2013 ኦክቶበር 15, ማክሰኞ









 ሰበረ‹ዜና  ረጅም ዕድሜ ያስቆጠሩ ተላላቅ አሥር አቢያተ ክርስቲያናት ተቃጠሉ
32ኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አጠቃላይ ዓለማቀፍ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባዔ ከተጀመረ ዛሬ ሁለተኛ ቀን ሆኖታል ፡፡ በዚህ ተላቅ ጉባዔ ላይ እጅግ አሳዛኝ ሪፖርቶች ተሰምተዋል ጥቂቶቹ
1.     የደቡብ ጎንደር ሀገረ ስብከት ሪፖርት በጉባዔው ላይ እንዳስደመጠው  አምስት ታላላቅ አድባራት  ማንነታቸው ባልታወቀ አጽራረ ቤተክርስቲያን  መቃጠላቸውን  በሪፖርቱ አስደምጦአል አድባራቱ  ታሪካዊና ውድ የሆኑ ቅርሶች የሚገኙበት በመሆናቸው ቤተከርስቲያኒቱን አሳዝኖአል በተያያዘ የኮነኔል ማእረግ የተለጠፈላቸው ሁለት ግለሰቦች ቅርሶችን የመዝረፍ ሙከራ እያደረጉ እያሉ በሀገረ ስበከቱና በህዝበ ክርስቲያኑ ርብርብ የዳነ መሆኑንም ጨምሮ የገለጸው ሪፖርቱ ሀገረ ስብከቱ ረጅም ዕድሜ ያስቆጠሩ ቅርሶች ሚገኙበት በመሆኑ የቅረስ ዘረፋም ከመጠን በላይ መሆኑንም ቸምሮ ገልጦአል እንዲሁም የ15 አቢያተ ክርስቲናት ይዞታ ጉዳይም ከብዙ ክረክር በኋላ መፍትሔ እንዳገኙ ተገልጦአል ፡፡
2.    ምሥራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት  በዚህም ሀገረ ስብከትም አሥር አቢያተ ክርስቲያናት መቃጠላቸውን የሀገረ ስብከቱ ሪፖርት ገለጸ  በሪፖርቱ እንደተገለጸው አቢያተ ክርስቲያናቱ ታሪካዊና የብዙ ቅርስ ባለቤት ሆኑት ተመርጠው መቃጠላቸው ህዝበ ክርስቲያኑን አሳዝኖአል እነዚህ የሀገር ሀብት ቅርሶች ሲወድሙ ዝም ማለትና ወንጀለኞችን ለህግ አለማቅረብ  ጉባዔውን በጣም ያሳዘነ መሆኑን ሪፖርቱ ጨምሮ ገልጦአል የዞኑም አስተዳደር ጉዳዩን በአጽንኦት ተመልክቶ መፍትሔ ሊወስድ ይገባል ሲሉ የጉባኤው ታዳሚዎች አስተያየታቸውን ገልጠዋል ፡፡
3.    ምዕራብ ወለጋ ሀገረ ስብከት  ሕዝቡን በሚገባ ያስተዳድራሉ ይመራሉ ተብለው ሓላፊነት የተሰጣቸው  የዞኑ እና የወረዳው ባለሥልጣናት  የአቢያተ ክርስቲያናቱን ቦታ  በመቀማት፤ ካህናቱን በመደብደብ፤ በቅዳሴ ሰዓት ሕዝቡን ከቅዳሴ ላይ ሂዱ ወደ ስብሰባ በማለት በመረበሽ ፤ በዚሁ ምክንያት አንድ ሴትና አንድ ወንድ  በድብደባ ለሞት መዳረጋቸውን የሀገረ  ስብከቱ ሪፖርት ገልጦአል  ባለሥልጣናቱ በሣሪያ አፈሙዝ በማስፈራራት በይፋ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮችን  መደብደብና ማንገላታት የዘወትር ስራቸው በመሆኑ በዞኑ ለመኖር አለመቻላቸውን ሪፖርቱ ጨምሮ ገልጦአል  የጉባዔው ተሳታፊዎችም መንግስት እንዲህ ያሉትን የግል አጀንዳ ያላቸውን ባለሥልጣናት በመከታተል እርምጃ ሊወስድ ይገባል ብለዋል ይህ ካልሆነ በሕዝቡ መካከል ተከባብሮ የኖረውን ሕዝብ ለማጨት መሆኑ የአደባባ ምሥጢር ነው ብለዋል ተሳታፊዎቸሁ ፡፡ በየሀገረ ስብከቶቹ ሁሉ ተመሳሳይ ችግሮች እንዳሉ  ሀገረስብከቶቹ  በየሪፖርታቸው ገለጠዋል ፡፡
ይሁን እንጂ የደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀገረስብከት በሀገረ ስበከቱ በየደብሩ ላይ   የተፈጸመውን   ፍንዳታ፤ የአቢያተ ክርስቲያናት መዘጋትና ሌሎች ችግሮችን ጨርሶ አለማንሳቱ ከፍተኛ ጥርጣሬ አሳድሮአል ችግሮቹ በሕዝቡ ዘንድ የሚታወቅ ቢሆንም የሀገረ ስብከቱ ሪፖርት ችግሩን ለጉባዔው አለማቅረቡ የችግሩ ተበባሪ አስመስሎታል   የሀገረ ስብከቱ ሥራስኪያጁ  እንደሚያሳየው ከሆነ ከላይ የተጠቀሱት ችግሮች እተባባሱ መሄዳቸው የሚታወቅ ቢሆንም  የአድባራቱን በመናፍቃን መወረርና መቃጠል ችግሮቻውን ከመቅረፍ ይልቅ ማባበሱ ላይ ያቶከሩ ናቸው በማለት ተሳታፊዎች ገልጠዋል፡፡ አንባቢዎች የሀገረስብከቱ አጠቃላይ ችግሮች ስላልተነሱ በዝርዝር የምናቀርብ ይሆናል፡፡


