2016 ሴፕቴምበር 23, ዓርብ

 የመስቀል ደመራ በዓል ለመጀምሪያ ጊዜ በፊንላንድ ሄልሲንኪ  በአደባባይ  እንደሚከበር ተገለጸ

ፊንላንድ በሰሜን አውሮፓ ሀገሮች መካከል አንዷ ናት 5.5 ሚሊየን ሕዝብ እንድሚኖርባት የሚነገርላት ፊንላንድ ወደ ሰሜን ዋልታ ጠጋ ያለች ሀገር በመሆኗ በቅዝቃዜዋም ትታወቃለች  ነዋሪዎቿ በሥነ ምግባራቸውና  በዝምታቸው ይታወቃሉ። ረዘም ያለ ጊዜ በሀገሪቷ የቆዩ የውጪ ዜጎችም ይህንኑ ጠባይ ይጋሩታል   በሃይማኖት በኩል ሲታይ በሀገሪቱ 2 % ያህሉ የፊንላንድ ኦርቶዶክስ  ሃይማኖት ተከታይ ሲሆኑ የቀሩት በአብዛኛው ሉተራውያን  ናቸው  የውጪ ዜጎች ሁሉም  አኃት አቢያተ ክርስቲያናት ቢኖሩም ክፍተኛ እንቅስቃሴ ያላቸው  ግን  የኢትዮጵያና እና የኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ተከታዮች ናቸው   በፊንላንድ ዋና ከተማ  ሄሊሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን እና የደብረ ሰላም መድኃኔዓለም  የኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አቢያተ ክርስቲያናት  ይገኛሉ ። ሁለቱም አድባራት መንፈሳዊ እና ምኅበራዊ አገልግሎቶችን በጋራ ይፈጽማሉ ። በሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ለመጀመሪያ ጊዜ  በ2009 ዓ.ም መስከረም 16 ቀን በሀገሪቱ ሰዓት አቆጣጠር  ከ 1730  ጀምሮ እንደ ሀገራችን ሁሉ በአደባባይ / መስቀል አደባባይ / ይከበራል  የፊንላንደ ኦርቶዶክስ የከተማው ከንቲባ ልዩ ልዩ መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት መጋበዛቸው ተገልጧል በአሁን ሰዓት ምእመናኑ በዝግጅት ላይ ይገኛሉ ምንም በስደት ሀገር ብንኖርም  ልክ እንደ ሀገራችን ሕዝቡ የሀገር ባህል ልብሱን ለብሶ ሕፃናትም ሁሉ ተሰልፈው በዝማሬ የደመራው ሥነ ሥረዓት  በልዩ  ሁኔታ እንደሚከበር  ይጠበቃል ።                                                       እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ አደረሳችሁ

                                   በአውሮጳ   የካህናት አንድነት ማኅበር ሊቋቋም መሆኑ ታወቀ በ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከመላዋ አውሮጳ   የተውጣጡ ካህናት፡” የ...