2014 ዲሴምበር 23, ማክሰኞ

የሐዊረ ሕይወት መርሐ ግብር በደብረ ሊባኖስ አንድነት ገዳም





ታኅሣሥ 13 ቀን 2007 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
dscn3853ማኅበረ ቅዱሳን 7ኛውን የሐዊረ ሕይወት መርሐ ግብር በደብረ ሊባኖስ ጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት አንድነት ገዳም ታኅሣሥ 12 ቀን 2007 ዓ.ም. አካሔደ፡፡

መነሻውን አዲስ አበባ ከሚገኘው ዋናው ማእከል ያድረገው ጉዞ ከለሊቱ 12፡00 ሰዓት ጀምሮ ከ80 በላይ በሚሆኑ አንደኛ ደረጃ አገር አቋራጭ አውቶቡሶች ከ5000 በላይ ምእመናንን በመያዝ ተንቀሳቅሰዋል፡፡

dscn3547መርሐ ግብሩ በገዳሙ አባቶች በጸሎተ ወንጌል ከረፋዱ 4፡30 ተጀምሯል፡፡ ብፁዕ አቡነ ቀውስጦስ የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤ ብፁዕ አቡነ ማትያስ የካናዳ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤ የገዳሙ 12ቱ ንቡራነ እድ፤ እንዲሁም የአድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች በተገኙበት “ቅንነት ግን ፊቱን ታየዋለች” መዝ. 11፡7 የሚለውን ጥቅስ መነሻ በማድረግ የተዘጋጀው 7ኛው የሐዊረ ሕይወት መርሐ ግብር በመዝሙራቱ፤ እንዲሁም በስብከተ ወንጌል አገልግሎቱ ሲቀርብ ውሏል፡፡dscn3525

በዚህም መሠረት በጠዋቱ መርሐ ግብር ክፍል አንድ የወንጌል ትምህርት የማኅበረ ቅዱሳን መደበኛ ሰባኬ ወንጌል በሆኑት በመምህር ምሥጢረ ሥላሴ ማናዬ “በቅንነት የሚሄድ ይድናል” ምሳ.28፡18 በሚል ርእስ ትምህርተ ወንጌል ሰጥተዋል፡፡

የደብረ ሊባኖስ ገዳም ገዳማዊ ሥርዓቱ እንደተጠበቀ ቢሆንም የጎርፍ አደጋ፤ የብዝኅ ሕይወት መመናመን፤ የሕገ ወጥ የመሬት ወረራና ሌሎችም ችግሮች እየተፈታተኑት ይገኛል፡፡ ይህንን ችግር ለመቅረፍና ዘላቂ መፍትሔ ለማምጣት በገዳሙና በማኅበረ ቅዱሳን ባለሙያዎች ፕሮጀክቶች ተቀርጸው ወደ ሥራ ተገብቷል፡፡ ፕሮጀክቱን አስመልከቶ የተዋቀረው ኮሚቴ ተወካይ በዲያቆን ቱሉ ስለ ጥናቱ ገለጻ ተደርጓል፡፡

በቀረበው ጥናትም የገዳሙ የወደፊት አቅጣጫና ዕጣ ፈንታ ያሳሰባቸው የገዳሙ አባቶች በ2003 ዓ.ም. ለማኅበረ ቅዱሳን በደብዳቤ በማሳወቃቸው ጥናቱን ለማጥናት እንደተቻለ ገልጸዋል፡፡

