2015 ኖቬምበር 30, ሰኞ

ግልጹ ደብዳቤ ለምን የአወዛጋቢነት ቁመና ይሰጠዋል? (የግል ምልከታ)


". . . በቤተ ክርስቲያኒቱ ፈቃድ ሳይሰጣቸው እና ሳያሳውቁ በየድንኳኑና አዳራሹ ጉባኤ የሚያካሂዱ መጻሕፍት፣ መጽሔት እና ጋዜጦች የመዝሙር ጋዜጦች በቤተክርስቲያኒቱ ስም የሚያሳትሙና የሚነግዱ ሁሉ ሕገ-ወጥ ተግባር እየፈጽሙ መሆኑንና በአሁኑ ጊዜ በልዩ ልዩ ሚዲያዎች በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስም የራሳቸውን ዓላማና ፍላጎት እያስተላለፉ ያሉ ተቋማት ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ውክልና ሳይሰጣቸው ሕገ-ወጥ ተግባር የሚፈጽሙ ግለሰቦች፣ ማኅበራትና ድርጅቶች ሁሉ ቤተ ክርስቲያኒቱን የማይወክሉ ስለኾነ ይኸው ሕገ-ወጥ ተግባራቸው ወደፊት እንዳይቀጥል ለኢ.ቤ.ኤስ የቴሌቪዥን ድርጅት እና የሚድያ አገልግሎት ኅትመት ለሚሰጡ ድርጅቶች እንዲሁም ለሚመለከታቸው ሚኒስቴር መ/ቤቶች በደብዳቤ እንዲገለጽ ኾኖ ከድርጊታቸው የማይቆጠቡ ከኾነ ግን በሕግ የተሰጣትን መብቷን ማስከበር የግድ ስለኾነ በጠቅላይ ቤተ ክህነት ሕግ አገልግሎት በኩል የሕግ ክትትል እንዲደረግባቸው " ሲል የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት በቁጥር ፴፭/፲፬/፳፻፰ በቀን ፳፫/፪/፳፻፰ ዓ.ም. ለጠቅላይ ቤተ ክህነት በተጻፈ ደብዳቤ ትእዛዝ አስተላልፏል፡፡
ይኽንን ደብዳቤ ተከትሎ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ለኢ.ቢ.ኤስ የቴሌቪዥን ድርጅት በሚል አድራሻ ". . . ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፈቃድ ሳይሰጣቸውና በቀጥታ ከኢ.ቢ.ኤስ የቴሌቪዥን ድርጅት ጋር ግንኙነት በመፍጠር እየተካሄደ ያለው ሕገ-ወጥ ድርጊት ሊታረም የሚገባ ድርጊት እንደመኾኑ መጠን ቤተ ክርስቲያናችን በሕገ መንግሥቱ የተሰጣትን መብት በመጋፋት በአሁኑ ጊዜ በልዩ ልዩ ሚድያዎች በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስም የራሳቸውን ዓላማና ፍላጎት እያስተላለፉ ያሉ ተቋማት እና ግለሰቦች፣ ማኅበራትና ድርጅቶች ሁሉ ቤተ ክርስቲያኒቱን የማይወክሉ እና እውቅና ያልተሰጣቸው በመኾኑ ይኸው ሕገ-ወጥ ተግባራቸውን እንዳይቀጥሉ በጥብቅ እያሳሰብን ከአሁን በኋላ ግን ከቤተ ክርስቲያኗ ፈቃድ ሳይሰጣቸው እንደካሁን ቀደም ወደፊት እንዳይቀጥል የኢ.ቢ.ኤስ ቴሌቪዥን ጣቢያው ፕሮግራማቸውን ተቀብሎ የሚያስተናግድ ከኾነ ሕገ መንግሥታዊ መብታችንን ለማስከበር ሲባል የቴሌቪዥን ድርጅት በሕግ የምንጠይቅ መኾናችንን እየገለጽን. . ." በማለት በቁጥር ፰፻፷፭/ ፳፯፻፹፱/፳፻፷ በቀን ፯/፫/፳፻፷ ዓ.ም. በተጻፈ ደብዳቤ እገዳ እንዲደረግ ጠይቋል፡፡
