2015 ኖቬምበር 7, ቅዳሜ

“ገርፎ የመጮኽ”፡- የተሐድሶዎች የማደናገሪያ ስልት


አትም ኢሜይል
ጥቅምት 26 ቀን 2008 ዓ.ም
ክፍል ሁለት
የተሐድሶዎችን እንቅስቃሴ በተመለከተ በክፍል አንድ ዝግጅታችን በማኅበረ ቅዱሳን ኅትመትና ኤሌክትሮኒክስ ሚዲያ ክፍል በስምዐ ጽድቅ ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ጋዜጣ በተከታታይ እየወጣ ያለውን ጽሑፍ አቅርበንላችሁ እንደነበር ይታወሳል፡፡ ክፍል ሁለትን ደግሞ እነሆ፡-
አማናዊቷ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በክርስቶስ ደም ተመሥርታ በሐዋርያት ስብከት ከሰፋችበት ጊዜ ጀምሮ ያለ ፈተና አልጋ በአልጋ የሆነ ሕይወት የመራችበት ጊዜ የለም፣ ወደፊትም አይኖርምም፡፡ በሐዋርያት ዘመን ይሁዳና ቢጽሐሳውያን፣ በሐዋርያውያን አበው ዘመን ግኖስቲኮች፣ በሊቃውንት ዘመን አርዮስ፣ መቅዶንዮስ፣ ንስጥሮስና ልዮን ቤተ ክርስቲያንን ለመፈተን የተነሡ ነበሩ፡፡ ቤተ ክርስቲያን በየዘመናቱ እንደ ተጻራሪዎች አሳብ አሉታዊ፣ በእግዚአብሔር ፈቃድ ግን ለምእመናን መንፈሳዊ ዕድገት አዎንታዊ አስተዋጽኦ የነበራቸው ብዙ መከራዎችን አሳልፋለች፡፡ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ከእናንተ ጋር ነኝ የሚለው የጌታችንና የአምላካችን የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ቃል ማረጋገጫ በዚህ ሁሉ በማያቋርጥ ማዕበል ውስጥ ቤተ ክርስቲያን ድል አድራጊ ሆና ወጀቡን ማለፍ መቻሏ ነው፡፡
04menafikanባለንበት ዘመን ቤተ ክርስቲያንን የማዳከምና ምእመናንን የመንጠቅ ተግባር ለይቶላቸው በሌላ የእምነት ጎራ የተሰለፉ አካላት ተልእኮ መሆኑ ቀርቷል፡፡ ይህ ተግባር ዛሬ ዛሬ ቤተ ክርስቲያን እሷ እንደ ሻማ እየቀለጠች ባበራችላቸው፣ በሥጋዊ ፈቃዳቸው የእንጀራ ማብሰያ ያደረጉትን ሙያ ባስተማረቻቸው፣ በጉያዋ ባደጉ፣ የእናት ጡት ነካሽ በሆኑ በራሷ ልጆች የሚፈጸም ሆኗል፡፡ እነዚህ ሰዎች በአለባበሳቸው፣ በአነጋገራቸው (ግእዝ ስለሚጠቅሱ)፣ በአካሔዳቸው (ቤተ ክርስቲያን ስለሚመላለሱ) እና በአገልግሎታቸው (ተአማኒነት ለመፍጠር ስለሚተጉ) ክርስቲያኖች ሊመስሉን ይችላሉ፡፡ ይህ ሁሉ ቀን እስኪወጣ ለማደናገሪያነት የተጠቀሙበት ማስመሰያ ጭምብል እንጂ በእውነት ፊት ሚዛን የሚደፋ መንፈሳዊነት ያለበት ሕይወት አይደለም፡፡ ይህ ድርጊታቸው የሚያስቀርብን ነገር ግላዊ ጥቅም ቢሆን ሁሉን ለእግዚአብሔር ሰጥቶ ማለፍ ይቻል ነበር፡፡ ነገር ግን ከውስጥ እስከ ውጪ በተዘረጋ መዋቅር፣ ቤተ ክርስቲያንን እስከ መረከብ፣ ካልተቻለ እስከ መክፈል በሚያደርስ የተቀናጀ ስልት፣ በፕሮቴስታንታዊ በጀት በታገዘ ድጋፍ አምልኮተ እግዚአብሔርን ከምድረ ገጽ ላይ ለማጥፋት የኤልዛቤልን ዕቅድ የሚያስፈጽሙ አካላትን መታገሥ አግባብ ባለመሆኑ ማንነታቸውን ገልጾ ሕዝብ እንዲያውቀው ማድረግ መንፈሳዊ ግዴታችን ይሆናል፡፡
እነርሱ መዋቅር ዘርግተው፣ ስልት ነድፈው፣ በጀት መድበው ቤተ ክርስቲያንን ለማጥፋት እየሠሩ ያሉት የተለያዩ ዘዴዎችን በመጠቀም ነው፡፡ ከዚህ በፊት በቀረቡ ጥናቶች እንደተገለጸው ተሐድሶዎች ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን እስከ መክፈል፣ ከተቻለም እስከ መረከብ ያደርሱናል ብለው የዘረጓቸው ስልቶች አሉ፡፡ እነዚህን ስልቶች እውን ለማድረግ ደግሞ የተለያዩ መንገዶችን ይጠቀማሉ፡፡ ከእነዚህ ተሐድሶዎች ከሚጠቀሟቸው መንገዶች መካከል ጥቂቶቹ የሚከተሉት ናቸው፡፡

፩.በሚያውቋቸው ሰዎች በኩል መቅረብ፡- ዛሬ ላይ ተሐድሶ ነን በማለት ቤተ ክርስቲያንን እናድሳለን የሚሉ አካላት የተዋሕዶ ሃይማኖት ተከታዮች ስለነበሩ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ብዙ ሰዎችን ያውቃሉ፡፡ በቤተ ክርስቲያን አስተዳደራዊ መዋቅር ውስጥ፣ በአብነት ትምህርት ቤት ወንበር ዘርግተው የሚያስተምሩ የአብነት መምህራንን፣ በልዩ ልዩ ገዳማት የሚገኙ መናንያንን እና አስተዳዳሪዎችን፣ የመንፈሳዊ ትምህርት ተቋማት አስተዳዳሪዎችን፣ መምህራንን እንዲሁም የሰንበት ትምህርት ቤት አመራሮችንና አባላትን ማወቃቸውና መቅረባቸው በእነርሱ በኩል ተልእኳቸውን የማስፈጸም ዕድል ፈጥሮላቸዋል፡፡


01menafikanለምሳሌ በ፲፱፻፺ ዓ.ም ቀኖና ተሰጥቶት ተጸጽቶ በመመለስ ፋንታ በኑፋቄው በመግፋቱ ምክንያት በ፳፻ወ፬ ዓ.ም በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባዔ ከተወገዙት ፲፮ የተሐድሶ አራማጅ ግለሰቦች መካከል አንዱ የሆነው፣ አሁንም ኦርቶዶክስ ነኝ በማለት የሚያደናግረው እና በሰሜኑ የአገራችን ክፍል የሚካሔደውን የተሐድሶ እንቅስቃሴ የሚመራው ጽጌ ሥጦታው ብዙ የአብነት መምህራንን ለመቀሰጥ ዕድል ያገኘው በአብነት ትምህ ርት ቤት የሚያውቃቸውን ሰዎች በመጠቀም ነው፡፡ መሠረተ ክርስቶስ ቸርችም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ለማደስ በሚደረገው እንቅስቃሴ ለአገልግሎት የምፈልጋቸው በኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ አገልግሎት የሚሰጡ ካህናትን ብቻ ነው ማለቷ የአብነት መምህራንን ለማጥመድ የቤተ ክርስቲያንን ቋንቋ የሚያውቅ አካል አስፈላጊ እንደሆነ በመረዳቷ ነው፡፡ ይህ ሁሉ የሚያሳየን ተሐድሶዎች ከቤተ ክርስቲያኒቷ ቋንቋና ከቤተ ክርስቲያን አባቶች ጋር መተዋወቃቸው በምእመናን ዘንድ ተቀባይ ነትን በማግኘት ተልእኳቸውን ለማሳካት ምን ያህል ያገዛቸው መሆኑን ነው፡፡

፪.በገንዘብ ማታለል፡- ተሐድሶዎች ቤተ ክርስቲያንን ለማጥፋት ከምንጩ ላይ መሥራት አለብን ብለው ትኩረት የሰጧቸው አብዛኛዎቹ ቦታዎች ላይ የሚገኙት የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮች የገንዘብ ችግር ያለባቸው ናቸው፡፡ አብነት ትምህርት ቤቶችን ብንወስድ በቤተ ክርስቲያን መዋቅር የተረሱ የቤተ ክርስቲያን የደም ሥሮች ናቸው፡፡ የሕዝቡ የኑሮ ሁኔታ ከመቀየሩ ጋር ተያይዞ በአሁኑ ዘመን ከዚህ በፊት እንደነበረው ቁራሽ እየለመኑ መማር የማይታሰብ እየሆነ መጥቷል፡፡ በዚህ ምክንያት የአብነት ተማሪዎች ሌሎች የገንዘብ ማግኛ ዘዴዎችን እየተጠቀሙ ትምህርታቸውን መቀጠል ይፈልጋሉ፡፡ በዚህ መካከል ከአሜሪካና ከአውሮፓ የፕሮቴስታንት ድርጅቶች በሚላክላቸው ገንዘብ ኪሳቸውን ያደለቡት ተሐድሶዎች አንድ አማራጭ ሆነው አብነት ተማሪዎችን ቀረቧቸው፡፡ ተሐድሶዎቹ ለገዳማት፣ ለመንፈሳዊ የትምህርት ተቋማት ተማሪዎችና ለገጠሪቷ ቤተ ክርስቲያን ካህናትና ዲያቆናትም ተመሳሳይ ድጋፍ እናደርጋለን በሚል ሰበብ እየበረዟቸው ይገኛሉ፡፡ ባለፈው ዓመት አዲስ አበባ ኮተቤ አካባቢ ባካሔዱት ስብሰባ ላይ ማኅበረ ቅዱሳን ያልደረሰባቸውን አብነት ትምህርት ቤቶችን ቀድመን በድጎማ መልክ መቅረብና መያዝ አለብን የሚል አቅጣጫ መንደፋቸውን ተናግረዋል፡፡

፫.€œአሠልጥኖ€/አሰይጥ
ኖ መመለስ፡- በትውውቅም ሆነ በማታለያ የቀረቧቸውን ሰዎች የጥፋት ዓላማቸውን ለመፈጸም የሚችሉበትን አቅም በሥልጠና ካስታጠቋቸው በኋላ ተልእኳቸውን ሳይረሱ ወደ ቀድሞ ቦታቸው ተመልሰው ሥራቸውን እንዲቀጥሉ ያደርጓቸዋል፡፡ የተሐድሶ ሥልጠናዎችን ወስደው ወይም ሃይማኖታቸውን ትተው ወደ ሌላ በረት ሔደው ከቆዩ በኋላ የጣሉትን ቆብና መስቀል ይዘው ኦርቶዶክሳዊ መስለው የተመለሱ ሰዎች ቁጥር ብዙ ነው፡፡ በዚህ መንገድ ውጪ ድረስ ሔደው ተምረው የመጡ አሁንም አባ እገሌ፣ ቄስ እገሌ፣ ዲያቆን እገሌ እየተባሉ የሚጠሩ በልብሳቸውና በምላሳቸው ኦርቶዶክሳውያን፣ በልባቸው ግን ፕሮቴስታንት የሆኑ ብዙ የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮች አሉ፡፡
02menafikan
፬.ሚዲያዎችን መጠቀም፡- ተሐድሶዎች እንቅስቃሴያቸውን ከግብ ለማድረስ የኅትመት፣ የኤሌክትሮኒክስና የብሮድካስት ሚዲያዎችን ይጠቀማሉ፡፡ ማን እንዳዘጋጃቸው የማይታወቁ ባለቤት አልባ በራሪ ወረቀቶችን፣ ጋዜጦችን፣ መጽሔቶችንና መጻሕፍትን እንዲሁም የተለያዩ የምስል ወድምጽ ውጤቶችን በማሠራጨት መርዛቸውን ይረጫሉ፡፡ ድረ ገጾችን፣ የጡመራ መድረኮችን፣ የሬዲዮ እና የቴሌቪዥን መርሐ ግብራትን በመጠቀም ኑፋቄያቸውቸውን እያስፋፉ ይገኛሉ፡፡

፬.፩.ጋዜጦች
ተሐድሶዎች እያሳተሙ ከሚያሠራጯቸውና መርዛቸውን ከሚረጩባቸው ጋዜጦቻቸው መካከል መጥቅዕ፣ በሃይማኖት ቁሙ፣ መርከብ፣ መና ተዋሕዶ፣ እውነት፣ ኖኅተ ብርሃን፣ ከሣቴ ብርሃን፣ ርግብ፣ ንቁ፣ ወዘተ ጥቂቶቹ ናቸው፡፡