  • Participants of the 32nd SGGA03


   
 
ሰበር ዜና ጅም ዕድሜ ያስቆጠሩ ተላላቅ አሥር አቢያተ ክርስቲያናት ተቃጠሉ

32ኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አጠቃላይ ዓለማቀፍ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባዔ ከተጀመረ ዛሬ ሁለተኛ ቀን ሆኖታል ፡፡ በዚህ ተላቅ ጉባዔ ላይ እጅግ አሳዛኝ ሪፖርቶች ተሰምተዋል ጥቂቶቹ እነሆ!
1.     የደቡብ ጎንደር ሀገረ ስብከት ሪፖርት በጉባዔው ላይ እንዳስደመጠው  አምስት ታላላቅ አድባራት  ማንነታቸው ባልታወቀ አጽራረ ቤተክርስቲያን  መቃጠላቸውን  በሪፖርቱ አስደምጦአል አድባራቱ  ታሪካዊና ውድ የሆኑ ቅርሶች የሚገኙበት በመሆናቸው ቤተከርስቲያኒቱን አሳዝኖአል በተያያዘ የኮነኔል ማእረግ የተለተፈላቸው ሁለት ግለሰቦች ቅርሶችን የመዝረፍ ሙከራ እያደረጉ እያሉ በሀገረ ስበከቱና በህዝበ ክርስቲያኑ ርብርብ የዳነ መሆኑንም ጨምሮ የገለጸው ሪፖርቱ ሀገረ ስብከቱ ረጅም ዕድሜ ያስቆርጠሩ ቅርሶች ሚገኙበት በመሆኑ የቅረስ ዘረፋም ከመጠን በላይ መሆኑንም ቸምሮ ገልጦአል እንዲሁም የ15 አቢያተ ክርስቲናት ይዞታ ጉዳይም ከብዙ ክረክር በኋላ መፍትሔ እንዳገኙ ተገልጦአል ፡፡
2.    ምሥራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት  በዚህም ሀገረ ስብከትም አሥር አቢያተ ክርስቲያናት መቃጠላቸውን የሀገረ ስብከቱ ሪፖርት ገለጸ  በሪፖርቱ እንደተገለጸው አቢያተ ክርስቲያናቱ ታሪካዊና የብዙ ቅርስ ባለቤት ሆኑት ተመርጠው መቃጠላቸው ህዝበ ክርስቲያኑን አሳዝኖአል እነዚህ የሀገር ሀብት ቅርሶች ሲወድሙ ዝም ማለትና ወንጀለኞችን ለህግ አለማቅረብ  ጉባዔውን በጣም ያሳዘነ መሆኑን ሪፖርቱ ጨምሮ ገልጦአል የዞኑም አስተዳደር ጉዳዩን በአጽንኦት ተመልክቶ መፍትሔ ሊወስድ ይገባል ሲሉ የጉባኤው ታዳሚዎች አስተያየታቸውን ገልጠዋል ፡፡
