ልጥፎችን በመለያ ዜና መዋዕል. በማሳየት ላይ። ሁሉንም ልጥፎች አሳይ
ልጥፎችን በመለያ ዜና መዋዕል. በማሳየት ላይ። ሁሉንም ልጥፎች አሳይ

2014 ጁላይ 10, ሐሙስ

የቅ/ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ በማስተርስ መርሐ ግብር የመጀመሪያዎቹን ደቀ መዛሙርት አስመረቀ


ሐራ ዘተዋሕዶ

    graduates in M.TH and B.TH of HTTC of the class 2014
  • በ፲፱፻፹፯ ዓ.ም. ዳግመኛ ከተከፈተ ወዲህ የተመረቁት ደቀ መዛሙርት ብዛት 2175 ደርሷል
  • የተቋማዊ ነፃነት ዕጦትና የበጀት እጥረት ‹‹ጥናትና ምርምር ላይ እንዳላተኩር አድርጎኛል፡፡››
  • መሠረቱ የወጣው ሕንፃ ሥራ እንዲቆም በጀቱም እንዲመለስ የተላለፈው ትእዛዝ አወዛግቧል
  • ወደ ዩኒቪርስቲ ደረጃ የማሸጋገሩ ሒደት በግንባታ ላይ የሚገኘውን ሕንፃ መጠናቀቅ ይጠብቃል
  • ‹‹ከዛሬው ደስታችኹ የሚበልጥ ደስታ ከፊታችኹ ስለተዘጋጀ ደስታችኹ ዕጥፍ ድርብ ነው፡፡›› /ብፁዕ አቡነ ጢሞቴዎስ/
***
  • መስተጋድላን አኃውና አኃት ደቀ መዛሙርት በእጅግ ከፍተኛና ከፍተኛ ማዕርጎች ተመርቀዋል
  • የሴት ደቀ መዛሙርት ብዛት እና ውጤታማነት ‹‹አገልግሎቱን የተሟላ ያደርገዋል›› ተብሏል
  • ምሩቃኑ ነገ በጠቅ/ቤ/ክህነቱ የትምህርትና ማሠልጠኛ መምሪያ የአገልግሎት ምደባ ዕጣ ያወጣሉ
  • በየገጠሩ ሊቃውንቱ እየተገፉ ያልተማሩት በንዋይ ብዛት የሚንደላቀቁበት ኹኔታ በቅኔዎች ተተችቷል
  • ‹‹ግእዝ የኛ ብቻ ስላልኾነ በተቋማት ኹሉ ይሰጥ፤ ዲፕሎማውም ወደ ዲግሪ ይደግ፡፡››/ምሩቃን/
***

2014 ጁን 10, ማክሰኞ

የ2006 ዓም የበጎ ሰው ሽልማት አሸናፊዎች ተሸለሙ



ከ120 ተጠቋሚ ኢትዮጵያውያን መካከል በበጎ ሰው ዳኞች የተመረጡት ሰባት ኢትዮጵያውያን ‹በጎ ሰዎች› ቅዳሜ ግንቦት 30 ቀን 2006 ዓም በኢሊሊ ሆቴል በተከናወነ ሥነ ሥርዓት ተሸለሙ፡፡

2014 ጁን 9, ሰኞ

አስቸኩዋይ ጥሪ ለምእመናን በሙሉ




የታላቁ የደብረ ሊባኖስ ገዳምን ለመርዳት  ገዳሙ ጥሪ አስተላለፈ ገዳሙ በአሁን ሰዓት በመሬት መንሸራተት ምክንያት  ከፍተኛ አደጋ እንደተጋረጠበት ተጠቅሶ ሰኔ 8 ቀን ከ7፡30 ጀምሮ በጠቅላይ ቤተ ክህነት የስብከተ ወንጌል አዳራሽ  ቅዱስ ፓትርያርኩ ብፁዓን  ሊቃነ ጳጳሳት እና ምእመናን  በሚገኙበት ፕሮግራም ላይ ስለሁኔታው ይገለጣልና ስለዚህ ስቸኩዋይ ጥሪ አስተላልፎአል

2014 ሜይ 31, ቅዳሜ

‹‹የዓመቱ በጎ ሰው›› የመጨረሻዎቹ ዕጩዎች

የ2006 ዓም ‹‹የዓመቱ በጎ ሰው›› ሽልማት በሰባት ዘርፎች የመጨረሻዎቹ ዕጩዎች ታውቀዋል፡፡ በልዩ ልዩ ዘርፎች ዕውቀትና ተሞክሮ ያላቸው፣ በሞያው ለረዥም ዘመን ያገለገሉ ምሁራን፣ ጋዜጠኞች፣ ታዋቂ ሰዎች፣ ደራስያን፣ የዜማ ሰዎች፣ ሳይንቲስቶች፣ የባሕል ባለሞያዎች፣ የሚገኙበት 21 ዳኞች የመጨረሻዎቹን ሰባት ተሸላሚዎች ለመለየት ድምፅ እየሰጡ ነው፡፡ ዳኞቹ እርስ በርሳቸው የማይተዋወቁ ሲሆን በዘርፋቸው የራሳቸውን ድምፅ ብቻ ይሰጣሉ፡፡ የመጨረሻዎቹ ዕጩዎች የሚታወቁት በሚቀጥለው ሳምንት ውስጥ ነው፡፡
የሽልማቱ ዲዛይን የታዋቂው ሰዓሊ የእሸቱ ጥሩነህ ነው፡፡ ‹‹ጀ›› ፊደል ኢትዮጵያዊ ፊደል በመሆኑ ኢትዮጵያዊነትን የሚወክል ሲሆን ‹በ› ና ‹ሰ› የሚሉ ፊደላት ተቀጣጥለውበታል፡፡ ይህም የበጎ ሰው ሽልማትን የሚገልጥ ነው፡፡ ከላይ ደግሞ የ‹ሽ› ምልክት አለው፡፡ ይህም ሽልማትነቱን ያሳያል፡፡ ከላይ ያለው የፊደሉ ቅጥያ የቁልፍ መክፈቻ ምልክት ያለው ይኼም የተሸላሚዎቹን ቁልፍ ማኅበረሰባዊ ሚና ያመለክታል፡፡ ከፊደሉ ሥር የሚገኘው ደረጃ ደግሞ ተሸላሚዎቹ ደረጃ

                                   በአውሮጳ   የካህናት አንድነት ማኅበር ሊቋቋም መሆኑ ታወቀ በ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከመላዋ አውሮጳ   የተውጣጡ ካህናት፡” የ...