፬.፪.መጽሔቶች

ሌሎች ተሐድሶዎች ኑፋቄያቸውን የሚያሠራጩባቸው የኅትመት ውጤቶች መጽሔቶች ናቸው፡፡ ከእነዚህ መጽሔቶች መካከል ጥቂቶቹ አንቀጸ ብርሃን፣ ብሔራዊ ተሐድሶ፣ ከሣቴ ብርሃን ዘኢትዮጵያ፣ ሰላማ ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ፣ ጮራ፣ ቤተ ፍቅር፣ ወዘተ ሲሆኑ ከእነዚህ ባልተናነሰ ሁኔታ ለተሐድሶ እንቅስቃሴው ድጋፍ ሰጪ የሆኑ ጽሑፎችን የሚያቀርቡ ጌሠም፣ ትሪኒቲ፣ ማቴቴስ፣ ካሪዝማ፣ ወዘተ የሚባሉ የፕሮቴስታንት መጽሔቶች አሉ፡፡

፬.፫.መጻሕፍት
03menafikanተሐድሶዎች በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስም ከአንድ መቶ ሰማንያ (፻፹) በላይ መጻሕፍት ጽፈዋል፡፡ መጽሐፎቻቸው የክርስቶስን አምላክነትና የእመቤታችንን አማላጅነት ክደው የሚያስክዱ፣ ቤተ ክርስቲያንን የሚነቅፉ፣ ቅዱሳንን የሚሳደቡ፣ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባርን የሚያጥላሉ ናቸው፡፡ ተሐድሶዎች የግብር አባታቸው የሉተር ልጆች እንጂ ኦርቶዶክሳውያን አለመሆናቸውን መጽሐፎቻቸው ይናገራሉ፡፡ ከቁጥራቸው ብዛት የተነሣ ሁሉንም የተሐድሶ መጻሕፍት መዘርዘር ከባድ ቢሆንም በ፳፻ወ፬ ዓ.ም ከእነ ጽጌ ሥጦታው ጋር የተወገዘው አሸናፊ መኮንን ብቻ ከሃያ አምስት በላይ መጻሕፍትን ጽፏል፡፡ የተለያዩ የብዕር ስሞችን በመጠቀም ቤተ ክርስቲያንን መሳደብ የእንጀራ ማብሰያው ያደረገው ሠረቀ ብርሃን ዘወንጌል መስተብቁዕ ዘሙታን፣ የዘመናት እንቆቅልሽ ሲፈታ፣ ማሳቀልና ሎፌ የሚሉ በመርዝ የተሞሉ መጻሕፍትን ጽፏል፡፡

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ምእመናንን በስውር መንጠቁ አላጠግባቸው ብሎ ቤተ ክርስቲያንን በግልጽ እየተዋጓት ያሉት ፕሮቴስታንቶችም የተሐድሶ እንቅስቃሴ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እንዳለ እና እንቅስቃሴውም ለእነርሱ ድጋፍ ሰጪ መሆኑን በመጽሐፎቻቸው ገልጸዋል፡፡ ለምሳሌ፡- ጸጋአብ በቀለ የተባለ የፕሮቴስታንት ፓስተር የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ተሐድሶ - ሳታድግ ያረጀች የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በሚለው መጽሐፉ፣ ዳንኤል ተሾመ የሚባል የመካነ ኢየሱስ ቸርች አባል የሆነ ፕሮቴስታንት የቅርብ ዘመኑ (፲፱፻፸፱-፲፱፻፺፱) የተሐድሶ እንቅስቃሴ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሚል ለሁለተኛ ዲግሪ ማሟያ ባዘጋጀው ጽሑፍ እንዲሁም በቀለ ወልደ ኪዳን የተባለ ከሌሊቱ ስንት ሰዓት ነው?በሚለው መጽሐፉ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ስላለው የተሐድሶ እንቅስቃሴ ገልጸዋል፡፡ እነዚህ መጻሕፍት የተሐድሶ እንቅስቃሴን ግብና ከፕሮቴስታንት ጋር ያለውን ድርና ማግነት ቁልጭ አድርገው የሚያሳዩ ናቸው፡፡

፬.፬.ድረ ገጾችና የጡመራ መድረኮች

በዚህ ዘመን ሁሉም ነገር በኤሌክትሮኒክስ መቅረብ የሚችል ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ተሐድሶዎች ኑፋቄያቸውን ለመዝራት ከተጠቀሙባቸው ስልቶች መካከል አንዱ ድረ ገጾችንና የጡመራ መድረኮችን መጠቀም ነው፡፡ ቁጥራቸ ውን በትክክል ማወቅ ባይቻልም በዛ ያሉ የተሐድሶ የጡመራ መድረኮችና ድረ ገጾች አሉ፡፡ ከእነዚህ ድረ ገጾችና የጡመራ መድረኮች መካከል አባ ሰላማ፣ ጮራ፣ ደጀ ብርሃን፣ የዲያ ቆን አሸናፊ መኮንን ገጽ፣ ተሐድሶ ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ፣ ዐውደ ምሕረት፣ ማራናታ፣ ቤተ ፍቅርና የዲያቆን አቤኔ ዘር ተክሉ ገጽ ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡፡

፭.ተገፋን ብሎ መጮህ፡- ጅራፍ ራሱ ገርፎ ራሱ ይጮሃል እንደሚባለው፣ ተሐድሶዎች አጥፊዎቹ፣ ቤተ ክርስቲያንን ለማፍረስ የሚተጉት ራሳቸው ሆነው ሳለ በራሳቸው ድረ ገጾች፣ የጡመራ መድረኮችና በተለያዩ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች በኩል ተገፋን እያሉ ይጮሃሉ፡፡ በ፳፻ወ፮ ዓ.ም የተወሰኑ ዘማርያ አሜሪካ ሔደው በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንና በማኅበረ ቅዱሳን ለተገፉ ሰባክያንና ዘማርያን በሚል ገንዘብ ሲሰበስቡ ነበር፡፡ በ፳፻ወ፬ ዓ.ም በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባዔ የተወገዘው ማኅበረ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን የተባለው የተሐድሶ ድርጅት ደግሞ የካቲት ፮ ቀን ፳፻ወ፮ ዓ.ም በቁ ጥር አ/ሰ/ማ/18/262/06 በማኅበረ ቅዱሳን አቀነባባሪነት የተወሰነብን የውግዘት ውሳኔ እንዲነሣልን ስለመጠየቅ ይመለከታል የሚል ደብዳቤ በአድራሻ ለብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ አስገብቶ ነበር፡፡ ደብዳቤው ርእሱ እንደሚናገረው ማኅበረ ቅዱሳንን የሚያወግዝና ውግዘታችን ይነሣልን የሚል ነው፡፡ ድርጅቱ በደብዳቤው፡-

05menafikanክልላዊ ማኅበር መመሥረት የለባችሁም፣ በአገር አቀፍ የተፈቀደለት ማኅበረ ቅዱሳን ብቻ ስለሆነ የማኅበረ ቅዱሳን አባላት ሁኑ፣ ካልሆናችሁ ግን መናፍቃን ናችሁ፣ ትለያላችሁ በማለት ሲዝትብን የነበረ ማኅበረ ቅዱሳን ከእኔ በቀር ሌላ ማኅበር መኖር የለበትም የሚል አቋም ይዞ በከፍተኛ ሁኔታ በመንቀሳቀስ ራሱን እንደ ልጅ በመቁጠር እኛን ደግሞ እንደ እንጀራ ልጅ እንድንታይና እንድንወገዝ ካለው ጽኑ አቋሙ የተነሣ ምንም ዐይነት የክህደት ትምህርት ሳንማርም ሆነ ሳናስተምር ያለ ምንም መረጃ ይሁን ማስረጃ በአሉቧልታና በትምክህት መናፍቃን ናቸው እያለ በገንዘብ ኀይል በሁሉም ዘንድ የተሳሳተ ግንዛቤ እንዲኖር በማድረግ ሳንጠየቅ፣ ሳንመከር፣ ሳንገሠጽ፣ እውነት ይሁን አይሁን ሳይጣራ፣ ቀርበን በወቅቱም ምንም ዕድል ሳይሰጠን በማኅበረ ቅዱሳን ከፍተኛ ተዋናይነት የውግዘት ውሳኔ መተላለፉ አሳዝኖናል ይላል፡፡

ከዚህም በተጨማሪ አባ ሰላማና ተሐድሶ ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ በሚባሉት ድረ ገጾቻቸው በ፳፻ወ፬ ዓ.ም ተሐድሶዎች ሲወገዙ፣ ከዚያም በኋላ እነሱን ለማስቆም ቤተ ክርስቲያኒቱ በምታደርገው እንቅስቃሴ ሁሉ አገልጋዮቿን የምታሳድድ ቤተ ክርስቲያን እያሉ ስሟን ሲያጠፉ ይሰማሉ፡፡ ለምሳሌ ተሐድሶ ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ኑ! እንዋቀስ በሚል ርእስ ባወጣው ጽሑፍ እንደ አለመታደል ሆኖ ሲኖዶሳችን መናፍቃንን በመደገፍ ጻድቃንን ያሳድዳል፤ ቀን ሲደርስ የእግዚአብሔርን ፍርድ እናያለን፤ እስከዚያው እንክርዳዱ ከስንዴው ጋር ተናንቆ ያድጋል፡፡ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቃሉና በመንፈሱ ተሐድሶ ይጎብኝልን፡፡በማለት ጽፈዋል፡፡ ሊያ የሚባል መጽሔት ላይ ደግሞ የወንድሞች ከሣሽ ማኅበረ ቅዱሳን በሚል ርእስ ሰፊ ሐተታ ያለው ጽሑፍ ጽፈው ነበር፡፡

06menafikanየኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምእመናን ቁጥር በሰባት ሚሊዮን መቀነሱን በይፋ አምናለች፡፡ ቤተ ክርስቲያን እንዲህ ስትል በአንድ ወገን መንጋው አለመጠበቁንና በዚህ ምክንያት መሰረቁን አምናለች፡፡ በሌላ በኩል ግን ሌሎች ሰረቁኝ፣ ወሰዱብኝ ከማለት ያለፈ ምክንያቱን በሚገባ ያጤነችው አትመስልም፡፡ ሌሎች በውጪ አግኝተው ከወሰዷቸው በላይ እንደ ማኅበረ ቅዱሳን ያለ የወንድሞች ከሳሽና አክራሪ ቡድን እኔን አልመሰላችሁምና መናፍቃን ሆናችኋል በሚል ሕገ ወጥ መንገድ ያሳደዳቸው ጥቂቶች አይደሉም፡፡ ምናልባት ለቁጥሩ መቀነስ የማኅበረ ቅዱሳን እጅም እንዳለበት መታመን አለበት ይላል፡፡ (ሊያ መጽሔት ቅጽ ፪ ቁጥር ፳፮ ሚያዝያ ፳፻ወ፭ ዓ.ም)

እስካሁን ያየነው የአገር ውስጡን ጩኸት ነው፡፡ ተሐድሶዎች ከፕሮቴስታንቶች ጋር በመተባበር ይህንን ጩኸት ዐለም አቀፋዊ አድርገውታል፡፡ ዓላማዬ የክርስቲያኖችን ጭቆና ለዓለም ማሳወቅ ነው የሚል ክርስቲያን ሳይንስ ሞኒተር የሚባል አንድ የዜና አውታር አለ፡፡ በቀን ከዐሥር በላይ ከሃይማኖት ጋር ግንኙነት ያላቸውን ዜናዎች ያወጣል፡፡ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮችን በደል አውጥቶ አያውቅም፡፡ በሶርያ በየዕለቱ ከሞት ጋር ስለሚታገሉት ኦርቶዶክሳውያን፣ ስለ ፓትርያርኩ ለዐሥራ አምስት ቀናት የሔዱበት አድራሻ አለመታወቅ የዘገበው ነገር አልነበረም፡፡ ያልዘገበው ግን ባለማወቅ ሳይሆን በዓላማ ነው፡፡ ለዚህ ድርጅት ክርስቲያን ማለት ፕሮቴስታንት ነው፡፡ የሚያሰማውም የእነሱን ጩኸት ነው፡፡

07menafikanተቀማጭነቱን አሜሪካ ያደረገ ኦፕን ዶርስ የሚባል ድርጅት አለ፡፡ ድርጅቱ አንድሪው ቫን ደር ቢጅል በሚባል ግለሰብ በ፲፱፻፶፭ የተመሠረተ መንግ ሥታዊ ያልሆነ የክርስቲያን ድርጅት ነው፡፡ እንደ ራሳቸው አገላለጽ በግለሰቦች መዋጮ የሚተዳደር ነው፡፡ ከ፲፱፻፺፩ ጀምሮ በዓለም አቀፍ ደረጃ በክርስቲያኖች ላይ ከፍተኛ ጭቆና የሚያደርሱ የአምሳ አገራትን ዝርዝር ያወጣል፡፡ በዚህ ድርጅት ዘገባ መሠረት አገራችን ኢትዮጵያ ክርስቲያኖችን ከሚጨቁኑት አምሳ አገራት መካከል ባለፉት አምስት ዓመታት ማለትም በ2011 ፵፫ኛ፣ በ2012 ፴፰ኛ፣ በ2013 €“፲፭ኛ፣ በ2014€“ ፲፯ኛ እና በ2015€“ ፳፪ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች፡፡ ድርጅቱ ባለፉት ሁለት ዓመታት ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው የክርስቲያኖች ጭቆና ከዓመት ወደ ዓመት እየቀነሰ ነው ይላል፡፡ ይህ አገላለጽ ሲብራራ ተሐድሶዎች ቤተ ክርስቲያንን ለማፍረስ የተሻለ ዕድል እያገኙ ነው ማለት ነው፡፡