በእነዚህ የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት እና የጠቅላይ ቤተ ክህነት ደብዳቤዎች ውስጥ እገዳ የተጣለባቸው እነማን ናቸው? የሚለው አወዛጋቢ ጥያቄ ምላሽ ማግኘት አለበት፡፡ "ሕገ-ወጥ" የሚለው ቃል ሊቀጸል የሚገባው ለእነማን ነው? ከእነዚህ ጋር ማኅበረ ቅዱሳን ሊደመር ይችላልን? ቀድሞውኑስ ለጊዜው የታወቁትን እና እንዲታገዱ የተፈለጉትን በስም ጠቅሶ ወደፊት ሊነሱ የሚችሉትን ደግሞ በጥቅሉ "ፈቃድ የሌላቸው" ማለት አይቻልም ነበርን?
በእርግጥ እንደ ኢ.ቢ.ኤስ. ላሉ ሦስተኛ ወገኖች የተጻፈው መልእክት ተጨማሪ ማብራሪያ ሊፈልግ እንደሚችል ማሰብ አይከብድም፡፡ በተቃራኒው ደግሞ እገዳው ተግባራዊ እንዲኾን ለጻፈው አካል ደግሞ ሙሉ በሙሉ ስለእነማን እንደተጻፈ ለመናገር መደናገር አይጠበቅም፡፡ ደብዳቤው እጁ የገባው የቴሌቪዥን አሠራጭ እነማንን እንደሚመለከት ለማወቅ ግርታ እንደተፈጠረበት ጠቅሶ እስኪታወቅ ድረስ ሥርጭቱን ለማቋረጥ መገደዱን አሳውቋል፡፡ በዚህ ጊዜ ወይ ሁሉንም በቤተ ክርስቲያን ስም መርሐግብር የሚያስተላልፉትን አለበለዚያም እገሌና እገሌ ብሎ መናገር መቻል ያለበት ለእኔ ጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ነው፡፡
ለዚህ ማብራሪያ የተጠየቀው ጠቅላይ ቤተ ክህነት ግን ጉዳዩን ወደ ቋሚ ሲኖዶስ እንደመራው ታውቋል፡፡ መሠረታዊው ጥያቄ መነሣት ያለበት እዚህ ላይ ነው፡፡ የሕግ ጥያቄ ተነሥቶ ቢኾን ሕግ ተርጓሚ ወደኾነው ቅዱስ ሲኖዶስ መምራቱ ምንም የማያሻማ ጉዳይ በኾነ፡፡ ነገር ግን ማንነትን የማጣራት ጥያቄ እንጂ የተነሣው የሕግ ጥያቄ አይደለም፡፡ ከቅዱስ ሲኖዶስ በወጣው ደብዳቤ ላይ "ማኅበራት" የሚል ቃል ስላለ ብቻ ሕጋዊ እና ሕገ ወጥ ማኅበራትን በጅምላ እና በአንድ መነጽር መመልከት አይቻልም፡፡
አይጥ በበላ ዳዋ ተመታ የሚባለው ብኂል ተፈጻሚ የኾነ ይመስላል፡፡ "ማኅበራት" የሚለው ቃል ስላለ ብቻ ማኅበረ ቅዱሳን እንዴት አብሮ ተጨፍልቆ ሊተረጎም ይችላል? ማኅበረ ቅዱሳን ሕገ ወጥ በሚለው ዘርፍ ፈጽሞ ሊፈረጅ የማይችል እንደኾነ ለመናገር ለእኔ ጥያቄው ከተነሣባት ቅጽበት አልፎ ሊውል ሊያድር መቻሉ አነጋጋሪ ኾኖብኛል፡፡ እንዲህ ለማለት መሠረታዊ ምክንያቶች አሉኝና፡፡
አንደኛ፡- ማኅበረ ቅዱሳን በቅዱስ ሲኖዶስ ደረጃ የተዋቀረ ሕጋዊ አካል ስለኾነ፡፡