3.    ምዕራብ ወለጋ ሀገረ ስብከት  ሕዝቡን በሚገባ ያስተዳድራሉ ይመራሉ ተብለው ሓላፊነት የተሰጣቸው  የዞኑ እነ የወረዳው ባለሥልጣናት  አቢያተ ክርስቲያናቱን ቦታ  በመቀማት፤ ካህናቱን በመደብደብ፤ በቅዳሴ ሰዓት ሕዝቡን ከቅዳሴ ላይ ሂዱ ወደ ስብሰባ በማለት በመረበሽ ፤ በዚሁ ምክንያት አንድ ሴትና አንድ ወንድ  በድብደባ ለሞት መዳረጋቸውን የሀገረ  ስብከቱ ሪፖርት ገልጦአል  ባለሥልጣናቱ በሣሪያ አፈሙዝ በማስፈራራት በይፋ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮችን  መደብደብና ማንገላታት የዘወትር ስራቸው በመሆኑ በዞኑ ለመኖር አለመቻላቸውን ሪፖርቱ ጨምሮ ገልጦአል  የጉባዔው ተሳታፊዎችም መንግስት እንዲህ ያሉትን የግል አጀንዳ ያላቸውን ባለሥልጣናት በመከታተል እርምጃ ሊወስድ ይገባል ብለዋል ይህ ካልሆነ በሕዝቡ መካከል ተከባብሮ የኖረውን ሕዝብ ለማጨት መሆኑ የአደባባ ምሥጢር ነው ብለዋል ተሳታፊዎቸሁ ፡፡ በየሀገረ ስብከቶቹ ሁሉ ተመሳሳይ ችግሮች እንዳሉ  ሀገረስብከቶቹ  በየሪፖርታቸው ገለጠዋል ፡፡
ይሁን እንጂ የደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀገረስብከት በሀገረ ስበከቱ በየደብሩ ላይ   የተፈጸመውን   ፍንዳታ፤ የአቢያተ ክርስቲያናት መዘጋትና ሌሎች ችግሮችን ጨርሶ አለማንሳቱ ከፍተኛ ጥርጣሬ አሳድሮአል ችግሮቹ በሕዝቡ ዘንድ የሚታወቅ ቢሆንም የሀገረ ስብከቱ ሪፖርት ችግሩን ለጉባዔው አለማቅረቡ የችግሩ ተበባሪ አስመስሎታል   የሀገረ ስብከቱ ሥራስኪያጁ  እንደሚያሳየው ከሆነ ከላይ የተጠቀሱት ችግሮች እተባባሱ መሄዳቸው የሚታወቅ ቢሆንም  የአድባራቱን በመናፍቃን መወረርና መቃጠል ችግሮቸሁን ከመቅረፍ ይልቅ ማባበሱ ላይ ያቶከሩ ናቸው በማለት ተሳታፊዎች ገልጠዋል፡፡ አንባቢዎች የሀገረስብከቱ አጠቃላይ ችግሮች ስላልተነሱ በዝርዝር የምናቀርብ ይሆናል፡፡

                                   በአውሮጳ   የካህናት አንድነት ማኅበር ሊቋቋም መሆኑ ታወቀ በ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከመላዋ አውሮጳ   የተውጣጡ ካህናት፡” የ...