የተቀረጹት 11 ፕሮጀክቶች በሦስት ዙር በመክፈል እጅግ አንገብጋቢ የሆኑትን፣ የመጸዳጃና የአካባቢ ንጽሕና፤ የመሬት መንሸራተርትና የጎርፍ አደጋ፤ የመነኮሳት በዓት ችግር፤ የአብነት ትምህርት ቤት አደጋ ላይ መሆኑ፤ መቃብር ቦታ ችግር ቅድሚያ ተሰጥቷቸው እንደሚሰሩ የጠቀሱት ዲያቆን ቱሉ በሁለተኛው ዙር የአብነት ትምህርት ቤትና የሥልጠና ማእከል ግንባታ፤ መኪና ማቆሚ ቦታ ዝግጅት፤ መቃብር ሥፍራ ዝገጅት ፕሮጀክች እንዲሁም በሦስተኛው ዙር የጤና ጣቢያ ግንባታ፤ የሁለገብ ሕንፃ ግንባታ፤ የአስኳላ ትምህርት ቤት ግንባታ ፕሮጀክቶች ይተገበራሉ ብለዋል፡፡

በቅድሚያ ሊሰሩ ከታቀዱት ውስጥ 24 ክፍል ያለው መጸዳጃ ቤት ግንባታ ተጠናቆ አገልግሎት መሥጠት መጀመሩን፤ 8 ክፍሎችን የያዘ የገላ መታጠቢያና መጸዳጃ ቤት መጠናቀቁን፤ የሕንፃ ቤተ ክርስቲያኑ መሠረት /ቤዝመንት/ እየገፋ ያለውን ጎርፍ ለመከላከል 100 ሜትር ርዝመት እና 10 ሜትር ቁመት ያለው የጎርፍ መከለያ ግንባታ በመጠናቀቅ ላይ እንደሚገኝ፤ በቅርቡም 2500 ሰው ማስተናገድ የሚችል የእንግዳ ማረፊያና ሁለገብ አዳራሽ ለመሥራት ዲዛይኑ አልቆ ቦታው በዝግጅት ላይ እንደሚገኝ ተጠቅሷል፡፡

dscn3668ከሰዓት በኋላ የተካሔደውን መርሐ ግብር በማኅበረ ሰላም መዘምራንና በሊቀ ዲያቆን ምንዳዬ ብርሃኑ ያሬዳዊ ዝማሬ በማቅረብ ተጀምሯል፡፡

ሁለተኛው የወንጌል ትምህርት በደብረ ገነት ሞጣ ቅዱስ ጊዮርጊስ የሐዲሳትና የፍትሐ ነገሥት ጉባኤ ቤት መምህር በሆኑት መምህር ወልደ ትንሣኤ “ቸልተንነት” በሚል ርእስትምህርት ተሰጥቷል፡

dscn3740ብፁዕ አቡነ ቀውስጦስ የሰላሌና ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ባስተላለፉት መልእክት “ዛሬ ባየሁት ነገር በጣም ተደስቻለሁ፤ በእንደዚህ ያለ ሰፊ ጉባኤ ተገኝቼ አላውቅም፡፡ ሊቁ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ `በጉባኤ መካከል እያለን ብቻችንን የቆምን ይመስለናል` ይላል፡፡ እኔም ምንድነው ነገሩ፤ የት ነው ያለሁት እስክል ድረስ በመንፈሳዊ ተመስጦ ውስጥ ገብቼ ነበር፡፡ ማኅበረ ቅዱሳን በዚህ ታላቅ ገዳም ይህንን ታላቅ ጉባኤ በማድረጉ ምእመናን እምነታችሁን በሥራ እየተረጎማችሁት መሆኑን ያየሁበት ነው. . . ክርስቲያናዊ ሥራ እየሠራ ያለ ክርስቲያን መሥጋት የለበትም፡፡ ፈቃዱን እየፈጸሙ የሚያገለግሉ ሁሉ ነፍሳቸው በአደራ ጠባቂው በእግዚአብሔር እጅ ላይ ነው፡፡ ራሳችሁን ለእግዚአብሔር አደራ ሰጥታችሁ ክርስቲናዊ አገልግሎታችሁን እስከ መጨረሻው ድረስ እንድትፈጽሙ አደራ እላለሁ” ብለዋል፡፡

