2014 ጃንዋሪ 1, ረቡዕ

ሊያዩት የሚገባ የቴሌቬዥን መርሐግብር ፡ ታህሳሥ 27 2006 ዓ.ም



  • አቡነ ተክለ ሃይማኖት ወይን ተክለው ለ12 ዓመታት በቦታው በመቀመጥ ሲጸልዩበት የነበሩበትና በርካታ ተዓምራትን ያከናወኑበት ቦታ ያዩበታል፡፡
  • ጻድቁ አቡነ ህጻኑ ሞአ የተወለዱበትና እንደ በሬ ተጠምደው በማረስ ገድላቸውን የፈጸሙበት ታላቅ ስፍራን ይመለከቱበታል፡፡
  • የቦታውን የቀደመ ታሪኩን ያውቁበታል ፤ ዛሬን ያዩበታል ፤ ነገን ያሳስብዎታል፡፡

(አንድ አድርገን ታህሳሥ 23 2006 ዓ.ም)፡- አቡነ ተክለ ሃይማኖት ከኢትዮጵያውያን አበው መካከል በእግዚአብሔር ቸርነት ተነሥተው ከሐዋርያ ማዕረግ  የደረሱ የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያንን ተስፋ ያደሱ ታላቅ አባት ሲሆኑ በሃያ ዓመት ዕድሜያቸው ጨለማ የሰለጠነባትን ክፍል ብርሃን እንድትሆን ‹‹አዲስ ሐዋርያ አድርጌ ሾሜሃለሁ›› ሲል ያከበራቸውና ለሾማቸው ‹‹ተክለ ሃይማኖት›› ብሎ ስም ለሠየማቸው ለፈጣሪያቸው ሕይወታቸውን  አሳልፈው ከሰጡበት ጊዜ ጀምሮ ያለ ጽልሁት ያለ ሐኬት በርዳታ በማስተማር በሰማዕትነት ፤ በድንግልና ፤ በምንኩስና ፤ በተባሕትዎና በልዩ ልዩ ተጋድሎ ሰማንያ ዘመን ሃይማኖቸውን ጠብቀው ፤ ፈጣሪያቸውን አገልግለው ፤ ገድላቸውን ካጠናቀቁ በኋላ በመቶ ዘመን ዕድሜያቸው በደብረ ሊባኖስ ገዳም አርፈዋል፡፡  

                                   በአውሮጳ   የካህናት አንድነት ማኅበር ሊቋቋም መሆኑ ታወቀ በ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከመላዋ አውሮጳ   የተውጣጡ ካህናት፡” የ...