ሰዎች ከአንዱ ሀገር ወደ ሌላው ሀገር በስደት መዘዋወሩ
በጎላ በተረዳ
ይታወቃል ። ይሁን እንጂ ታዲያ የሚያሳዝነው ስደቱን እጥፍ የሚያደርገው የመንፈሳዊ አገልግሎት ፤የማኅሌቱ፤ የቅዳሴው
፤ የስብከተ ወንጌሉ እና የመሳሰለው መንፈሳዊ አገልግሎት መተግበሪያ
/ መገልገያ ቤተክርስቲያን አለመኖሩ ነው ። ምንም እንኩዋን በአውሮጳ
/ፓ የሉተራውያን የካቶሊካወያን አቢያተ እምነታት በሙሉ የተዘጉ እና
የእምነቱ ተከታዮች ሁሉን ነገር ትተውታል ። እጅግ በሚያስደንቅ ጥበብ የታንጹ አቢያተ እምነቶቻቸው በጣም ያሳዝናሉ ። ጥቂት የሚሆኑ
የእምነቱ ተከታዮች አረጋወያን በቻ እሁድ ረፋድ ላይ ይገኛሉ ። በስደት የሚገኙ ኦርቶዶክሳውያን መእመናን በየአካባቢያችው ይህንኑ
ቤተ እምነት አስፈቅደው ይገለግሉበታል አንዳንዶቹም አቅሙ ያላቸው ውርሃዊ ክፍያ በመክፈል ይክራዩታል። ይህንን ማድረግ ያልቻሉ ግን እሁድ ጠዋት
ሲከፈት ገብተው ቶሎ ቶሎ ብለው ቅዳሴውን ቀድሰው ንዋዬ ቅዱሳቱን
ይዘው ይወጣሉ ። ነሐሴ ኪዳነ ምሕረት የእመቤታችንን በዓለ ዕርገት
ለማክበር ከሐምቡርግ ፍራንክፈርት አቅራቢያ ወደ ምትገኝ ሐመረ ኖህ ኪዳነ ምሕረት ቤተክርስቲያን ተጓዝን በዓሉ
የተከበረው ነሓሴ 17 ነበረ ቅዳሴው በብፁዕ
አቡነ ሙሴ የደቡብ መዕራብና ምሥራቅ አውሮጳ/ፓ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳሳት ኢየተመራ እያለ ሰዓት ደረሰ ቶሎ ታቦቱ ወጥቶ ቶሎ መግባት
አለበት ስለተባለ ቶሎ ቶሎ ታቦተ ድንግል ማርያም ቶሎ ቶል ተብሎ ወጥቶ ቶሎ ተመልሶአል ወዲያውኑ ምንጣፉን መጋረጃውን የመሳሰሉትን ንዋዬ ቅዱሳቱን ሰብስቦ መሮጥ ነው ።ይህኛውስ ስደት መፍትሔው
ምንድንነው?
ብቸኛው አማራጭ የሉተራውያንን አቢያተ ክርስቲያናትን መግዛት

ይሁን እንጂ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ለዚህ ሁሉ ጅምር በጎ
አገልግሎት በተለይ በአውሮጳ/ፓ እንቅፋት እየሆነ የመጣው እንፈውሳለን
፤ እናጠምቃለን ባሕታውያን ነን የሚሉ ገለሰቦች ለበጎ ነገር በአንድነት ተባብሮ ያገለግል ይገለገል የነበረውን ዳግመኛ እንዳይስማማ አድርገው በመከፋፈል ላይ መገኘታቸውና ሕዝቡም ያለ ማስተዋል
መከተሉ ትልቅ ችግር ሆኖ ይታያል ፡፤ ከዚህ በተረፈ ግን የራሳችንን ቤተ ክርስቲያን የመግዛቱን ነገር በትኩረት መመልከት ይገባል
። እግዚአብሔር ይርዳን ።
ማስገንዘቢያ ሁለቱ የሉተራን ቤተ እምነት ናቸው