ብፁዕ አቡነ ማትያስ በሰጡት ቃለ ምእዳን “ልጅ አባቱ አይዞህ ካለው ካሰበው ሁሉ ነገር ላይ መድረስ ይችላል፡፡ በእግዚአብሔር ትእዛዝና ሕግ የሚጓዝ ብፁዕ ነው እንዳለው ቅዱስ ዳዊት የምንመካውም ኃይላችንም እግዚአብሔር ስለሆነ በርትታችሁ አገልግሎታችሁን ፈጽሙ” ብለዋል፡፡

“ወኩኑ ታቦተ መንፈሳዌ ለክህነት ቅድስት ወንጽሕት፤ ቅዱሳን ካህናት እንድትሆኑ መንፈሳዊ ቤት ለመሆን ተሠሩ” /፩ኛ ጴጥ. ፪፥፭/





ታኅሣሥ 14ቀን 2007 ዓ.ም.
መምህር ኅሩይ ባዬ
የዲያቆናት አለቃ የመጀመሪያው ሰማዕት ቅዱስ እስጢፋኖስ በሠላሳ አምስት ዓመተ ምሕረት በድንጋይ ተወግሮ ሰማዕትነትን ተቀበለ፡፡ ያን ጊዜም በክርስቶስ የባሕርይ አምላክነት አምነው ክርስቲያን የሆኑ የአይሁድ ወገኖች ተበተኑ፡፡

ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስም መከራ ውን ሳይሠቀቁ እምነታቸውን ጠብቀው በሃይ ማኖት እንዲጸኑ በስድሳ ዓመተ ምሕረት መጀ መሪያይቱን መልእክት ለተበተኑ ምእመናን ጽፎላ ቸዋል፡፡

ወኩኑ ታቦተ መንፈሳዌ ለክህነት ቅድስት ወንጽሕት፤ ቅዱሳን ካህናት እንድትሆኑ መንፈ ሳዊ ቤት ለመሆን ተሠሩ ሲል ሰማያዊ ጥቅም ከማያሰጥ ከክህነተ ኦሪት በተለየ ለክህነተ ወን ጌል መንፈሳዊ ማደሪያ ለመሆን ተዘጋጁ ማለቱ ነው፡፡ ቅድስት ማለቱም ምሳሌያዊ ከሆነው የኦ ሪት ክህነት ተለይቶ አማናዊ ክህነትን ለመ ያዝ የእግዚአብሔር ማደሪያ መንፈሳዊ ቤት ሆኖ መሠራት ስለሚያስፈልግ “ቅዱሳን ካህናት እንድትሆኑ መንፈሳዊ ቤት ለመሆን ተሠሩ” እያለ ይጽፋል፡፡

በዚህ ትምህርታዊ ስብከት ካህን የሚለውን ቃል በመተርጐም የካህናትን ተልእኮ በማመልከት የሓላፊነቱን ታላቅነትና ክቡርነት እንመለከታለን፡፡ በሁለተኛው ክፍልም ክህነት ከእግዚአብሔር የተቀበልነው፣ የታደልንለት እና የተጠራንለት አደራ በመሆኑ ሥልጣነ ክህነታችንን ጠብቀን ራሳችንን፣ ቤተ ክርስቲያናችንን፣ እምነታችንን፣ እና ምእመናንን እንዴት መጠበቅ እንዳለብን እንማራለን፡፡

“ተክህነ” የሚለው ቃል ተካነ አገለገለ ክህነትን ተሾመ /ተቀበለ/፤ በእግዚአብሔርና በሰዎች መካከል ቆሞ ለማገልገል ካህን ተባለ የሚለውን ትርጓሜ ያመለክታል፡፡ “ክሂን” ከሹመት በኋላ ማገልገልን፤ “ተክህኖ” ከማገልገል በፊት መሾምን የሹመትን ጊዜ የተቀበሉበትን ዕለትና ሰዓት ያሳያል፡፡