ተቋሙ በ2013 ባወጣው ዘገባው ስለ ኢትዮጵያ እንዲህ የሚል ቃል አስቀምጧል፡-

Ethiopia has a complex mix of persecution dynamics.Ecclesiastical arrogance is the country historical persecution dynamic. For years, the Ethiopian Orthodox Church (EOC) has been seriously persecuting believers who have left their ranks or joined the renewal movements within the EOC. (World Watch List 2013)

ኢትዮጵያ ዘርፈ ብዙ የሆነ ጭቆና የሚካሔድባት አገር ናት፡፡ ቤተ ክህነታዊ እብሪትየአገሪቱ ታሪካዊ የጭቆና መታወቂያ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ወጥተው አዲስ የመጣውን የፕሮቴስታንት እምነት እና በቤተ ክርስቲያን ውስጥ እያሉ የተሐድሶውን ጎራ የተቀላቀሉትን አማኞች ክፉኛ ትጨቁናለች፡፡ካለ በኋላ ቀጥሎ፡-

The fanatic group inside the EOC (€˜Mahibere Kidusan) is a growing threat for non-traditional Protestants and renewal movements within the EOC. The group allegedly wants to control the government policies to restrict the activities of other religions. Mahibere Kidusan is currently riding high. (World Watch List 2013)

08menafikanበኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሥር የሚገኘው ማኅበረ ቅዱሳን የሚባለው አክራሪ ቡድን ለፕሮቴስታንቶች እና በቤተ ክርስቲያኒቱ ውስጥ ላሉ ተሐድሶዎች ታላቅ ሥጋት ነው፡፡ ቡድኑ ሌሎች የእምነት ቤቶች የሚያደርጓቸውን እንቅስቃሴዎች ለመገደብ የመንግሥትን ፖሊሲዎች በጥብቅ መቆጣጠር በጥብቅ ይፈልጋል፡፡  በአሁኑ ጊዜ ማኅበሩ በፍጥነት እያንሠራራ ነው፡፡

2013 ማለት በኢትዮጵያ ተሐድሶ ዎች የተወገዙበት ዓመት ማግስት ማለት ነው፡፡ ለዚህም ነው እየተጨቆንን ነው የሚለው ጉዳይ ዓለም አቀፋዊ አጀንዳ እንዲሆን እና ፖለቲካዊ አቅጣጫ እንዲይዝ ለማድረግ የሞከሩት፡፡ ተሐድሶዎች የዘረጉት መስመር የት እንደሚደርስ ወይም ተሐድሶው በማን ግፊት እየተመራ እንደሆነ ይህ አገላለጽ ሁነኛ ማሳያ ነው፡፡ ኦርቶዶክስ ሳይሆኑ ኦርቶዶክስ ነን በማለት የቤተ ክርስቲያንን አስተምህሮ ለመቀየር ብሎም ቤተ ክርስቲያንን ለመክፈል የሚሠሩ ወገኖች ቁጥራቸው በርከት ባሉባቸው ቦታዎች ኦርቶዶክሶችን በማሸማቀቅ፣ በማስፈራራትና በመዝለፍ ቤተ ክርስቲያንን ለማጥፋት የተነሡት እነርሱ ሆነው ሳለ ራሳቸው የሠሩትን ግፍና በደል ለቤተ ክርስቲያን አድርገው ተሳደድን ብለው ይጮሃሉ፡፡ ብዙዎቻችንም ዐውቀንም ይሁን ሳናውቅ የእነርሱ ጩኸት ደጋፊዎችና ጠበቆች እየሆን ነው፡፡ የራስን አጥብቆ መያዝና ለሌላ ወገን አላስደፍርም ማለት ማስወቀስና ማስተቸት ከጀመረ ቆይቷል፡፡

እነርሱ እነዚህን መንገዶች ተጠቅመው ቤተ ክርስቲያንን የማዳከም፣ ዶግማና ቀኖናዋን የመቆነጻጸል ተግባራቸውን ቀጥለውበታል፡፡ እኛ ይህ ሁሉ ሲፈጸም ምን ያከናወንነው ተግባር አለ ተብለን ራሳችንን ብንጠየቅ መልሳችን ምንም የሚል ነው፡፡ ስለዚህ ቢያንስ የችግሩን አሳሳቢነትና የአደጋውን አስከፊነት ጠንቅቀን ማወቅና መንገዶቻቸውን ለመዝጋት የሚያስችሉ ሥራዎችን መሥራት ይገባናል፡፡ እነርሱ በገንዘብ ለማታለል ምቹ ሁኔታ ያገኙት እኛ አብነት ትምህርት ቤቶችን እና ገዳማትን ባለመደገፋችን መሆኑን መረዳት አለብን፡፡

ይቆየን

2015 ኖቬምበር 5, ሐሙስ

የተሐድሶን ምንነት ሳታውቁ፣ ስለ ተሐድሶዎች ማንነት አትጠይቁ!!

አትም ኢሜይል
ጥቅምት 23 ቀን 2008 ዓ.ም
ክፍል አንድ
በተሐድሶ ዙሪያ በስምዐ ጽድቅ ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ጋዜጣ የተጻፉትን ጽሑፎች ከክፍል አንድ ጀምሮ ተከታትለን እናቀርብላችኋለን፡፡
ስለ ነገረ ተሐድሶ ለመጻፍ የሚነሣ ሰው ከሚቸገርባቸው ጉዳዮች አንዱ €œከእንቅስቃሴው ውስጥ ምኑ ላይ ባተኩር አንባብያን ላይ የሚፈለገውን ግንዛቤ መፍጠር እችላለሁ€ የሚለው ነው፡፡ ስለ ታሪካዊ ዳራውና አመጣጡ፣ ስለ ምንነቱ፣ ስለእንቅስቃሴው መሪዎች ማንነት፣ ስለ ተሐድሶዎች €œአስተምህሮ€፣ ከፕሮቴስታንት ጋር ስላለው አንድነትና ተመሳሳይነት (ልዩነት ስለሌለው) ወይስ ስለ ምን መጻፍ ቀላል፣ የሁሉንም ልብ የሚያኳኳ፣ ለመፍትሔው የሚያነሣሣ ይሆናል የሚለው የጸሐፊውን ልብ የሚያስጨንቅ ጥያቄ ነው፡፡ እኛም ከምኑ ጀምረን ወደ የት መሔድ እንዳለብን ብንቸገርም የእንቅስቃሴውን ምንነትና መገለጫ ሳያውቁ ወደ ሌላ ርእሰ ጉዳይ መግባት ግን መልካም መስሎ አይታየንም፡፡
ከዚህ በፊት በአንድ ጽሑፍ ላይ እንደገለጽነው ተሐድሶ እንቅስቃሴ እንጂ እምነት ስላልሆነ የራሱ ዶግማ፣ ቀኖና እና ሥርዓት የለውም፡፡ ይህንንም ራሳቸው ባዘጋጁት ጽሑፍ ላይ:- €œወደፊት ከምንሠራቸው ሥራዎች አንዱ የሃይማኖት ምዕላድ ማዘጋጀት ነ€ ስላሉ እስካሁን በጋራ የተስማሙበት ቋሚ የእምነት መሠረት እንደሌላቸው ሆነው የቀረቡበት ነው፡፡ ሆኖም ግን እስካአሁን እየገለጡት ካለው መረዳት እንደሚቻለው የተስማሙበት ዶግማና ቀኖናቸው ቤተ ክርስቲያንን ማፍረስና ፕሮቴስታንታዊ ማድረግ የሚለው ነው፡፡ በዚህ ምክንያት የተሐድሶን ምንነት በቀላሉ መግለጽ ከባድ ይሆናል፡፡ ምክንያቱም እንደ ቡድኑና እንደ ግለሰቦች አቅም የሚወሰን እንጂ ቋሚ የሆነ አስተምህሮ ስለሌለው፡፡ የእንስሳትን ትርጉም ከመናገር ምሳሌ መስጠቱ እንደሚቀለው ሁሉ፣ ለተሐድሶም ትርጉም ከመስጠት ይልቅ ዓላማውንና ተግባሩን ማሳየት የተሻለ ገላጭ ስለሚሆን በእርሱ እንጀምራለን፡፡
ተሐድሶ በአገራችን ዐውድ ሲታይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ዶግማ፣ ቀኖና፣ ትውፊት እና ሥርዓት በመቀየጥ፣ በመቀየር ወይም በማጥፋት ፕሮቴስታንት ማድረግ፣ ምእመናንን ደግሞ በእምነት ስም አታሎ አስገብቶ ዓለማዊ (ሴኪዩላር) የማድረግ እንቅስቃሴ ነው፡፡ ፕሮቴስታንቲዝም በምዕራባውያን ዘንድ እምነትነቱ ቢያልፍበትም በእኛ አገር ግን እስከ አሁን ድረስ €œሃይማኖታዊ መልክ እንደ ተላበሰ ስለሆነ ተሐድሶን ለፕሮቴስታንቲዝም ዓላማ ማስፈጸሚያ መሣሪያነት እየተጠቀሙበት ነው፡፡ ተሐድሶና ፕሮቴስታንቲዝም በአካሔድ፣ በስልትና በግብ አንድ ዐይነት ናቸው፡፡ የሁለቱም ግብ ኦርቶዶክሳውያንን ፕሮቴስታንት ከዚያም ዓለማዊ ማድረግ ነው፡፡ ይህንን ቁርኝታቸውን መጋቢት ፳፻፮ ዓ.ም በወጣው ከሣቴ ብርሃን በሚባል ጋዜጣቸው ሲገልጹት፡-

ባለፉት አሥርና አሥራ ሁለት ዓመታት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንና በወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት መካከል ስላለው መሠረታዊ ልዩነት ለማጥናት ሞክረናል፡፡ ያገኘነው ውጤት እኛ እንድትኖረን የምንፈልጋት የታደሰችና ጥንታዊቷ የኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያናችን ከወንጌላውያኑ ጋር ያላት ልዩነት የአምልኮት ባህልና የቋንቋ ብቻ መሆኑን በሚገባ ተገንዝበናል ይላሉ፡፡
ይህንን የተናገረው ገድል ወይስ ገደል€ የሚለውን መጽሐፍ የጻፈው ጌታቸው ምትኩ ነው፡፡ ጌታቸው ምትኩ በሌላ ገጽ ላይ ስለ ከሣቴ ብርሃን የተሐድሶ ማኅበር አመሠራረት፣ ስለ ደረሰባቸው ስደት€ እና ስለ ወሰዱት እርምጃ ሲገልጽ ደግሞ እንዲህ ብሏል፡-
በተሐድሶ ጥያቄ ሰበብ በማኅበር ከተሰበሰቡት የቤተ ክርስቲያኒቱ አገልጋዮች ብዙዎች ከሥራ የመባረር፣ ከቤተሰቦቻቸው የመለያየትና ማኅበራዊ ተቀባይነትን የማጣት ዕጣ ሲገጥማቸው የወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናትን ድጋፍ በመሻት፣ በነጻነት ቃለ እግዚአብሔርን ለማወቅና ለመማር እንዲሁም አምልኮተ እግዚአብሔርን ለመፈጸም በገፍ ነጉደዋል፡፡ በእርግጥ በመሠረታዊው የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ረገድ ከወንጌላውያን ጋር የጎላ ልዩነት ባለመኖሩ ወደዚያ መሔዳቸው ክፋት ባይኖረውም €ተሐድሶውን ጎድቶታል፡፡

ይህ ገለጻ የተሐድሶ ዓላማና ግብ ምን እንደሆነ በግልጽ ያሳያል፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከሦስት ሺ ዓመታት በላይ እግዚአብሔርን ስታመልክ፣ ላለፉት ሁለት ሺ ዓመታት ወንጌልን ስትሰብክ እንዳልኖረች ሁሉ ዛሬ ክርስቶስን እንዳልሰበከች በድፍረት የሚናገሩ የውስጥ እሾሆች በቀሉባት፡፡ ባያውቁት ነው እንጂ €œመታደስ አለባት የሚሉት ሰዎች ራሳቸው እግዚአብሔርን ያወቁት በእናት ቤተ ክርስቲያን አማካኝነት ነበር፡፡ ለቤተ ክርስቲያን ወንጌል እንደ አዲስ ሊሰበክላት ይገባል ብለው እየተሳደቡ የማርቲን ሉተርን ዓላማ ለማስፈጸም የተቋቋሙትን ድርጅቶች ደግሞ €œወንጌላውያን€ ብለው ጠሯቸው፡፡ እነቅዱስ አትናቴዎስ ከአርዮስ ጋር፣ እነቅዱስ ቄርሎስ ከንስጥሮስ ጋር፣ እነቅዱስ ዲዮስቆሮስ ከልዮን ጋር እስከ ነፍስ ሕቅታ የተጋደሉላት ንጽሕት ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ከሉተር ድርጅቶች ጋር በአስተምህሮ አንድነት ስትፈረጅ ከመስማት በላይ የሚያም ነገር የለም፡፡