ማኅበረ ቅዱሳን በአንድ መምሪያ ወይም ሀገረ ስብከት ወይንም በጠቅላይ ቤተ ክህነት ደረጃ ሳይኾን የቤተ ክርስቲያን ላዕላዊ መዋቅር በኾነው በቅዱስ ሲኖዶስ ውሣኔ የተቋቋመ የአገልግሎት ማኅበር ነው፡፡ በዚህ ደረጃ የተዋቀሩት የቤተ ክርስቲያን መዋቅሮች በጣት የሚቆጠሩ ናቸው፡፡ ከእነዚህም መካከል ልማትና ተራድኦ ኮሚሽንን፣ የኪራይ ቤቶችን አስተዳደር፣ የሕጻናትና ቤተ ሰብ መምሪያን፣ የትንሣኤ ዘጉባኤ ማተሚያ ድርጅትን መጥቀስ ይቻላል፡፡ ማኅበረ ቅዱሳንም ከ፲፱፻፹፮ ዓ.ም. ጀምሮ በቤተ ክርስቲያን ዕውቅና ተሰጥቶት በሕጋዊነት ተዋቅሮ እየሠራ ያለ ማኅበር ነው፡፡ ከዚያም በፊት ቢኾን በተለይ ከ፲፱፻፹፬ ዓ.ም. ጀምሮ በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ እና በአበው ሊቃነ ጳጳሳት እስከ ፓትርያርኩ ድረስ ዕውቅና አግኝቶ አገልግሎት ሲሰጥ የነበረ መኾኑ ሊዘነጋ አይችልም፡፡
ይልቁንም ብዙ ጥናት ሲደረግበት ከቆየ በኋላ የማኅበሩ ደንብ በ፲፱፻፺፬ ዓ.ም. በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ጸድቆ በሥራ ላይ የተሰየመ አንድ የእናት ቤተ ክርስቲያን ደጋፊ አካል ኾኖ በመሥራት ላይ ይገኛል፡፡ በየትኛውም መሥፈርት ይህንን አካል ሕገወጥ የሚል ያልተገባ ቃል መግለጥ አመክንዮአዊ አይኾንም፡፡ ከፍ አድርገን እንመልከተው ከተባለ ማኅበሩን በዚህ ጎራ መሰየም ቅዱስ ሲኖዶስን ከመዝለፍ ጋር ይመሳሰላል፡፡
ስለኾነም የተጻፈው ደብዳቤ በምንም ምክንያት ማኅበረ ቅዱሳንን እንደማይመለከት መናገር በልብ የታሰብን በአንደበት እስከመናገር ድረስ ካለው የጊዜ ክፍተት በላይ ሊውል ሊያድር የሚችል አልነበረም፡፡ ጅብን ሲወጉ አህያን ይጠጉ ዓይነት እንዳይኾን ስጋት አለኝ፡፡ ሕገወጥ የኾኑትን ለመቅጣት ሕጋዊውን ማስደንበር ለምን አስፈለገ?
ሁለተኛ፡- ማኅበረ ቅዱሳን ከተፈቀደለት መስመር አፈንግጦ ከኾነ በውስጥ ደብዳቤ ሊገሰጽ የሚገባው በመኾኑ
ማኅበሩ ከተመሠረተበት ጊዜ አንስቶ እጅግ በርካታ የኾኑ የደብዳቤ ልውውጦች ከፓትርያርክ ጽ/ቤት እስከ አኅጉረ ስብከት ብሎም እስከ ወረዳ ቤተ ክህነት ሲደረጉ ኖረዋል፡፡ አሁንም በዚያው መልክ ቀጥሎ ይገኛል፡፡ ሲያለማ እንደተመሰገነው ሁሉ ሲያጠፋም ሊገሠጽ ይገባዋል፡፡ ስለኾነም ጥፋት በፈጸመባቸው ጊዜያት ተግሣጽ ሲሰጠው የኖረ ማኅበር ነው፡፡ ሳያስፈቅድ የቴሌቪዥን መርሐግብር ሲያካሂድ ከተገኘም እንደ አንድ የቤተ ክርስቲያን አካል በሚመለከተው ክፍል ተገቢው እርምጃ ሊወሰድበት የሚችል አካል ነው፡፡ ስለዚህ ለራስ አካል በሦስተኛ ወገን በኩል ትእዛዝ ይተላለፋል ብሎ ማሰብ አይቻልም፡፡ እናም ደብዳቤው ማኅበሩን በጭራሽ አይመለከተውም ለማለት አናመነታም፡፡