ክህነት ቢልም መካን ማስካን ካህንነት ተክኖ ማገልገልን ያሳያል፡፡ ካህን የሚለውን ቃል ሶርያ ውያን “ኮሄን”፣ ዕብራውያን “ካህን”፣ ሲሉት ዐረ ቦች ደግሞ ካህና በማለት ይጠሩታል፡፡ ካህን የሚ ለውን ቃል በቁሙ ቄስ ጳጳስ የእግዚአብሔር አገልጋይ የሕዝብ መሪ አስተማሪ መንፈሳዊ ሀብት ብለው አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ ይተረጉሙ ታል፡፡

እነዚህን የመዝገበ ቃላት ትርጓሜዎች እንደ ዋልታ አቁመን ጠቅላላ ትርጓሜ መስጠት ይቻ ላል፡፡ ክህነት “ተክህነ” አገለገለ ከሚለው የግእዝ ግስ ይወጣል፡፡ ክህነት የሥልጣኑ ስም ሲሆን አገልጋዮቹ ካህናት ይባላሉ፡፡ ክህነቱ የሚገኝበት መንፈሳዊ ምሥጢርም ምሥጢረ ክህነት ይባላል፡፡ በሚታይ የአንብሮተ እድ አገልግሎት የማይታይ የሥልጣነ ክህነት ሐብት ይገኝበታልና ምሥጢር የተባለበት ምክን ያትም በሚታይ አገልግሎት የማይታይ ጸጋ መንፈስ ቅዱስ ስለሚገኝበት ሲሆን ምሥጢረ ክህነትን የጀመረው /የመሠረተው/ ባለቤቱ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡

በክቡር ደሙ የዋጃትንና የመሠረታትን ቤተ ክርስቲያን እንዲያገለግሉ ካህናትን የለየ፣ የጠራና የሰየመ አምላካችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡ ቅዱሳን ሐዋርያት ከትንሣኤው በኋላ የመነሣቱን አዋጅ ለማብሰር ወደ ዓለም ሲላኩ በክህነታቸው ታላላቅ ተአምራትን አድርገዋል፡፡ /ማር. ፲፮፥፲፮/ ያስሩም ይፈቱም ነበር፡፡ /ማቴ. ፲፰፥፲፰/ ይህ የማሰርና የመፍታት ሥልጣን እስከ ኅልፈተ ዓለም የሚቀጥል መሆኑን አምላካችን በቅዱስ ወንጌል አስተም ሯል፡፡ /ማቴ. ፳፰፥፳/

ክህነት በቤተ ክርስቲያናችን አስተምህሮ ሦስት ደረጃዎች አሉት፡፡ እነርሱም ዲያቆን፣ ቄስ፣ ኤጲስ ቆጶስ በመባል ይታወቃሉ፡፡ የአንጾኪያው ሊቀ ጳጳስ ቅዱስ አግናጥዮስ እነዚህን ሦስት የክህነት ደረጃ ዎች እንዲህ በማለት ገልጿቸዋል፤ “ለእግዚአብሔር የሚገባችሁን ሁሉ ለማድረግ ፍጠኑ፤ የሚመ ራችሁ ኤጲስ ቆጶስ የእግዚአብሔር እንደራሴ ነው፡፡ ቄሱም እንደሐዋርያት ዲያቆናትም ለክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ባለአደራዎች ናቸውና”

በሌላ አገላለጥ ከሦስቱ ጾታ ምእመናን /ወንዶች፣ ሴቶችና ካህናት/ አንዱ ካህን ነው፡፡ ካህን ከወንዶችና ከሴቶች ምእመናን በተለየ ከፍ ያለ ሓላፊነት አለው፡፡ ይህ ሓላፊነት ምድ ራዊ ሳይሆን ሰማያዊ፤ ሥጋዊ ሳይሆን መንፈ ሳዊ ሓላፊነት ነው፡፡ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ አንድ ወጣት ቅስና ለመቀበል ፈልጐ ወደ እርሳ ቸው ሔደ፡፡ ቅዱስነታቸውም አሁን የምሰጥህ የክ ህነት ሥልጣን ሹመት ሳይሆን ሓላፊነት ነው በማለት ተናግረዋል፡፡