የተሐድሶ እንቅስቃሴው ከተጀመረ በጣም ጥቂት ጊዜ ቢያስቆጥርም የመጀመሪያዎቹ የተሐድሶ መነኮሳት ኅብረት ከተወገዙበት ከ፲፱፻፺ ዓ.ም ወዲህ ግን መልኩን እየቀየረና እየተስፋፋ እንደመጣ ግልጽ ነው፡፡ በተለይም በቅርብ ጊዜ (፳፻ወ፬ ዓ.ም) በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ሰባት ማኅበራትና ዐሥራ ስድስት ግለሰቦች ከተወገዙ በኋላ ሁላችንም የተሐድሶ ጉዳይ ያበቃ መስሎን እጃችንን አጣጥፈን ተቀምጠን ሳለን እነርሱ መረባቸውን ዓለም አቀፋዊ አድርገው እየተንቀሳቀሱ ነው፡፡ ከአሜሪካ እስከ እንግሊዝ፣ ከዱባይ እስከ ኢትዮጵያ የሚደርስ ሰፊ መረብ ዘርግተዋል፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ከተናጠል እንቅስቃሴ በጋራ መሆን ይሻላል በሚል ከዐሥር በላይ የሚሆኑ የተሐድሶ ማኅበራት €œየወንጌል አገልግሎት ማኅበራት ኅብረት€ የሚባል ማኅበር አቋቁመዋል፡፡ ኅብረቱ በከሣቴ ብርሃን አነሣሽነት የተመሠረተ የተሐድሶ ኅብረት ነው፡፡ ሁለተኛ ዓመት የምሥረታ በዓሉን አስመልክቶ መጋቢት ፳፻ወ፯ ዓ.ም ባወጣው ልዩ ዕትም መጽሔት ላይ ኅብረቱ የካቲት ፴/፳፻ወ፭ ዓ.ም እንደ ተመሠረተ፣ መስከረም ፲፮/፳፻ወ፯ ዓ.ም ከፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ሕጋዊ ዕውቅና እንዳገኘ ገልጸዋል፡፡ በመጽሔቱ የኅብረቱ ሥራዎች ተብለው ከተጠቀሱት ጉዳዮች መካከል፡-

የጋራ የሆነ የእምነት መግለጫ ማዘጋጀት፣

የጋራ የሆነ በየደረጃው ላሉ የሚያ ለግል የማስተማሪያና የማሠልጠኛ ማቴሪያል ማዘጋጀት፣

የቤተ ክርስቲያኒቷ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሚጠቀሙበት የጋራ የሆነ ሥርዐተ ትምህርት መቅረጽ፣

የቤተ ክርስቲያኗን ብርቱ ጎንና ደካማ ጎን ለይቶ በማውጣትና በመጽሐፍ ቅዱስ በመመዘን ሊጸና የሚገባው እንዲጸና፣ ሊወገድ የሚገባው እንዲወገድ፣ ሊሻሻል የሚገባው እንዲሻሻል፣ ቤተ ክርስቲያኒቱ ልትይዘው ሲገባ ያልያዘችውን መጽሐፍ ቅዱሳዊ እውነት ደግሞ እንድትይዝ ለማድረግ ብርቱ የሆነ የጋራ ተሐድሶአዊ ምእላድ ማዘጋጀት የሚሉት ይገኙበታል በማለት የወደፊት ዕቅዳቸውን ገልጸዋል፡፡

ተሐድሶ እስከ አሁን እንቅስቃሴ ብቻ እንደ ነበረ አሁን ግን እየሰፋና ወደ ተቋምነት እያደገ እንደሆነ ይህ ሁነኛ ማሳያ ነው፡፡ እነርሱ በየጽሑፎቻቸው ኦርቶዶክሳዊ አይደለንም፣ የፕሮቴስታንት ቅጥያዎች ነን እያሉ እየገለጹ ዛሬም ስለ ተሐድሶ መኖር አለመኖር የሚከራከሩ የዋሀን አሉ፡፡ እንቅስቃሴው ገባን የሚሉት እንኳን ማወቅ የሚፈልጉት ተሐድሶዎች እነማን እንደሆኑ እንጂ ስለ እንቅስቃሴው ምንነት፣ ስፋት፣ አደጋና ከእነሱ ስለሚጠበቀው ድርሻ አይደለም፡፡ በመጀመሪያ የተሐድሶዎችን ማንነት ማወቅ ብቻውን ዕውቀት አይደለም፡፡ ለሚዲያ ፍጆታ ካልሆነ በስተቀር ለቤተ ክርስቲያን የሚሰጠው ጥቅምም የለም፡፡ ስለ ተሐድሶ ሲታሰብ የሰዎችን ማንነት ከማወቅ ያለፈ ሥራ ማሰብ ይጠይቃል፡፡ ሁሉ ነገር እንዲነገረን መፈለግ ሳይሆን መገለጫ ቸውን ዐውቀን በዚህ መሠረት ማንነታቸውን መለየት እና መመዘን የእኛ ሥራ መሆን አለበት፡፡

ብዙ ሰዎች የሚጠይቋቸው የተለመዱ ጥያቄዎች አሉ፡፡ €œእገሌ ተሐድሶ ነው? ከሆነ ለምን ከቤተ ክርስቲያን አልታገደም? ለምን አልተወገዘም? ስለ እመቤታችን እያስተማረ ለምን ተሐድሶ ይባላል? ግእዝ እየጠቀሰ ለምን ኦርቶዶክስ አይደለም ትላላችሁ?የሚሉ ጥያቄዎች ይሰማሉ፡፡ ይህ ብቻ አይደለም፣ €œእገሌ በጣም የምንወደው ሰባኪ ስለሆነ ተሐድሶ እንዳትሉት፣ እገሊት ስትዘምር ድምጿ ስለሚያምር እንዳትነኩብን€ ብለው ሰዎችን ከቤተ ክርስቲያን በላይ ያስቀመጡም አሉ፡፡ እነዚህ ሁሉ የተሐድሶን ምንነት ካለ መረዳት የሚመጡ ችግሮች እንደሆኑ ግልጽ ነው፡፡ በመጀመሪያ ይህንን እንወቅ፡፡ ግእዝ የሚጠቅስ፣ ስለ እመቤታችን የሚያስተምር (ስልት ስለሆነ)፣ ወይም ድምጹ የሚያስገመግም ሰባኪ ሁሉ ኦርቶዶክሳዊ አይደለም፡፡ ራሳቸው አንድ ሥልጠና ላይ የተናገሩትን ከዚህ መጥቀስ ይበጃል፡፡

ስትሰብኩ ኢየሱስ ብቻ አትበሉ፣ መድኀኔ ዓለም፣ መድኀኒታችን አምላካችን፣ እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ በሉ፡፡ ከቻላችሁ ግእዝ ጥቀሱ፣ ግእዝ ከተናገራችሁ ትታመናላችሁ፣ ሕዝቡ ይሰማችኋል፡፡ ከአዋልድ መጻሕፍትም ለምሳሌ፡- ከውዳሴ ማርያም፣ ከሰዓታት፣ ከዚቅ፣ ከመልክአ መልኮች ጠቅሳችሁ ማስተማር ትችላላችሁ፡፡ ስለ ማርያምም አስተምሩ፣ ድንግል ስለመሆኗ፣ በከብቶች በረት ኢየሱስን ስለ መውለዷ፣ በስደት ስለ መንገላታቷ አስተምሩ፡፡ ብቻ ዓላማችሁን ሳትስቱ ሰዎች በሚሰሟችሁና በምትታመኑበት መንገድ ካስተማራችሁ ሕዝቡን መያዝ ትችላላችሁ፣ ቆይታችሁ ዋናውን ትምህርት ታስተምራላችሁ ብለዋል፡፡

ስለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም መናገር የማደናገሪያ ስልት እንጂ የስብከታቸው ዓላማ እንዳልሆነ መረዳት አለብን፡፡ በመሆኑም ቤተ ክርስቲያን በማታውቃቸው የቴሌቪዥን መርሐ ግብራት የእመቤታችንን ሥዕል ከጐናቸው አድርገው ቢያስተምሩ ተአማኒነትን ለማግኘት እንጂ በእመቤታችን አማላጅነት ወይም በሥዕላት ክብር አምነው እንዳልሆነ እነርሱም እኛም እናውቃለን፡፡ ስለ እመቤታችን እናስተምራለን ብለው ጀምረው ስለ እመቤታችን አንድም ነገር ሳይናገሩ €œጸሎተኞች፣ ጸሎታችሁ ያልተሰማው በስሙ ስለማ ትጸልዩ ነው ብለው በቅዱሳን ስም መጸለይ እንደማይገባ ሲናገሩ ካልገባን እየበለጡን ነው፡፡ ታዲያ ይሄ ኦርቶዶክሳዊ በሚመስል ርእስ እኛን በመሸንገል ኑፋቄያቸውን ለማስገባት ምቹ ሁኔታ እየፈጠሩ እንጂ ስለ ቅዱሳን ክብር በመቆርቆር እየተናገሩ ነው የሚያስብል ምን ነገር አለው?

እነሱም ይህ ስልት የበለጠ አዋጭና ለአቅጣጫ ማስቀየሪያ እንደሚበጅ ዐውቀው በደንብ እየተጠቀሙበት ነው፡፡ እነሱ ቅኔ ሲቀኙ፣ የተማሩባቸውን እና ያስተማሩባቸውን ወይም ያገለገሉባቸ ውን አጥቢያዎች ሲናገሩ፣ የእኛ አጀንዳ የተሐድሶ አደገኛነት ሳይሆን የተናገሩት ጉዳይ እውነትነት ላይ ይሆናል፡፡

ለምሳሌ ብንጠቅስ የሰሜኑን የተሐድሶ እንቅስቃሴ (በተለይ አብነት መምህራን ላይ ትኩረት አድርጎ የሚንቀሳቀስ) ከጽጌ ሥጦታው ጋር ሆኖ የሚመራው ሙሴ መንበሩ የሚባል ግለሰብ፡- €œቤተ ክርስቲያን እንደምታውቀኝ ለማረጋገጥ እነብሴ ሣር ምድር ሔዳችሁ መጠየቅ ትችላላችሁ ብሎ ስድስት አድባራትን ይጠራል፡፡ ከዚያም ቅኔ ይቀኛል፡፡ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ መሪ ጌታ እንደሆነም ይናገራል፡፡ የሚገርመው ግን ይህንን ሁሉ የሚልበት ቪሲዲ ርእስ ኦርቶዶክስ መልስ ካላት እኛም ጥያቄ አለን€ የሚል ነው፡፡ የቪሲዲው ርእስ ራሱ አቅራቢዎቹ ኦርቶዶክሳውያን እንዳልሆኑ አፍ አውጥቶ እየተናገረ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ነው ያለነው ብለው ሊያሳምኑን ይፈልጋሉ፡፡ አንዳንድ የዋሀን ደግሞ ይህንን ተከትለው €œኦርቶዶክሳዊ ናቸው፣ ይሄው ቅኔ እየተቀኙ፣ የቀደሱበትን ቦታ እየተናገሩ€ ብለው ይከተሏቸዋል፡፡