አሁንም በውስጥ ደብዳቤ ለጊዜው ማጣራት አስፈላጊ ስለኾነ ሥርጭቱን አቁም ቢባል በጸጋ ተቀብሎ ለማስተናገድ ችግር የሌለበት ማኅበር ነው፡፡ ነገር ግን ጉዳዩ ማኅበሩን የማይመለከት ስለኾነ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ይኽኛውን መንገድ እንዳልመረጠ መረዳት ይቻላል፡፡ ሌሎቹ ግን ምንም ዓይነት ሕጋዊ የሚባል ግንኙነት ከጠቅላይ ቤተ ክህነት ጋር ስለሌላቸው የተጻፈው ደብዳቤ በቀጥታ እነርሱን እንደሚመለከት አያወላዳም፡፡ ጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ከእነ መፈጠራቸውም ምንም ዓይነት ሕጋዊ መሠረት እንዳላገኘባቸው ግልጽ ነው፡፡ ነገር ግን በጉልበት ወይንም በማን አለብኝነት የቅደስት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ስም ይጠቀማሉ፡፡ እነርሱን በተመለከተ ውሣኔው ከማርፈዱ በስተቀር ምንም እንከን የለበትም፡፡
ዘገባ እያቀረበ እና እያስጸደቀ፣ ሂሳቡን እያስመረመረ፣ ትእዛዝ እና መመሪያ እየተቀበለ የእናት ቤተ ክርስቲያንን መዋቅራዊ ሰንሰለት ጠብቆ እየሠራ የሚገኝን ማኅበር አድራሻ ከሌላቸው አካላት ጋር መፈረጅ እንዳይመስልም ደጋግሞ ማሰብ ያስፈልጋል፡፡ በየአጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤው በየአሕጉረ ስብከቱ ዘገባ ተካትቶ ሥራው የሚነገርለትን ማኅበር ከእነ እገሌ ጋር ጨፍልቆ ማሰብ አይመጥነውም፡፡
ሦስተኛ፡- ማኅበሩ ትምህርተ ወንጌልን በተለያዩ ዘርፎች እንዲያስተላልፍ የተፈቀደለት መኾኑ
ቀደም ሲል በጠቀስነው በ፲፱፻፺፬ ዓ.ም. በጸደቀው የማኅበረ ቅዱሳን መተዳደሪያ ደንብ ላይ በአንቀጽ ፬ ላይ የማኅበሩ ዓላማና ተግባር በሚለው ርእስ ሥር በቁጥር ፮ ላይ ". . . ትምህርተ ወንጌል በተለያዩ ዘዴዎች በመጽሔቶች፣ በጋዜጦች፣ በበራሪ ጽሑፎች፣ በካሴቶች፣ በኢንተርኔት፣ በኤሌክትሮኒክስ መገናኛ እና በመሳሰሉት እንዲስፋፋ ማድረግ . . ." የሚል ይገኛል፡፡
ከጠቅላይ ቤተ ክህነቱም ኾነ ከቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት የወጡት ደብዳቤዎች በቀጥታ የሚመለከቱት ፈቃድ ያልተሰጣቸውን ነገር ግን በቤተ ክርስቲያን ስም የሚነግዱትን መኾኑ ግልጽ ሲኾን ማኅበረ ቅዱሳን ግን በማያሻማ ሁኔታ በማንኛውም የዘመኑ ጥበብ (ቴክኖሎጂ) በሚፈቅደው መንገድ ትምህርተ ወንጌልን ለማሠራጨት ፈቃድ የተሰጠው ገና በማለዳ ነው፡፡ በዚሁም መሠረት ላለፉት ፳፫ ዓመታት በተጠቀሱት መንገዶች ሁሉ ቃለ ወንጌልን ሲያሠራጭ ቆይቷል፡፡ አሁን ምንም የተለየ ሁኔታ አልተፈጠረም፡፡ ስለዚህ ደብዳቤው በየትኛውም መስፈርት ማኅበረ ቅዱሳንን ሊያካትት እንደማይችል እርግጠኛ መኾን ይገባል፡፡