ሹመት ደረት ያቀላል፤ ሆድን ይሞላል፤ ሓላ ፊነት ግን ያሳስባል፣ ያስጨንቃል፣ እንቅልፍ ያሳ ጣል፣ ክህነት ሓላፊነት በመሆኑ አንድ ካህን ሳይ ታክትና ሳይሰለች በጸሎት በጾምና በስግደት ስለ ራሱ ኃጢአት እና ስለ መንፈሳዊ ልጆቹ ክርስቲ ያናዊ ሕይወት ስለሚጨነቅ ምንጊዜም ቢሆን ዕረ ፍት የለውም፡፡ አምላካችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ “ግልገሎቼን አሠማራ፣ ጠቦቶቼን ጠብቅ፣ በጎቼን አሠማራ” /ዮሐ. ፳፩፥፲፮/ ብሎ ለካህናት የኖላዊነትን ሓላፊነት የሰጠበት የአደራ ቃልም እንደዋዛ የሚታይ አይደለም፡፡


ካህን ካህን ከመሆኑ አስቀድሞ ምእመናንን የማስተማር ብቃቱ፣ ቤተሰቡን የመምራት ችሎ ታው፣ የአንድ ሴት ባል መሆኑ፣ ቤተሰባዊ ሓላፊ ነቱን የመወጣት አቅሙ፣ ልጆቹን የማስተዳደር ክሂሎቱ እና ከሰዎች ጋር ያለው የሠመረ ግንኙ ነቱ ጤናማ ሊሆን እንደሚገባ ቅዱሳት መጻሕ ፍት ያስረዳሉ፡፡

ካህን ከሕይወቱ ሊያስወግዳቸው የሚገቡ ክፉ የሆኑ ጠባያትም በመጽሐፍ ተዘርዝረዋል፡፡ ካህን ለብዙ የወይን ጠጅ የማይጎመጅ /የማይ ሰክር/፣ በሁለት ቃል የማይናገር፣ ከፍቅረ ንዋይ የራቀ፣ አጥብቆ ገንዘብን የማይወድ፣ በንጹሕ ሕሊና የሃይማኖትን ምሥጢር የሚጠብቅ፣ ግልፍተኛ ያልሆነ፤ ሊሆን ይገባዋል፡፡ በአንጻሩም ትሑት፣ የማይጋጭ፣ ይቅር የሚል፣ ትዕግሥተኛ የሆነ እንደሆነ ለሚመራቸው ምእመናን ትክክለኛ አርአያ መሆን ይችላል፡፡

ካህናት በሐዋርያት መንበር ተቀምጠው የማሠርና የመፍታትን ሓላፊነት ይወጣሉ፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንደጻፈልን “ካህናት በምድር የፈጸሙትን ጌታ በሰማይ ያጸናላቸ ዋል፤ የባሮቹን /የካህናትን/ አሳብ ጌታ ይቀበለ ዋል” በመሆኑም ካህናት በምድር ላይ የሚፈጽሙአ ቸውን ምሥጢራት እግዚአብሔር በሰማያዊ ምሥ ጢር ተቀብሎ ያከብራቸዋል፡፡
ኤጲስ ቆጶሳት መዓርገ ክህነቱን ለሚመለከ ታቸው ወገኖች ከመስጠታቸው በፊት የቅድ ሚያ ጥንቃቄ ሊያደርጉ እንደሚገባ፤ ምእመናንም በጉዳዩ ላይ አሳብና አስተያየታቸውን ለኤጲስ ቆጶሱ ቢናገሩ መልካም እንደሆኑ የሚደነግጉ መጻ ሕፍት አሉ፡፡ ስለሆነም

