ይገባናል፡፡

በመጨረሻም ስለሃይማኖታቸው ሰማዕትነትን የተቀበሉትን ወንድሞቻችንን አምላካችን እግዚአብሔር ቅዱሳንን ባከበረበት ክብር እንዲያከብራቸው፣ ለቅዱሳን ሰማዕታት ያቀዳጃቸውን የክብር አክሊል እንዲያቀዳጃቸው በፍጹም እምነት እየጸለይን ቤተሰዎቻቸውንና ወዳጆቻቸውንም ቸሩ ፈጣሪያችን መጽናናትን እንዲያድላቸው እንመኛለን፡፡

2015 ኤፕሪል 21, ማክሰኞ

ሰበር ዜና – ቅ/ሲኖዶስ ከነገ ሚያዝያ ፲፬ ቀን ጀምሮ የሰባት ቀናት ጸሎተ ምሕላ ዐወጀ፤ ቤተሰቦች የተሠው ክርስቲያኖችን ፎቶ፣ ስመ ክርስትና እና ሙሉ አድራሻ እንዲያቀርቡ አዘዘ – ‹‹ልጆቻችን የሃይማኖት ሰማዕትነትን የተቀበሉ የሃይማኖት መስተጋድላን ናቸው››


pat mat
  • ቅዱስ ሲኖዶስ በሊቢያ በግፍ የተሠው ክርስቲያኖች፣ ሃይማኖታችንን አንክድም በማለት የሃይማኖት ሰማዕትነትን የተቀበሉየሃይማኖት መስተጋድላን መኾናቸውን አረጋገጠ፤ ‹‹የልጆቻችን ሰማዕትነት በእግዚአብሔር መንግሥት ታላቅ ዋጋ ስላላቸው በዚኽ ከሐዘናችኹ እንድትጽናኑ ቤተ ክርስቲያን ታሳስባለች፡፡››
  • ነገ ወቅዱስ ፓትርያርኩ እና ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፣ መላው የአዲስ አበባ ገዳማት እና አድባራት አስተዳዳሪዎች፣ ሊቃውንት፣ ካህናት የሰንበት ት/ቤቶች ወጣቶች እንዲኹም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የየመምሪያው ሓላፊዎች እና ልዩ ልዩ ሠራተኞች በተገኙበት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ጸሎተ ፍትሐት እና ጸሎተ ወንጌል ይከናወናል 
  • ሥነ ሥርዐቱ በደቡብ አፍሪቃ በግፍ የተገደሉ ንጹሐን ኢትዮጵያውያንንም ይጨምራል

ነፍስህን ይማር በሉኝ


 ሁለት የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮች በአንድ ላይ  ያገለግላሉ  ሰባክያነ ውንጌል ናቸው  አንደኛው ለአገልግሎት ውደ ክፍለ ሀገር ወጥተው  ሲመለሱ የመኪና አደጋ ደረሰና ወደ 35 ሰዎች ህይወታቸው  ሲያልፍ ሰባኬ ወንጌሉ ተረፉ  ይህንን የሰማ በልደረባቸው  የስራ አጋሮቹን ጠርቶ  ከፊታቸው ቁጭ ብሎ  ነፍስህን ይማረው  በሉኝ  እኔ እደሆን  ለአገልግሎት መንቀሳቀሴ አይቀርም  አደጋውም  አይቀርምና መሞቴ ሰለማይቀር  ከወዲሁ  አይኔ እያየ ጆሮየ እየሰማ  ነፍስህን  ይማረው በሉኝ  አለ ይባላል ፡፡
 በጆሮአችን ስንሰማ የነበረውን  በመጽሐፍ ስናነብ ነበረውን  ሰማእትነት  በዐይን አይተናል  ድሮውኑ ክርስቲያን መሆን ሰማእትነት የሚያጎናጽፍ ስለሆነ  ሁላችንም አንገታችንን እንደ ሰጠን ለጊዜው እየቆጠርን ተግባራዊ ለሚሆነው ሰማእትነት መታደል የሚጠይቅ ቢሆንም ሃይማኖታዊ ዝግጅት ማድረግ ያስፈልጋል፤፤

ለነገሩ በቸልተኝነት አልፈነው ነው እንጂ  1999 ዓ.ም በጅማ  የነበረው ሰማእትነት  ትኩረት ስላልተሰጠው አሁን  ገና ዋጋ ያስከፍላል፡፡  በተለይ የሃይማኖት መሪዎችን፡ በነገራችን ላይ እስካሁን የግብጾችንም ጨምሮ  የሃይማኖት መሪዎች  ለሰማእትነት  አልተመረጡም  ምሥጢሩ ምን ይሆን ?

                                   በአውሮጳ   የካህናት አንድነት ማኅበር ሊቋቋም መሆኑ ታወቀ በ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከመላዋ አውሮጳ   የተውጣጡ ካህናት፡” የ...