በደንቡ ላይ በግልጽ እንደተመለከተው በኤሌክትሮኒክስ መገናኛ ትምህርተ ወንጌልን ለማስፋፋት ተፈቅዶለታል፡፡ ኤሌክትሮኒክስ መገናኛ የሚለው ብዙ ዘርፎችን የሚያካትት ሲኾን ከእነዚህም መካከል አንደኛው የቴሌቪዥን ሥርጭት ይገኝበታል፡፡ ስለዚህ የፈቃድን ጉዳይ በማኅበሩ ላይ ማንሣት ተገቢ አይኾንም፡፡
ይሁን እንጂ ደብዳቤው የተጻፈለት አካል ጥያቄውን ማንሣቱ ስህተት አለበት ብሎ ማሰብ አይቻልም፡፡ ጠቅላይ ቤተ ክህነቱ እነዚህን ከላይ የተነሡትን መሠረታዊ ነጥቦች ግንዛቤ ውስጥ አስገብቶ ፈጣን ምላሽ ሊሰጥ ይገባዋል፡፡ ጀምበር እስክትጠልቅ የሚያቆይ ምንም ዓይነት ብዥታ ወይንም ግርታ ሊፈጠርበት በማይችለው ጉዳይ ላይ ውሎ ማደሩ በጥንቃቄ ሊታይ የሚገባው ነውና አሁንም ሌሎች ተጨማሪ ቀናት እንዳይባክኑ ቢደረግ ሠናይ ነው፡፡
የገበያ ግርግር ለሌባ ያመቻል እንዲሉ በዚህች አጋጣሚ ሰርጎ ለመግባት በር የሚከፈትላቸው አካላት መኖራቸው ሌላው አሳሳቢ ጉዳይ ነው፡፡ ክፍተቱን እንደ በጎ አጋጣሚ በመውሰድ በቴሌቪዥን ጣቢያው ለመጠቀም በርካታ ተቃራኒ አካላት ማሰፍሰፋቸው እየተሰማ ይገኛል፡፡ ከእነዚህም ውስጥ ዋነኛው የቤተ ክርስቲያን ጠላት ተብሎ የተወገዘው "የከሣቴ ብርሃን" ሐራጥቃ ተሐድሶ ይገኝበታል፡፡ ከእርሱም ባሻገር ከነባሮቹ በቤተ ክርስቲያን ነጋዴዎችም በኩል ሌላ የፍቀዱልን ውስጣዊ ግፊት እየተደረገ ይገኛል፡፡ ስለኾነም፡-
፩. የማጣራቱ ጉዳይ ቶሎ እልባት አለማግኘቱ ዕድሉን ለሌሎች በሰፊው መክፈት ይኾናልና በፍጥነት ውሣኔ ቢሰጠው እና ማኅበሩ ወደጀመረው አገልግሎት እንዲቀጥል ቢደረግ፡፡
፪. ግርግሩን ምክንያት በማድረግ በደብዳቤው የታገዱት ሁለት አካላት ፈቃድ እንዲሰጣቸው አንዳንድ ሰዎች ሀሳብ እያቀረቡ እንደኾነ መሰማቱ ከፍተኛ ተቃውሞ እያስነሳ ይገኛል፡፡ ለማኅበረ ቅዱሳን በመፍቀድ ሰበብ ሌሎችም የዚህ ጽዋ ተቃማሽ እንዲኾኑ ለማድረግ ያደቡ ሰዎች እንዳሉ ግልጽ ነው፡፡ ይኽ ከተደረገ ግን ማጣፊያ የሚያጥረው ስህተት ይኾናል፡፡ ስለዚህ ደግመው ደጋግመው አባቶች እዲያስቡበት ያስፈልጋል፡፡ እንዲህ ከሚደረግ የማኅበረ ቅዱሳንም አገልግሎት ቢዘገይ እመርጣለሁ፡፡ ምክንያቱም ለእነዚያ ሰዎች ሙሉ ዕውቅና ከመስጠት የማይተናነስ ድርጊት ስለሚኾን፡፡ ብዙ ጊዜ አንድ ጊዜ በኾነች ሰበዝ ልክ የተሰፋችን አለላ ነጥሎ ለማውጣት ስንቸገር ዐውቃለሁና፡፡
፫. በተጻፉት ደብዳቤዎች ውስጥ "ሕገ-ወጥ" የሚለው ቃል በተደጋጋሚ ሲጠቀስ እንመለከታለን፡፡ ቅዱስ ሲኖዶስም ኾነ ጠቅላይ ቤተ ክህነት እነዚህን ደብዳቤዎች ሲጽፉ ሕገወጥ የኾኑ አካላት መኖራቸውን ያረጋግጣል፡፡ እነዚህ ሕገወጥ እየተባሉ የተጠሩት አካላት አሁን ተመልሰው ሕጋዊ የሚኾኑበት መንገድ ሊኖር አይችልም፡፡ ጥንትም ሕገወጥ ተብለዋልና፡፡ ማኅበራት የሚለው ቃልም የተጠቀሰው ከእነርሱ መካካል ማኅበር መሥርተናል እያሉ የሚናገሩ በመኖራቸው የተጠቀሰ ቃል እንጂ ነው፡፡

