2014 ማርች 13, ሐሙስ

የቤተ ሰብእ መሪ

                      

                                            አርባ ምንጭ መንበረ ጵጵስና

                                                                                                                                                              ከካቲት 28- 30 ድረስ ለመንፈሳዊ አገልግሎት ወደ አርባ ምንጭ  ከባልደረቦቼ መጋቤ ሐዲስ መንግስቱ አማረ ፤ ዲ. ተመስገን ዘገዬ እና ዘማሪት መሠረት ማሞ ጋር በመሆን ተጉዘን ነበር  አርባ ምንጭ እንደሚታወቀው ሁለቱን ሐይቆች አባያ እና ጫሞን ዓይን አድርጋ ውበትን የተላበሰች ቱሪስቶች ሁል ጊዜ የማይለይዋት ሞቃት ከተማ ናት ፡ አርባ ምንጭ  በከተማዋ ከላይና ከታች/ ከመግቢያዋና ከመወጫዋ ታላላቅ ዩኒቨርስቲዎች ይገኛሉ ፡፡ የሀገረ ስብከቱም ሊቀጳጳስ አቡነ ኤልያስም በቅርቡ አሰርተው በቅዱስ ፓትርያርኩ ያስመረቁትም ሁለገብ የሆነ መንበረ ጵጵስና ሁለቱን ሀይቆች በርቀት ይቆጣጠራል፡፡ እኛም የተጓዝንበትም አገልግሎት ውጤታማ ነበረ፡እሁድ ከቅዳሴ በኋላ በከተማዋ መሃል በሚገኘው ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ቅጥር ገቢ ወደ ሚገኘው የማኅበረ ቅዱሳን አርባ ምንጭ ማዕከል ብቅ አልን አባላቱ ውይይት ላይ ናቸው፡፡ የመወያያ አጀንዳው ‹‹የቤተ ሰብእ መሪ ›› የሚል ነበር  አባላቱ መንፈሳዊ አገልግሎትን  ለማጠናከር ሲሉ አሥር ያህል አባላት ያሉት ቡድን አዋቅረዋል  አንድ የቤተ ሰብእ መሪ አለው፡፡ ቤተ ሰብእ መሪው ስለመንፈሳዊ ሕይወታቸው አጠቃላይ ይከታተል ዘንድ ተመርጧል ለምሳሌ፤
                                ከንስሐ አባታቸው ጋር ያለቸውን   ግንኙነት
                                 በሰንበት ት/ቤት አገልግሎት
                                 በሰበካ ጉባኤ ያለቸውን ተሳትፎ
                                 በማህበራዊ ኑሮ
                                 ከሀገረ ስብከቱ እና አድባራት አገልጋዮች ያለቸውን መልካም ግንኙነት ይከታተላል የቤተ ሰብእ መሪው ፤ እኔም ይህ ተሞክሮ ለሌሎች የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮ ጥሩ ምሳሌ ስለሆነ ይበል እንላለን፡፡
                                           

                                   በአውሮጳ   የካህናት አንድነት ማኅበር ሊቋቋም መሆኑ ታወቀ በ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከመላዋ አውሮጳ   የተውጣጡ ካህናት፡” የ...