ካህኑ ከመሾሙ በፊት፡-

1. የሃይማኖትን ምሥጢር ጠንቅቆ የሚያውቅ መሆን እንዳለበት ሐዋርያት በጉባኤ ኒቅያ ደንግገዋል፡፡ /ጉባኤ ኒቅያ ፫፻፳፭ ቀኖና ፲፱/
2. አዲስ አማኒ ያልሆነ /ጉባኤ ኒቅያ ፫፻፳፭ ቀኖና ፪-፱/
3. የመንፈስ ጤንነት ያለው /የሐዋ. ቀኖና ፸፰/
4. ዕድሜው ከሠላሳ ዓመት ያላነሰ፤ ሊሆን እንደ ሚገባ /ስድስተኛው ሲኖዶስ ቀኖና ፲፫/ በግልጥ ያስቀምጣል፡፡

የካህናት ተልእኮ

የኤጲስ ቆጶሳት ተልእኮ ቀሳውስትን እና ዲያቆናትን ይሾማሉ፣ ያስተምራሉ፣ ያጠምቃሉ፣ ያቆርባሉ፡፡ በሀገረ ስብከታቸው ያሉት ምእመናን ማኅበራዊና መንፈሳዊ ችግር ሲደርስባቸው ይመክ ራሉ፣ ያጽናናሉ “ሕዝቡን ጠዋትና ማታ ለነግህና ለሠርክ ጸሎት በቤተ ክርስቲያን ይገኙ ዘንድ” ያዝዟቸዋል፡፡

የቀሳውስት ተልእኮ፡- እንደ ኤጲስ ቆጶሱ ያስተ ምራሉ፤ ያጠምቃሉ፣ ያቆርባሉ፡፡

የዲያቆናት ተልእኮ፡- ለኤጲስ ቆጶሱና ለካህኑ ይላላካሉ፤ ምሥጢራትን ግን የመፈጸም ሓላፊነት የላቸውም፡፡
ከእነዚህ መሠረታዊ የክህነት ደረጃዎች ሌላ በቤተ ክርስቲያን የሚታወቁ መዓርጋት አሉ፡፡ እነርሱም ንፍቅ ዲያቆን፣ አንባቢ /አናጉንስጢስ/ መዘምር፣ ኀፃዌ ኆኅት /በረኛ/ በመባል ይታወቃሉ፡፡ ንፍቅ ዲያቆን ዋናውን ዲያቆን ይረዳል፡፡ አንባቢ /

አናጉንስጢስ/ በቅዳሴ ጊዜ መልእክታትን ያነብ ባል፡፡ መዘምር ደግሞ የመዝሙር አገልግሎት ይሰጣል፡፡ ኀፃዌ ኆኅት ቤተ ክርስቲያንን ይጠር ጋል፣ ያጸዳል፣ ያነጥፋል፣ ደወል ይደውላል፣ በጸሎት ጊዜ ቤተ ክርስቲያንን ይከፍታል ይዘጋል፡፡
ከእነዚህ የተቀብዖ ስያሜዎች ውስጥ ፓትር ያርክ የሚባለው መዓርግ ከሊቃነ ጳጳሳት መካከል ለአንዱ በፈቃደ እግዚብሔር በምርጫ ይሰየ ማል፡፡

ይህ የመዓርግ ስም የተጀመረው በአምስተ ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ሲሆን በዚህ የመዓርግ ስም ይጠሩ የነበሩት የሮም፣ የእስክንድርያና የአን ጾኪያ ታላላቅ ከተሞች አባቶች /መጥሮ ፖሊሶች/ ነበሩ፡፡ በኋላ ግን ራሳቸውን ችለው የሚተዳደሩ አገሮች ሁሉ የየራሳቸውን ፓትርያርክ ሹመዋል፡፡ ፓትርያርክ ማለት በግሪኩ ቋንቋ ርእሰ አበው /አባት/ ማለት ነው፡፡