2015 ኖቬምበር 29, እሑድ

“በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የጽሑፍ ቅርስ ላይ ከአለኝ ትዝብት”


የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን

ኒው ዮርክ ከተማ

(የተራድኦ ድግስ ምሽት፥ ኅዳር  ቀን ፳፻፯ . = November 14, 2015) 


ጌታቸው ኃይሌ

ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን እንድታገለግሉ የተመረጣችሁ የተከበራችሁ ካህናትናዲያቆኖት፥ የመድኃኔ ዓለም አባላት እንድትሆኑ የሐዋርያትን ጥሪ ያከበራችሁየኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ምእመናን እኅቶቼና ወንድሞቼ፥ በዚህ የበጎአድራጎት ምሽት ላይ ተገኝቼ ለሥጋ ጣፋጩን የኢትዮጵያ ምግብ በስመጥር ጠጅአያወራረድኩ እንድመገብና ስለመንፈስ አርኪው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የሥነ ጽሑፍ ቅርስ ያሉኝን አንዳንድ ትዝብቶች እንዳጫውታችሁ ስለጋበዛችሁኝ ከልብ አመሰግናለሁ።

እኛ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ምእመናን የትልቅ ታሪክ ችቦ ተሸካሞችነን። ችቦውን መሸከም መስቀለ ሞቱን የመሸከም ያህል ይከብዳል፤ ግን የኩሩውማንነት መታወቂያችን ስለሆነ ከባዱን ሸክም በደስታና በጸጋ እንሸከመዋለን።ስለችቦውና ስለ አቀጣጣዮቹ ተናገር ስላሉኝ ተደስቻለሁ። ቅዱስ ዳዊት “ተፈሣሕኩእስመ ይቤሉኒ ቤተ እግዚአብሔር ነሐውር” (ወደ እግዚአብሔር ቤት እንሂድ ስላሉኝተደስቻለሁባለው አነጋገር ስለተጠቀምኩ መንፈሱ እንደማይወቅሰኝ እለምነዋለሁ።