ሌላ አንድ ማሳያ ብናይ አንድ የመጋቤ ሐዲስነት ማዕርግ የተሰጠው ሰው የጻፈው መጽሐፍ ላይ እንዲህ የሚል አሳብ አስፍሯል €œይህ ሄኖክ የተናገረውና በሐዋርያው በይሁዳም የተጠቀሰውን ትንቢት ቃል በቃል በዚህ በ፷፮ቱ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ባይገኝም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን በምትጠቀምበት በሰማንያ አሐዱ መጽሐፍ (መጽሐፈ ሄኖክ) ላይ ተጠቅሶ ይገኛል€ ይላል፡፡ ይህ ንግግር ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በአፍኣ ያለ ሰው የተናገረው እንጂ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መድረክ ላይ ቆሞ የሚሰብክ ሰባኬ አይመስልም፡፡ የገጸ ንባቡ አሳብ መጽሐፍ ቅዱስ የሚባለው ስድሳ ስድስቱ እንደሆነ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሌላ የተለየ መጽሐፍ ቅዱስ እንዳላት የሚያደርግ ነው፡፡ ይኸው ሰው በአንድ ወቅት በአንድ የቴሌቪዥን መርሐ ግብር ላይ €œእኔ ኢትዮጵያ ውስጥ እንደ ተቋም ተሐድሶ አለ ብየ አላምንም፣ ካለ ቢሮውን ቢያሳዩን€ ብሎ ሲከራከር የነበረ መሆኑን ስናስብ ብዙ ነገር ያስጠረጥራል፡፡ ከዚህ ንግግሩ በኋላ ደግሞ ቦንጋ ሔዶ በዝግ ስብሰባ €œተሐድሶ የሚባሉ የተወሰኑ አካላት አሉ፣ ብዙዎቹ ግን ማኅበረ ቅዱሳን ያሳደዳቸው ናቸው€ ብሎ ማኅበረ ቅዱሳንን በመክሰስ ራሱን ነጻ ለማድረግ ሲተጋ ነበር፡፡
እነርሱ ለእኛ ማደናገሪያና መከራከሪያ የሚሆኑ ጉዳዮችን እየጫሩ እኛ በማይጠቅመው ነገር ስንወጠር ሥራቸውን እየሠሩ ነው፡፡ በዚህም ምክንያት ተረፈ አርዮሳዊ የሆኑ ሰዎች ቤተ ክርስቲያን በማታውቀው ግን በቤተ ክርስቲያን ስም በሚተላለፍ መርሐ ግብር ላይ €œበምድር ላይ ሞቼ ነበር ብሎ ቆሞ ሲያወራ የሰማነው ወይም ሲናገር ያየነው ፍጡር አልነበረም፣ የለምም፣ ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ በቀር፡፡ የሚል ስብከት እንዲሰበክ ዕድል ፈጠርንላቸው፡፡ በብዙ ድካምና በብዙ መከራ የሚገባባትን የእግዚአብሔርን መንግሥት መጠጥ ቤት የመግባት ያህል አቃለው ሰው በልቡ አምኖ ይጸድቃል፣ በአፉ መስክሮ ይድናልና፣ መንገዱ ረጅም አይደለም ወገኖቼ፤ ውጣ ውረድ የለበትም፡፡ የምትከፍለው አይደለም፣ የተከፈለበት ነው፡፡ አንተ የምታደርገው ነገር አይደለም፣ የተደረገልህ ነው፡፡ የምትሆነው አይደለም፣ የሆነልህ ነው፡፡ ይህንን ብታምን በአፍህ ብትመሰክር ትድናለህ፡፡ ከምንድንነው የምትድ ነው? ከኀጢአትና ኀጢአት ከሚያመጣው ሞት€ በማለት በወንጌል ቃል ይሳለቁበት ጀመር፡፡ እንዲያውም ዋናው ዓላማቸው በጸጋው ድናችኋልና አትድከሙ በመሆኑ ዕለት ዕለት የሚሉን €œየእግዚአብሔር ቃል የሚነግረን መዳን ማለት በልብ ማመንና በአፍ መመስከር እንጂ እኛ በድካም የለመድነውን አይደለም፡፡ እየታገልን አንዴ ሲሳካ አንዴ ሳይሳካ እያለቃቀስን የምንኖረውን አይደለም€ የሚል ያለፈበት የፕሮቴስታንት €œስብከት€ ነው፡፡
ይህ ሁሉ የሆነው በእኛ መተኛት እንጂ በእነርሱ ትጋት እንዳልሆነ ሁላችን ውስጣችንን ስንፈትሽ የምንረዳው እውነት ነው፡፡ ስለ ጉዳዩ ትኩረት ሰጥተን ያልሰማንበት ጊዜ ረጅም ነው፣ እስካሁንም ከዚህ አዚም ያልተላቀቅን እንኖራለን፣ ጉዳዩን የምናውቀውም ትኩረት ሰጥተን የሰማንበት ጊዜ ሩቅ እንዳልሆነ እናውቃለን፡፡ ለቤተ ክርስቲያን ከማድላት ይልቅ ለሰዎች የወገንንበት ጊዜ ብዙ ነው፡፡ ዛሬም ዓላማቸውን ራሳቸው ስለገለጹት እንጂ እኛ መርምረን ደርሰንበት አይደለም፡፡ ከእንቅልፋችን እስካልነቃን ድረስ ችግሩ ይቀጥላል፡፡ በመጀመሪያ አንድ ሰው ኦርቶዶክሳዊ ለመባል መስፈርቱ ኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮ ማስተማሩ እንጂ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ነኝ ማለቱ አይደለም፡፡

ተሐድሶ ማለትም ጫካ ውስጥ የኖረ አውሬ ማለት ሳይሆን ከቤተ ክርስቲያን ጉያ የወጣ ጠላት ነው፡፡ ስለዚህ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ነበሩ፣ አሁንም አሉ፣ ነገር ግን በትምህርታቸውም ሆነ በዓላማቸው ከቤተ ክርስቲያን ወገን አይደሉም ነው የተባለው፡፡ እነ አርዮስም እስከሚወገዙ ድረስ ጳጳስ ነበሩ፡፡ ከተወገዙም በኋላ ብዙዎችን ከመንገድ ያስወጡት መናፍቃን ነን ብለው ሳይሆን ክርስቲያኖች ነን ብለው ነው፡፡ ዛሬም ሰዎች ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ተምረናል፣ ቀድሰናል፣ እናም ኦርቶዶክሳውያን ነን ቢሉም ትመምህርታቸው ግን ኦርቶዶክሳዊ አይደለም፡፡ ቤተ ክርስቲያን የቤተ ክርስቲያን አባቶች ብላ ዕውቅና የሰጠቻቸው ቅዱሳን አበው ይህንን ዕውቅና ሲሰጡ መስፈርቶቹ የቅድስና ሕይወት፣ ኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮ፣ የቤተ ክርስቲያን ምስክርነትና ጥንታዊነት ናቸው እንጂ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ያላቸው የአገልግሎት ቦታ አይደለም፡፡

ስለዚህ ከዚህ በኋላ ተሐድሶዎች እነማን እንደሆኑ ንገሩን ማለት መብቃት አለበት፡፡ ሚዛኑ ካለን በሚዛን መዝነን ማንነታቸውን ማወቅ ከባድ አይሆንም፡፡ ምናልባት ማንነታቸውን የምንጠይቀው የራሳችንን ሥራ ለማቃለልና ሥናወራ እንዲመቸን ለማድረግ ካልሆነ በቀር በሥራቸው ታውቋቸዋላችሁ ስለተባልን በሥራቸው መመዘን ነው፡፡ በድምጽ መጎርነን እና ማማር፣ በመልክ ማማር፣ በታዋቂነት፣ ወዘተ ስም ሰዎችን ከቤተ ክርስቲያን የምናስበልጥ ከሆነ ክርስትና ውስጥ አይደለንም ማለት ነው፡፡ ስለ እንቅስቃሴው ሲነገረን ጆሮ ዳባ ልበስ የምንል ከሆነ እግዚአብሔርን ከመስማት ይልቅ እናንተን እንሰማ ዘንድ በእግዚአብሔር ፊት የሚገባ እንደሆነ ቁረጡ እኛስ ያየነውንና የሰማነውን ከመናገር ዝም ማለት አንችልም አሉዋቸው€ /የሐዋ. ሥራ ፬፥፲፱-፳/ በማለት የተናገሩትን የአባቶቻችንን የሐዋርያትን አሰረ ፍኖት ከመከተል ይልቅ በከንቱ ውዳሴ ተጠልፎ አርዮስን ከውግዘቱ በመፈታቱ እንደተቀሰፈው አኪላስ መሆናችንን መረዳት ይገባናል፡፡ በሃይማኖታችን እያሾፍንበት እንደሆነ ማወቅም ይገባናል፡፡ ቤተ ክርስቲያን የገሃነም ደጆች አይችሏትም ስለ ተባለች ሁሉንም ፈተናዎች አሸንፋ እስከ ዓለም ፍጻሜ ትዘልቃለች፡፡ እኛ ግን ነቅተን ቅጽራችንን ካልጠበቅን የተቀደሰውን አሳልፈን እንሰጣለን፣ ከሰማያዊ ርስትም ዕጣ ፈንታ እናጣለን፡፡ ስለዚህ በዚህ ዘመን ጸንተን ብንገኝና በአቅማችን እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ? ብለን ብንነሣ፣ በጠላት የተዘጋጀልን ፈተና የተሐድሶ እንቅስቃሴ መሆኑን ተረድተን መንፈሳዊ መሣሪያዎቻችንን ሁሉ ታጥቀን መነሣት አለብን፡፡ ፈተና ከሌለ ጽናት፣ ጽናት ከሌለ ድል፣ ድል ከሌለ የድል አክሊል አይገኝምና፡፡

ምንጭ፡- ስምዐ ጽድቅ ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ፣ 23ኛ ዓመት ቁጥር 1/ቅጽ 23፣ቁጥር 329 መስከረም 16-30 ቀን 2008 ዓ.ም

ይቆየ

2015 ኖቬምበር 2, ሰኞ

ከቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ


አትም ኢሜይል
ጥቅምት 22 ቀን 2008 ዓ.ም
06tikm sinodosየኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ከጥቅምት 11-22 ቀን 2008 ዓ.ም ሲያካሔድ የቆየውን መደበኛ ስብሰባ በዛሬው ዕለት አጠናቋል፡፡

ከቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠውን መግለጫ እንደሚከተለው አቅርበነዋል፡፡
01tikm sinod
02tikm sinod
03tikm sinod
04tikm sinod
05tikm sinodos

ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ: በአ/አበባ ሀ/ስብከት በቅዱስ ሲኖዶስ የተመደበቡትን ሓላፊነት እንዳይወጡ መደረጋቸውን ተናገሩ፤“ሥልጣንን አላግባብ በመጠቀም ዐቢይ የሕግ ግድፈት ተፈጽሟል