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስ ቲያን ሥርዐት ሦስቱ ዐበይት የክህነት መዓርጋት ዲቁና ቅስና ኤጲስ ቆጶስ ናቸው፡፡ ንፍቀ ዲቁና አንባቢ፣ መዘምርና ኀጻዌ ኆኅት በመባል የሚታ ወቁት አራቱ ንኡሳን መዓርጋት በአገልግሎት ውስጥ በግልጽ የሚታዩና በዲቁና ወስጥ የሚጠ ቃለሉ መዓርጋት ናቸው፡፡
ሥልጣነ ክህነት የነፍስ ሕክምና አገልግሎት በመሆኑ ልዩ ጥንቃቄና ክብካቤ ያሻዋል፡፡ ሥልጣነ ክህነት በዘመድ፣ በዘር፣ በአገር ልጅነት በገንዘብ አይሰጥም፡፡ ለመሾም ተብሎም እጅ መንሻ መስ ጠትና መቀበል ፈጽሞ የቤተ ክርስቲያን ትው ፊት፣ ሥርዐትና ቀኖና አይደለም፡፡

የካህናትን ክብር ካስተማሩን አበው መካከል አንዱ ቅዱስ አትናቴዎስ በቅዳሴው “ኦ ካህናት አንትሙ ውእቱ አዕይንተ እግዚአብሔር ብሩሃት ተናጸሩ በበይናቲክሙ አሐዱ ምስለ ካልዑ፤ ካህ ናት ሆይ ብሩሃን የእግዚአብሔር ዓይኖች እናንተ ናችሁ እርስ በርሳችሁ አንዱ ካንዱ ጋራ /ተያዩ/ ተመለካከቱ” ይላል፡፡ ይህም በችግሮቻችን ዙርያ መወያየት፤ መነጋገርና መደማመጥ የሚያስፈልግ መሆኑን ያስረዳናል፡፡

“የኩነኔ አገልግሎት ክብር ከሆነ ይልቅ የጽድቅ አገልግሎት በክብር አብዝቶ ይበልጣልና” /፪ኛ ቆሮ. ፫፥፱/ እንዳለው ሐዋርያው የክህነት አገልግሎት የተለየ እና ክቡር መሆኑን መገንዘብ ይገባል፡፡ ክህ ነት ከእግዚአብሔር የተገኘ መሆኑ ብቻ ሳይሆን ወደ እግዚአብሔርም የሚያደርስ ታላቅ መሰላል ነው፡፡

የሥርዐተ ጥምቀት፤ የሥርዐተ ቁርባን፤ የሥርዐተ ተክሊልና የምሥጢረ ንስሐ መፈጸሚያና ማስፈጸሚያ መንፈሳዊ መሣሪያ ሥልጣነ ክህነት መሆኑን ስንረዳ የምንሰጠው ክብርም የተለየ መሆኑ አያጠራጥርም፡፡ “ወወሀቦሙ ሥልጣነ ዘከማሁ ይእስሩ ወይፍትሑ ኲሎ ማእሠረ አመጻ፤ እንደ እርሱ የኃጢአትን ማሠሪያ ያሥሩና ይፈቱ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው” /ዮሐ. ፳፥፳፪-፳፫/ መዓርጉ ክቡር በመሆኑ አምላካችን ልዑል እግዚአብሔር ክቡር የሆነውን ክህነት አክብረን እንድንከብርበት መለኮ ታዊ ኃይሉ ይርዳን፡፡

                                   በአውሮጳ   የካህናት አንድነት ማኅበር ሊቋቋም መሆኑ ታወቀ በ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከመላዋ አውሮጳ   የተውጣጡ ካህናት፡” የ...