?
ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ፡-
  • ከቅዱስ ፓትርያርኩም ኾነ ከጠቅላይ ጽ/ቤቱ ጋር በመልካም የሥራ ግንኙነት ላይ ነበርኩ
  • የአ/አበባ ሀ/ስብከትን ኹለት ሥራ አስኪያጆች የመለመለውና ያቀረበው አካል አይታወቅም
  • ሒሳቡን እንዲያንቀሳቅሱ ሌላ ፈራሚ ሊቀ ጳጳስ የተመደቡበት ኹኔታ አሳዛኝ ክሥተት ነው
  • በረዳት ሊቀ ጳጳስነት የመደበኝ ምልዓተ ጉባኤው፣ ለቤተ ክርስቲያን የሚበጅ መፍትሔ ይስጠኝ
በምልአተ ጉባኤው ስብሰባ፡-
  • ልዩ ደንብና መመሪያ ባልወጣበት የፓትርያርኩ ልዩ ሀ/ስብከት መኾኑ ክፍተት ፈጥሯል
  • የፓትርያርኩ፣ የረዳት ሊቀ ጳጳሱና የሥራ አስኪያጁ ተግባርና ሓላፊነት መታወቅ አለበት
  • በሚሻሻለው ቃለ ዐዋዲ የሦስቱ ሓላፊዎች ሥልጣንና ተግባር ተካቶ እንዲቀርብ ተወስኗል
  • ፓትርያርኩ ያለረዳት ሊቀ ጳጳሱ ምርጫ ሥራ አስኪያጆችን በመሾም የሕግ ግድፈትና ጣልቃ ገብነት የፈጸሙበትን አካሔድ በመደገፍ “ሕመም ቢኖርብኝም የሥራ ፍላጎት አለኝ” በሚል በአዲስ አበባ ለመመደብ የጠየቁት ሊቀ ጳጳስ ክፉኛ ትዝብት ላይ ወድቀዋል
*            *            *
ጥቅምት 15 ቀን 2008 ዓ.ም.
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን
ለቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ
አዲስ አበባ
ጉዳዩ፡- በቅዱስ ሲኖዶስ በተሰጠኝ የሥራ ሓላፊነት ላይ ከሕገ ቤተ ክርስቲያኑና ከቃለ ዐዋዲው ውጭ በደል በመፈጸሙ፤ የተፈጸመውን የሥራና የሕግ ግድፈት በቅዱስ ሲኖዶሱ ለማሳረምና ትክክለኛ ፍትሕ እንዲሰጠኝ የቀረበ አቤቱታ ነው
ብፁዕ ወቅዱስ አባታችን፤ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት አባቶቼ፤ እንደሚታወቀው ኹሉ በጥቅምት 2007 ዓ.ም. በመንፈስ ቅዱስ መሪነት እና የበላይነት በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ለአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በቤተ ክርስቲያኗ ሕግ መሠረት የቅዱስ ፓትርያርኩ ረዳት ሊቀ ጳጳስ በመኾን መመደቤ ይታወቃል፡፡
እኔም በዚህ በመንፈስ ቅዱስ በሚመራው ታላቅ ጉባኤ እና በአባቶቼ የተሰጠኝን ሓላፊነትና አደራ ከተመደብኩበት ጊዜ አንሥቶ አቅሜ በፈቀደ መልኩ ያለውን ነባራዊ ኹኔታ በማገናዘብ ከቅዱስ ፓትርያርኩ ጋር በመመካከር የጠቅላይ ቤተ ክህነቱንም የሥራና የደረጃ መዋቅርን በመጠበቅ እያገለገልኩ እገኝ ነበር፤ ለዚህም እንደ ማሳያ፡-
ሀ/በሀገረ ስብከቱ የባለጉዳዮች መስተንግዶ ሥርዐት ዘመናዊና ቀልጣፋ እንዲሁም ተጠያቂነት ያለው እንዲኾን በማድረግ የተለያዩ አደረጃጀቶችን ሊጠቅም በሚችል መልኩ በማውጣት፤
ለ/የንብረትና የገንዘብ አጠባበቅ ኹኔታ በመረጃ የተደራጀ እና ዘመናዊ አሠራር እንዲኖረው በማድረግ፤
ሐ/በመንግሥት በኩል ቤተ ክርስቲያኗ ያላትን መብትና ጥቅም በመገንዘብ ከቀረጥ ነጻ በኾነ መንገድ ለቅዱስ ፓትርያርኩ እና ለሀገረ ስብከቱ የትራንስፖርት መገልገያ የሚውሉ መኪናዎች እንዲገቡ ጥረት በማድረግ፤
መ/ሀገረ ስብከቱ የሚያከናውናቸው ሥራዎች በአጠቃላይ በተጠና ዕቅድ እንዲሠራ፤ የየክፍሎቹ ሓላፊዎች በሚለካና ሊደረስበት በሚችል መልኩ ዕቅድ እንዲዘጋጅና የቀረበው ዕቅድም በአስተዳደር ጉባኤው ተገምግሞ ሥራ ላይ እንዲውል መመሪያ በመስጠት ስንሠራ ቆይተናል፡፡
ከላይ ለማሳያነት የጠቀስኋቸው ተግባራት ብዙ ጠለቅ ያለ የአፈጻጸም ሒደቶች ቢኖሯቸውም አቅም በፈቀደ መልኩ ስንቀሳቀስ ቆይቼ ነበር፡፡
ኾኖም ከቅዱስ ፓትርያርኩም ኾነ ከጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ጋር በመልካም የሥራ ግንኙነት፣ በቤተ ክርስቲያኗ ሕግና መመሪያ መሠረት አባቶቼ የሰጣችኹኝን የሥራ ሓላፊነት በመወጣት ላይ ነበርኩ፡፡
ይኹንና ዐቢይ የሕግ ግድፈት በመፈጸሙ ምክንያትና ሥልጣንን አለአግባብ በመጠቀም ጣልቃ ገብነት ሥራዬን በሓላፊነት እንዳላከናውን ተደርጌአለኹ፡፡ ከዕንቅፋቶቹና ከተፈጸሙት የሕግ ስሕተቶችም መካከል፤
1/ በጥቅምት ወር 2007 ዓ.ም. በቅዱስ ሲኖዶስ ጸድቆ በወጣው ሕገ ቤተ ክርስቲያን አንቀጽ 50፣ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ሀገረ ስብከት ነው፤ ካለ በኋላ በንኡስ ቁጥር ሦስት፣ ሀገረ ስብከቱ የሚገኘው የሀገሪቱ ርእሰ ከተማ ላይ እንደ መኾኑ መጠን ከሌሎች አህጉረ ስብከት የሚለይባቸው ልዩ ኹኔታዎች ስላሉ እኒኽን ኹኔታዎች ከግምት ያስገባ ለየት ያለ አደረጃጀት በቃለ ዐዋዲው እንዲኖረው እንደሚደረግ ይገልጻል፡፡
በዚህ መሠረት ልዩ መመሪያ ባልወጣበት ኹኔታ አንቀጹን በሌላ መንገድ በመተርጎምና ምክንያቱን በግልጽ ባላወቅሁት መንገድ ሕገ ቤተ ክርስቲያን አንቀጽ 53 ንኡስ ቁጥር 8ን በመተላለፍ፤
1.1) ሊቀ ጳጳሱ ለሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ መልምለው ለቅዱስ ፓትርያርኩ ሳያቀርቡና በሕጉም መሠረት የጋራ ስምምነት ሳይኖረን፤
1.2) በመቀጠልም በሕጉ መሠረት የረዳት ሊቀ ጳጳሱንና የቅዱስ ፓትርያርኩን ይኹንታ መሠረት አድርጎ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ማጽደቅ ሲገባው ይህ መሠረታዊ ሒደት ባልተፈጸመበት ኹኔታ፤
1.3) መልማዩና አቅራቢው በውል ማን እንደኾነ ባልታወቀበትና ሕግ በማይፈቅደው መልኩ በፓትርያርኩ ቀጥተኛ የሹመት ደብዳቤ ሥራ አስኪያጅ እና ምክትል ሥራ አስኪያጅ ለሀገረ ስብከቱ በመመደቡ ምክንያት ሀገረ ስብከቱ ከፍተኛ ቀውስ ውስጥ ገባ፡፡
2. እኒህን ዋነኛ የሕግ ግድፈቶች በመዘርዘር ጉዳዩ በቅዱስ ፓትርያርኩ እንዲታረም በመጀመሪያ በ11/07/2007 ዓ/ም በመቀጠልም በ16/07/2007 ዓ/ም በተጻፈ ደብዳቤ ጠይቄ ነበር፤ ነገር ግን ምላሽ አልተሰጠኝም፡፡ በተጨማሪም ጉዳዩ በቋሚ ሲኖዶስ ትኩረት ተሰጥቶት እንዲታረም በ17/7/2007 ዓ/ም አቅርቤ ነበር፡፡
3. ያለሊቀ ጳጳሱ አቅራቢነትና መልማይነት፣ ያለጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ጽ/ቤት ዕውቅናና አጽዳቂነት ከሕግ ውጭ በቀጥታ በቅዱስ ፓትርያርኩ ለሀገረ ስብከቱ የተሾሙት ሥራ አስኪያጅ፣ የቃለ ዐዋዲውን አንቀጽ 45 ንኡስ ቁጥር 7ን በመተላለፍ፣ አሳማኝ እና ምክንያታዊ ባልኾነ መንገድ በሀገረ ስብከቱ በክፍል ዋና ሓላፊነት ተመድበው የሚሠሩትን ሠራተኞች በ30/08/2007 ዓ/ም ያለሀገረ ስብከቱ ረዳት ሊቀ ጳጳስ ዕውቅናና ፈቃድ የተወሰኑትን ከደረጃ ዝቅ በማድረግ፣ የቀሩትንም እዚያው ባለው የሥራ ክፍል አዘዋወሩ፡፡
ከዋና ክፍል ሓላፊዎቹ በቀረበልኝ አቤቱታ፤ ሕጉን የጣሰና ምክንያቱ በትክክል ያልታወቀ ዝውውርና ከደረጃም ዝቅ ማድረግ በመኾኑ በተጨማሪም ሠራተኞች በተሰማሩበት የሥራ መስክ ላይ ተረጋግቶ የመሥራት መብትን የሚያሳጣ በመኾኑ ባለኝ ሥልጣንና ሓላፊነት መሠረት በ30/08/2007 ዓ/ም ዝውውሩንና ከደረጃ ዝቅ ማድረጉን አገድኩ፡፡ ይህም በሕጉ መሠረት ተጢኖ መታየትና መገምገም ሲኖርበት የቃለ ዐዋዲውን አንቀጽ 60 ቁጥር 2 ፊደል (ሰ)እና(ሸ) ያለአግባብ በመጥቀስና በመጠቀም በ4/9/2007 ዓ/ም በቅዱስ ፓትርያርኩ በተፈረመ ደብዳቤ እኔ ያስተላለፍኩት ሕጋዊ እግድ ያለአግባብ ተሻረ፡፡
4. ይህ በእንዲህ እንዳለ በ24/09/2007 ዓ/ም ከቅዱስ ፓትርያርኩ በተጻፈ ደብዳቤ በሥራ ገበታዬ ተገኝቼ ሥራዬን እንድቀጥል ደብዳቤ ደረሰኝ፡፡ እኔም በ25/09/2007 ዓ/ም ለደብዳቤው፣ በቅን ልቡና ሥራዬን እየሠራሁ መኾኑን፤ የሠራተኞችን ደመወዝ፣ የሚታወቁና አይቀሬ የኾኑትን የሀገረ ስብከቱን ዕለታዊ የሥራ ማስኬጃ ወጪዎችንም እየፈረምኩ ሥራዎች እየተከናወኑ እንደኾነ በመግለጽ ሥራዬን እንደምሠራ አሳወቅሁ፤ ነገር ግን ባልተለመደ አኳኋን ገንዘብን በሚመለከት ሌላ ሊቀ ጳጰስ እንደተመደበ ሰማኹ፤ ይህ አሳዛኝ ክሥተት ነው፡፡
ስለዚህም በረዳት ሊቀ ጳጳስነት መመደቤን በመወሰን ሥልጣኑንና ሓላፊነቱን የሰጠኝ ይህ ምልዓተ ጉባኤ እንደ መኾኑ፣ ለቤተ ክርስቲያናችን በሚበጅ አካሔድ መፍትሔ ይስጠኝ ዘንድ እጠይቃለኹ፡፡
እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ

2015 ኦክቶበር 29, ሐሙስ

ሰበር ዜና – አጥማቂ ነኝ ባዩ ግርማ ወንድሙ በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ዋለ



(ኤፍ ቢ ሲ፤ አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 17 ቀን 2008 ዓ.ም.)
girma wondimu
የአዲስ አበባ ፖሊስ፣ አጥማቂ ነኝ ባዩን ግርማ ወንድሙን በቁጥጥር ሥር አዋለ።
የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ምንጮች፣ አጥማቂ ነኝ ባዩን ግርማ ዛሬ በፖሊስ በቁጥጥር ሥር ውሎ ምርመራ እየተደረገበት መኾኑን ተናግረዋል።
አጥማቂ ነኝ ባዩ ግርማ፣ በማጥመቅ እፈውሳለኹ በሚል በተለያዩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አጥቢያ አብያተ ክርስቲያን ሕገ ወጥ ሀብት ሲያካብት እና በርካታ ምእመናንን ለተለያዩ ችግሮች ሲዳርግ ቆይቷል፡፡
ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ያነገጋረው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት፣ አጥማቂ ነኝ ባዩ ግርማ ዕውቅና እና ፈቃድ በይፋ የተነፈገው ሕገ ወጥ እንደኾነ አረጋግጧል።
የፋና ምንጮች፣ አጥማቂ ነኝ ባዩ ግርማ በፈውስ አገልግሎት ስም የማጭበርበር ወንጀል ሳይጠረጠር እንዳልቀረ ነው የተናገሩት።

2015 ኦክቶበር 28, ረቡዕ

ሰበር ዜና – ፈቃድ የሌላቸው የኢ.ቢ.ኤስ ፕሮግራሞች በቤተ ክርስቲያን ስም እንዳይጠቀሙ ተወሰነ፤ የ24 ሰዓት የቴሌቭዥን አገልግሎት ይጀመራል


  • የጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ፈቃድ እና ዕውቅና የሌላቸው የፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ አቀንቃኞቹ፣ ታዖሎጎስ እናቃለ ዐዋዲ  በምልአተ ጉባኤው ውሳኔ በስም ተለይተው ተጠቅሰዋል
  • በምልአተ ጉባኤው ውሳኔ መሠረት፣ በቋሚ ሲኖዶስ የተቋቋመው የብዙኃን መገናኛ ቦርድ ሥራውን ለመጀመር እየተንቀሳቀሰ ነው
  • በፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ ኑፋቄ ላይ የቀረቡ ማስረጃዎች የበለጠ ተጠናክረው አጀንዳው በልዩ የምልአተ ጉባኤ ስብሰባ እንዲታይ ተወስኗል
synod tik2008 Edited
የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ፣ ከማእከል የተሰጠ ሕጋዊ ፈቃድ ሳይኖራቸው በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስም፣ በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ሰርቪስ(EBS) የቴሌቭዥን ጣቢያ“ሃይማኖታዊ ትምህርት” የሚያስተላልፉ ፕሮግራሞች፣ የቤተ ክርስቲያንን ስም እንዳይጠቀሙ ወሰነ፡፡
ምልአተ ጉባኤው በዛሬ፣ ጥቅምት 17 ቀን 2008 ዓ.ም. ስድስተኛ ቀን የቀትር በፊት ውሎው ያሳለፈው ውሳኔ ተፈጻሚ እንዲኾን፤ የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር እና የኢ.ቢ.ኤስ ቴሌቭዥን በደብዳቤ እንዲያውቁት ይደረግ ዘንድ ትእዛዝ ሰጥቷል፡፡
በውሳኔው÷ የፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ አቀንቃኞቹ፣ “ታዖሎጎስ” እና ቃለ ዐዋዲ”  በስም የተጠቀሱ ሲኾን በፕሮግራሞቹ አዘጋጅነት የሚታወቁት በተለይ የ“ታዖሎጎስ” ግንባር ቀደም ምንደኞች፣ ፕሮግራማቸው “ራሱን የቻለ የሚዲያ ተቋም” እንጂ  ከቅዱስ ሲኖዶሱ ይኹን ከጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ጋር ተቋማዊ ግንኙነት እንደሌላቸው በይፋ በሰጡት መግለጫ ማረጋገጣቸው ይታወሳል፡፡
ምልአተ ጉባኤው ከዚሁ ጋር በማያያዝ፤ በሊቃውንት ጉባኤ ሳይመረመሩ እና በማእከል ሳይፈቀዱ በግለሰቦች እየተዘጋጁ የቤተ ክርስቲያንን ስም ይዘው ስለሚወጡ የስብከት፣ የመዝሙር እና የመጻሕፍት ኅትመቶች እንዲኹም የአዳራሽ ጉባኤያት እና ስብሰባዎች ከተወያየ በኋላ ቀደም ሲል ያሳለፋቸውን ውሳኔዎች በማጽናት ተመሳሳይ ትእዛዝ መስጠቱ ታውቋል፡፡
ቅዱስ ሲኖዶሱ፣ “ስብከተ ወንጌል እና ሚዲያን በተመለከተ” በተራ ቁጥር ሦስት በያዘው አጀንዳ፤ ቤተ ክርስቲያን ማእከላዊነቱን ጠብቆ የራስዋን ድምፅ ለዓለም የምታሰማበት እና ስብከተ ወንጌልን የምታስፋፋበት የ24 ሰዓት የቴሌቭዥን አገልግሎት እንዲጀመርም ወስኗል፡፡
ለቤተ ክርስቲያን የብዙኃን መገናኛ ስርጭት የሚያስፈልገውና በስብከተ ወንጌል እና ሐዋርያዊ ተልእኮ መምሪያ አስተባባሪነት ተጠንቶ የቀረበው በጀት ባለፈው ዓመት ግንቦት በምልአተ ጉባኤው የጸደቀ ሲኾን በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ የመክፈቻ ንግግር እንደተመለከተው፤ በዚኽ ዓመት በጀቱ በአፋጣኝ ሥራ ላይ እንዲውል የቀረበውን ጥያቄ በመቀበል የፋይናንስ ምንጮቹን ወስኖ ለነገ የሚያቀርብ ሦስት አባላት ያሉት የብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት(ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ፣ ብፁዕ አቡነ ሳሙኤል እና ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ) ኮሚቴ በምልአተ ጉባኤ ተሠይሟል፡፡
ምልአተ ጉባኤው ባለፈው ዓመት ግንቦት ባጸደቀው የሚዲያዎች (የሬዲዮ እና የቴሌቭዥን አገልግሎት) ሥርጭት ደንብ መሠረት፤ በስብከተ ወንጌል እና ሐዋርያዊ ተልእኮ የበላይ ሓላፊ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ማርቆስ የሚመራ የብዙኃን መገናኛ የሥራ አመራር ቦርድ የተቋቋመ ሲኾን ተግባሩን ለመጀመር እየተንቀሳቀሰ እንዳለ ለ34ኛው የመንበረ ፓትርያርክ የሰበካ አስተዳደር አጠቃላይ ጉባኤ የቀረበው ሪፖርት ያስረዳል፡፡
በሪፖርቱ እንደተጠቀሰው፤ ቤተ ክርስቲያኒቱ ስብከተ ወንጌልን ከዐውደ ምሕረት ባሻገር በአጽናፈ ዓለም ለማስፋፋት እና ለማጠናከር ስለሚያስፈልጓት ሚዲያዎች፣ በመምሪያው አስተባባሪነት በብዙኃን መገናኛ ባለሞያዎች የተካሔደውን ጥናት መሠረት አድርጎ መተዳደርያ ደንብ፣ ኤዲቶሪያል ፖሊሲ እና የቴሌቪዥን ሥርጭት መመሪያ/ማኑዋል ተዘጋጅቷል፡፡
በተያያዘ ዜና፣ “የቤተ ክርስቲያኗን ወቅታዊ ኹኔታ በጥልቀት ማየት” በሚል ዐቢይ አጀንዳ ሥር በፊደል ተራ ቁጥር 4/መ፣ “የተሐድሶ እንቅስቃሴን በተመለከተ”፤ የተዘጋጀው ሰነድ በተጨማሪ ማስረጃዎች ተስፋፍቶ እና ተጠናክሮ ራሱን በቻለ ልዩ የምልአተ ጉባኤ ስብሰባ እንዲታይ ቅዱስ ሲኖዶሱ ወስኗል፡፡
የስብሰባው ምንጮች እንደተናገሩት፤ ከፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ ግንባር ቀደም መሪዎች በሚሰጣቸው ተልእኮ እና ድጋፍ በቤተ ክርስቲያናችን የአስተዳደር እና የአገልግሎት መዋቅር ውስጥ በመስረግ የኑፋቄውን አስተሳሰብ እና ድርጊት የሚያራምዱ የ66 አካላት እና ግለሰቦች የሰነድ፣ የምስል እና የድምፅ ማስረጃዎች ከኃምሳ ገጾች ማብራሪያ ጋር ተደግፎ ተዘጋጅቷል፡፡
ከቤተ ክርስቲያናችን ዐውደ ምሕረት እና የአስተዳደር መዋቅር ባሻገር፣ የኑፋቄው ግንባር ቀደም መሪዎች እና ምንደኞቻቸው በከፍተኛ ትምህርት ተቋሞቻችን(መንፈሳዊ ኮሌጆች እና የካህናት ማሠልጠኛዎች) ውስጥ በተለያየ ሽፋን የሚያደርጉት እንቅስቃሴ ትኩረት እንዲደረግበት ምልአተ ጉባኤው ኮሚቴውን አሳስቧል፡፡
Beriyaበመካከለኛው ምሥራቅ አህጉረ ስብከት፣ ብፁዕ ሊቀ ጳጳሱ ሳያውቁት ከሥርዐተ ቤተ ክርስቲያን ውጭ በተቋቋመው የኑፋቄው መናኸርያ “ዱባይ ሚካኤል” እና “ቤርያ ቲኦሎጂካል ኢንስቲትዩት” በሚል መሪዎቹ የመሠረቱት ሕገ ወጥ ተቋም በከፍተኛ ደረጃ ያነጋገረ ሲኾን በምልአተ ጉባኤው ጥናት ተካቶ እንዲቀርብ መወሰኑ ተጠቁሟል፡፡
በተመሳሳይ ኹኔታ ጉባኤውን ያነጋገረው፣ በመንበረ ፓትርያርኩ የውጭ ጉዳይ መምሪያ በሓላፊነት የተቀመጡት መልአከ ሰላም አባ ቃለ ጽድቅ የተባሉ ግለሰብ፣ ከፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ ኑፋቁ አንጻር ያላቸው ሃይማኖታዊ አቋም እና ሥነ ምግባራዊ ኹኔታ ነበር፡፡ የግለሰቡ አመጣጥ እና አመዳደብም ከፓትርያርኩ ልዩ ጸሐፊ ንቡረ እድ ኤልያስ ኣብርሃ ጋር ባላቸው የጥቅም ግንኙነት እንደኾነ መጠቆሙ ደግሞ ችግሩ ከግለሰቡም በላይ ልዩ ጽ/ቤቱ እንደ መዋቅር ያለበትን አስከፊ ደረጃና አሳሳቢነቱን ለምልአተ ጉባኤው አለብቧል፡፡ 
ከዚኽ ውስብስብነቱና ከሚያስፈልገው ጠንካራ ቅንጅት አኳያ፤ አጀንዳው ራሱን በቻለ አስቸኳይ እና ልዩ የምልአተ ጉባኤ ስብሰባ እንዲታይ ቅዱስ ሲኖዶሱ ሲወስን ጊዜው በመጪው ወርኃ ጥር ላይ ሊኾን እንደሚችል ከወዲኹ የተጠቆመ ቢኾንም በኮሚቴው ውጤታማ እንቅስቃሴ ላይ እንደሚመሠረት ነው፣ በብዙኃን የምልአተ ጉባኤው ዘንድ መግባባት የተደረሰበት፡፡
በሕገ ቤተ ክርስቲያን የቅዱስ ሲኖዶስ የስብሰባ ሥነ ሥርዐት መሠረት፤ አስቸኳይ እና ድንገተኛ ጉዳይ ሲያጋጥም ቅዱስ ፓትርያርኩ ወይም ቋሚ ሲኖዶሱ ወይም የቅዱስ ሲኖዶሱ ዋና ጸሐፊ በሚያደርጉት ጥሪ የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ ሊካሔድ ይችላል፡፡ ቅዱስ ሲኖዶስም በማናቸውም ስብሰባ ላይ ውሳኔዎችን ሲያሳልፍ፤ ሃይማኖትንና ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን የሚመለከት ከኾነ በሙሉ ድምፅ ያልፋል፤ በሃይማኖት እና በቀኖና ጉዳይም ድምፀ ተዓቅቦ ማድረግም አይቻልም፡፡

 

  •  

                   by ሐራ ዘተዋሕዶ

2015 ኦክቶበር 22, ሐሙስ

የ34ኛው አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ የአቋም መግለጫ

አትም ኢሜይል
ጥቅምት 11 ቀን 2008 ዓ.ም
01 sebeka11በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመንበረ ፓትርያርክ 34ኛው አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ከጥቅምት 8-10 ቀን 2008 ዓ.ም ሲካሄድ ቆይቶ ባለ 23 ነጥብ የጋራ የአቋም መግለጫ አውጥቷል፡፡

በቅዱስ ፓትርያርኩ ቃለ በረከት ጥቅምት 8 ቀን 2008 ዓ.ም የተጀመረው ጉባኤ ለሦስት ተከታታይ ቀናት የብፁዕ አቡነ ማቴዎስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የወላይታ ኮንታና ዳውሮ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የ2007 ዓ.ም አጠቃላይ ሪፖርት እና የየአህጉረ ስብከት ሪፖርቶች በቅደም ተከተል ቀርበዋል፡፡ በቀረቡት ሪፖርቶች መሠረትም ቃለ ጉባኤ ተነቦ በማጽደቅ ባለ 23 ነጥቦች የጋራ የአቋም መግለጫ አውጥቷል፡፡

የአቋም መግለጫውን እንደሚከተለው እናቀርባለን፡-
1.ቅዱስ ፓትርያርኩ ለ34ኛው አጠቃላይ ሰበካ ጉባኤ ያስተላለፉትን ቃለ ቡራኬና አባታዊ የሥራ መመሪያ ሙሉ ለሙሉ ተቀብለን ተግባራዊ ለማድረግና የሚጠበቅብንን ለመወጣት ዝግጁ መሆናችንን ቃል እንገባለን፡፡

2.በቅዱስነታቸው ቃለ ቡራኬ ከተላለፉት መሠረታዊ መልእክቶች ውስጥ ቅዱስነታቸው ዐቢይ ጉባኤው ትኩረት ሰጥቶ እንዲወያይባቸው ያሳሰቧቸው፡-
አንደኛ፡-ምእመናንን የመጠበቅ ተልእኮ በሚገባ እየተወጣን አይደለምና ባዶ እጃችንን ከመቅረታችን በፊት ለተደራጀና ለድንበር የለሽ ስብከተ ወንጌል ብንነሣ፡፡

ሁለተኛ፡-የአስተዳደር ሥራችን ለምእመናን ሕሊና እንቅፋት እየሆነ ነውና የሃይማኖቱን መርህ አስጠብቀን አስተዳደራችን የሕግ የበላይነትን ያረጋገጠ፣ ግልጽ፤ ተአማኒና ተጠያቂነትን ያሰፈነ የምእመናንን ልብ የሚያረካ፣ ምእመናን በቤተ ክርስቲያናቸው ኩራት እንዲሰማቸው የሚያስችል አሠራር ብናረጋግጥ ተጨባጭ ለውጥ ማስመዝገብ እንችላለን በማለት የሰጡትን መመሪያ በተግባር ለመለወጥ ቃል እንገባለን፡፡

3. የቅዱስ ሲኖዶስን ሉዓላዊነት የሚጋፉ፣ ለቤተ ክርስቲያን ማእከላዊ አመራር አንታዘዝም የሚሉ፣ ቤተ ክህነት ምን አገባው፣ ሀገረ ስብከት ምን አገባው፣ ቅዱስ ሲኖዶስ ምን አገባው፣ የጠቅላይ ቤተ ክህነት አስተዳደራዊ መዋቅራዊ ምን አድርጎልናል በሚል የማደናገሪያ ስልት መዋቅርን የሚንዱ ችግሮች በከፍተኛ ፍጥነትና ብዛት በተደራጀና በተጠና ስልት በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር በከፍተኛ ፍጥነት እያደጉ ስለሆነ ቅዱስ ሲኖዶስ ለጉዳዩ ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት እንዲወያበትና መፍትሔ እንዲሰጠው ለዘመናት ጸንቶ የቆየውን የቤተ ክርስቲያንን መዋቅር እንዲያስጠብቅ በከፍተኛ ስሜት እንጠይቃለን፡፡

4. በሁሉም አህጉረ ስብከት የታየው የብፁዓን አባቶች ሐዋርያዊ ጉዞ እጅግ ውጤታማ፣ ለምእመናን ጥንካሬ፣ ለቤተ ክርስቲያን ከፍተኛ እድገት አስተዋጽኦ ያለው ስለሆነ ተጠናክሮ እንዲቀጥል እንጠይቃለን፣ በእኛም በኩል የሚገባንን ለማድረግ ቃል እንገባለን፡፡

5. በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁና በማደራጃ መምሪያው የተገለጹት የሁለትዮሽ የሒሳብ አያያዝ /Double Entry/ ሥርዓት የፋይናንስ ማእከላዊነትን በማረጋገጥ፣ የአገልጋዮችን የሥራ አቅም ብልጽግና በማሳደግ ብክነትነትን በማስወገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያለው ስለሆነ ከብዙ ጊዜ ማሳሰቢያ በኋላ ተግባራዊ መሆኑ ጉባኤውን አስደስቷል፡፡ ይህ አሠራር በቀጣይነት በየደረጃው እስከ ታች የቤተ ክርስቲያን መዋቅር ድረስ ተግባራዊ እንዲሆን ይልቁንም አሠራሩ ዘመኑ አሁን የደረሰበት የሥልጣኔ ደረጃ መሠረት በማድረግ በኔትዎርክ ተሳስሮ፣ በሥልጠና ተደግፎ፣ ግልጽና ተጠያቂ በሆነ መንገድ ተግባራዊ እንዲሆን ወጥና ቀጥ ያለ አመራር እንዲሰጥ እየጠየቅን እኛም ለተግባራዊነቱ የድርሻችንን ለመወጣት ቃል እንገባለን፡፡

6. ተቋርጦ የነበረው የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ስምሪት መጀመሩ ጉባኤውን እጅግ ያስደሰተ ሲሆን ስምሪቱ በተጠናከረ መንገድ አስተማማኝ የሆነ የራሱ በጀት ተመድቦለት በሥልጠናና በተደራጀ ውጤት ተኮር በሆነ መንገድ እንዲቀጥል የበኩላችንን ሁሉ ለማድረግ ቃል እንገባለን፡፡

7. የታየው የገቢ እድገት ጉባኤውን እጅግ ያስደሰተ ሲሆን ከበጀት እድገቱ ጎን ለጎን በልማት ሥራዎች ለቤተ ክርስቲያን ቋሚ ንብረት ለማፍራት የቀደሙት አባቶች ሠርተው እንዳወረሱን ሁሉ ቋሚና ዘላቂ ንብረት ለቤተ ክርስቲያን ለማፍራት በልማት ለመትጋት ቃል እንገባለን፡፡

8. ብፁዓን አባቶች ባደረጉት ጥረት ምእመናንና ካህናትን በማስተባበር የሚካሔደው የልማትና ለቤተ ክርስቲያን ንብረት የማፍራት ዘላቂ ገቢ የማስገኘት ሥራ ለሚመራው አህጉረ ስብከትም ሆነ ተቋማት ሕልውና ዋስትና ለብፁዓን አባቶች አብረዋቸው ለደከሙት የሥራ ሓላፊዎች የድካማቸው መዘክሮች ስለሆኑ ንብረቶቹ በየአህጉረ ስብከቱና በዋናው መሥሪያ ቤት ባሕር መዝገብ በአግባቡ ተቆጥረውና ተመዝግበው እንዲያዙ እንጠይቃለን ለአፈጻጸሙም የበኩላችንን ለማድረግ ቃል እንገባለን፡፡

9. ስብከት ወንጌልን ለማስፋፋት፣ የቤተ ክርስቲያንን ተልእኮ በተፈለገው መጠን ለማዳረስ ብቃትና ታዛዥነት ያላቸው አገልጋዮች እጥረት ትልቅ እንቅፋት ስለሆነ የአገልጋዮችን እጥረት በተለይም በልዩ ልዩ ብሔሮችና ብሔረሰቦች ቋንቋዎች የሚያስተምሩ መምህራነ ወንጌል በጥራትና በቁጥር ለማሳደግ የበኩላችንን ለማድረግ ቃል እንገባለን፡፡

10. ስብከተ ወንጌል አገልግሎት ከዐውደ ምሕረት ባሻገር በማረሚያ ቤቶች፣ በጤና ማእከላትና በመሳሰሉት ለማዳረስ በተለይም ዘመኑ በሚፈቅደው በብዙኀን መገናኛ ወይም ሚዲያ በመታገዝ በመላው ዓለም ቤተ ክርስቲያን ድምጿን በራሷ በኩል ማእከላዊነቷን ጠብቆ ለማሰማት የሚደረገውን ጥረት ከልብ በመደገፍ ለተግባራዊነቱ የበኩላችንን ለመወጣት ቃል እንገባለን፡፡

11. ለስበከተ ወንጌል እንቅፋት የሆኑ ሕገወጥ ሰባኪያን፣ ሕገወጥ አጥማቂዎች ነን ባዮችና መዋቅር ያልጠበቁ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ክብር የሚያስነቅፉ እንቅስቃሴዎች ለመግታት እስካሁን ከተሠራው በይበልጥ ለመሥራት ቃል እንገባለን፡፡

12. በየጊዜውና በየዘመኑ ወቅቱ በሚፈቅደው መጠን መስመሩን ሳይለቅ ሲሻሻልና ሲዳብር የኖረው ቃለ ዓዋዲ አሁንም በይበልጥና በጥራት የሕግ ጸባይ በመያዝ ለሀገር ውስጥም ሆነ ለውጭ ሀገረ መንግሥታት ተቀባነት በሚያገኝ መልኩ መሻሻሉ ሁሉም የሚጠብቀው ስለሆነ ቅዱስ ሲኖዶስ ለጉዳዩ ልዩ ትኩረት በመስጠት በተለይ እስካሁን ያልተደረገው በውጭ አህጉረ ስብከት ያሉ አብያተ ክርስቲያናት ማእከል ባደረገ መልኩ ጊዜ ሳይሰጠው ተዘጋጅቶ እንዲሻሻል በአጽንኦት እየጠየቅን ለሚደረገው ሁሉ የበኩላችንን ለመወጣት ቃል እንገባለን፡፡

13. ለማሰልጠኛዎችና ለአብነት ትምህርት ቤቶች እየተሰጠ ያለው ትኩረት ከምን ጊዜውም የተሻለ ቢሆንም በተቀናጀና ማእከላዊነቱን በጠበቀ መልኩ እንዲደራጅ፣ በጀት ያልተመደበላቸው በጀት እንዲያገኙ፣ በበጎ አድራጊ ምእመናን የተሠሩ ሁሉ በማእከል እውቅና እየተሰጣቸው የቤተ ክርስቲያን ባለቤትነት እንዲያገኙ እየጠየቅን ቅዱስ ሲኖዶስ በተለይ ለአብነት ትምህርት ቤቶችና ቀመዛሙርቶቻቸው ልዩ ትኩረት እንዲሰጥ በታላቅ አክብሮት እንጠይቃለን፡፡

14. ለሰንበት ትምህርት ቤቶች አደረጃጀት የተሰጠው ትኩረት ልዩ ልዩ ሥልጠናና የሥርዓተ ትምህርት ከመዝሙር መጽሐፍ ጋር ተዘጋጅቶ መሰራጨቱ ወጣቶችን በወጥነት ለማስተማር በሃይማኖትና ሥነ ምግባር ለማሳደግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያለው መሆኑን ጉባኤው ያመነበት ሲሆን ሂደቱ ተጠናክሮ እንዲቀጥል በመምሪያው በኩል የቀረቡ ችግሮች በተለይም ከልዩ ልዩ የወጣቶችና የጎልማሶች ማኅበራት ያለው ተጽእኖ እንዲቆም፤ የወጣቶች የሰንበት ትምህርት ቤቶች ቆይታ የእድሜ ገደብ እንዲከበር በቅዱስ ሲኖዶስ መመሪያ እንዲሰጥ እንጠይቃለን፡፡

15. በቅርስ ጥበቃና ምዝገባ በተመለከተ በአንዳንድ አህጉረ ስብከት የታየው ከመንግሥት ጋር የተቀናጀ የቅርሶች ምዝገባ፣ የቅርሶች ማስመለስ፣ የሙዚየሞች ማደራጀት፣ለቅርሶች ዋስትና ቢሆንም ሁሉንም ጥረቶች ለቤተ ክርስቲያኒቱ የቅርሶቿና የታሪክ ባለቤትነት በሚያረጋግጥ መልኩ እንዲፈጸሙ ቅዱስ ሲኖዶስ አስቸኳይና ወቅታዊ መመሪያ እንዲሰጥ በታላቅ አጽንኦት እንጠይቃለን፡፡

16. ወደ መናፍቃንና ወደ ኢአማኒነት ከሚፈልሰው ምእመን ቁጥር ባልተናነሰ አስተዋጽኦ የሚያደርገው ለአገልጋዮች ዋስትናና ከለላ ማጣት ለቤተ ክርስቲያን የወደፊት ሕልውና ከፍተኛ ስጋት የሆነው የመልካም አስተዳደር እጦትና ሙስና ለመቅረፍ በሥልጠና የታገዘ ሥራ፣ ሥራና ሠራተኛን በማገናኘት ላይ ያተኮረ አስተዳደርን፣ ችግሮችን በመፍታት ብቁ አገልጋዮችን ለማፍራት ያለመ መልካም አስተዳደርን ለማስፈን ቅዱስ ሲኖዶስ ልዩ ትኩረት እንዲሰጠው እየጠየቅን እኛም ለተግባራዊነቱ የበኩላችንን ለመወጣት ቃል እንገባለን፡፡

17.በተፈጠረው የአየር ለውጥ ምክንያት በወቅቱ ለተከሰተው ድርቅ በተጎዱ አህጉረ ስብከት ለሚገኙ አድባራት፣ ገዳማትና አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ምእመናን በርካታ በመሆናቸው ቅዱስ ሲኖዶስ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመነጋገር አስቸኳይ መፍትሔ እንዲሰጠው እንጠይቃለን፡፡

18. በልማት፣ በአረጋውያን እንክብካቤ፣ ወላጆቻቸውን ያጡ ሕፃናትን በማሳደግ፣ በአካባቢ ጥበቃ፣ በማኅበራዊ አገልግሎትና ለወገን ደራሽነት አብያተ ክርስቲያናት በማሳነጽ ቋሚና ዘላቂ ልማት በማስፋፋት የሚደረገውን ጥረት ለመደገፍ ቃል እንገባለን፡፡

19. የቤተ ክርስቲያን አስተዳደር ሲኖዶሳዊ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ይሁን እንጂ በአንዳንድ አካባቢዎች እንደ ፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ አብያተ ክርስቲያናት ከሲኖዶሳዊ መዋቅር የወጣ ቀኖናዊ ትውፊትን ያልጠበቀና ኢክርስቲያናዊ ኢኦርቶዶክሰዊ የሆነ ገለልተኛ ቅንጅት በመፍጠር ምእመናንን በሚያደናግሩ አካለት ዙሪያ ቅዱስ ሲኖዶስ አስቸኳይ መፍትሔ እንዲያስቀምጥለት ለተግባራዊነቱም የበኩላችንን ለማድረግ ቃል እንገባለን፡፡

20. የቅዱስነታቸው ሐዋርያዊ ጉዞ የቤተ ክርስቲያን ዓለም አቀፋዊነት የሚያረጋግጥ በመሆኑ በውጭ ያሉትን አህጉረ ስብከት የሚያጠናክር በመሆኑ ቀጣይነት እንዲኖረው እየጠየቅን በዚህ ረገድ ከኦርየንታል አብያተ ክርስቲያናት በተለይም ከግብፅ ኮፕት ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ጋር ያለውን ግንኙነት በሚገባ እንዲተኮርበት በታለቅ አጽንኦት እንጠይቃለን፡፡

21. በአሁኑ ጊዜ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በመላው ዓለም እየሰፋችና ከራሷ ምእመናን አልፎ የውጭ ሀገር ተወላጅ የሆኑ ምእመናንን ያፈራች በመሆኑ የውጭ ግንኙነት ሥራዋ ዓለማቀፋዊ ይዘቱን እንደጠበቀ እንዲስፋፋ ቅዱስ ሲኖዶስ ልዩ ትኩረት እንዲሰጠው እንጠይቃለን፡፡

22. በሊቢያ በረሃ ስለ ክርስትና ሃይማኖታቸው ሰማዕትነትን የተቀበሉ ወጣቶችን አስመልክቶ የተደረገው ሲኖዶሳዊና ቀኖናዊ ውሳኔ የተቀበልን ሲሆን በፍትሕ መንፈሳዊ ሰማዕታትን የሚያስቡ፣ ከሰማዕታት ዋጋ ያገኛሉ የሚለውን በመከተል የቅዱስ ሲኖዶስን ውሳኔ ተግባራዊ ለማድረግ ቃል እንገባለን፡፡

23. የእግዚአብሔርን ሕግና ትእዛዝ የተፈጥሮ ሕግን ወሰን በማለፍ በታላላቅ ሀገሮች ተጽእኖና ድጋፍ እየተስፋፋ ያለውን የግብረ ሰዶምን እንቅስቃሴ በመቃወም ቤተ ክርስቲያን ድምጿን ለዓለም ማሰማት እንዳለባት እየጠየቅን ጥያቄውን ከዚህ በፊት ላስተጋቡ ብፁዓን አባቶች ላደረጉት ጥረት ልባዊ ድጋፋችንና አጋርነታችን በመስጠት ሃይማኖታዊና ቀኖናዊ ግዴታችን ስለሆነ ምእመናንን በትምህርት ወንጌል ለማነጽ ቃል እንገባለን፡፡

                                   በአውሮጳ   የካህናት አንድነት ማኅበር ሊቋቋም መሆኑ ታወቀ በ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከመላዋ አውሮጳ   የተውጣጡ ካህናት፡” የ...