ትልቁን ታሪካችንን በመመዝገብ የትልቅ ሕዝብ ቀጣዮች መሆናችንን የነገሩን የቤተክርስቲያን ሊቃውንት ናቸው። ባለውለታዎች ስለሆኑ፥  እናመስግናቸው፤ ቅዱሳንስለሆኑ፥  እንዲጸልዩልን እንለምናቸው።
“ሊቃውንት አባቶቻችን ምን ምን መዘገቡልን? የሚለውን ጥያቄ ለመመለስ ጥናቱእንደቀጠለ ነው። በዚህ ጥናት ላይ የምዕራባውያን ምሁራን ተሳትፎ ከፍ ያለ ቦታይዟል፤ አድናቆትም አለኝ። የምዕራባውያን ምሁራን በምርምራቸው የሚያደርጉትንስሕተት ሁሉ ከክፋታቸው እንደመነጨ አድርጌ አላየውም። ለምሳሌ በኪዳነ ወልድክፍሌ ስም የሚታወቀውን መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገበ ቃላት ሐዲስየሚመጥን የግዕዝ መዝገበ ቃላት በኢትዮጵያ አልተጻፈም። የዚህ ድንቅ መጽሐፍመሠረት ጀርመናዊው ዲልማን በላቲን ቋንቋ ያዘጋጀው የግዕዝ መዝገበ ቃላት ነው።እኔም ማስረጂያ ይዤ እንዲያርሙ የምጠይቃቸውን እርማት፥ በማልቀበለውምክንያት እምቢ ያሉበትን ጊዜ አላጋጠመኝም።

የምዕራባውያን ምሁራን የግዕዝን ምንጮች ከሚመረምሩበት ምክንያት አንዱ፥በዓለም ላይ የጠፉ የጥንት የክርስትና ሃይማኖት ምንጮች ኢትዮጵያ ገዳማት ውስጥይገኙ እንደሆነ ለማወቅ ነው። ክርስትና የዛሬውን መልክ እስኪይዝ ብዙ እንቅፋቶችንአልፏል። እንቅፋቶቹን ከፈጠሩት ምክንያቶች አንዱ ብዙ የክርስትናን ታሪክ ዘጋቢዎችመነሣት ነው። እዚህ ላይ በእኛ ዘንድ የተፈጸመውንና የታመነውን የሥራውን ዜናበሥርዐት ሊጽፉ የጀመሩ ብዙዎች ናቸው ያለውን የቅዱስ ሉቃስን ምስክርነትመጥቀስ ይቻላል። የጥንቶቹ ሊቃውንት ከውዝግብ ለመውጣት ሲሉ ጥቂቶቹንመጻሕፍት መርጠው የቤተ ክርስቲያን ሕጋዊ መጻሕፍት አድርገው አወዛጋቢ ነገርያለባቸውን ሌሎቹን ኮነኗቸው፤ አጠፏቸውም። ዛሬ የሃይማኖት ተመራማሪዎችእነዚህ የተኮነኑ መጻሕፍትና በሌላ ምክንያት የጠፉ ስለክርስትና ታሪክ የሚነግሩን ነገርይኖራል በማለት ይፈልጓቸዋል።

በመጠኑም ቢሆን ተገኝተዋል። በጣም የታወቁትን ልተውና አንድ አሜሪካዊ ተማሪበቅርብ ቀን ስላገኘው የጥንታዊ ድርሰት ብጣሽ (fragment) ልናገር። ሙሴናየፈርዖን ጠንቋዮች ታምራት በመሥራት ይወዳደሩ እንደነበረ እናስታውሳለን። አንድያልታወቀ ደራሲው ስለፈርዖን ጠንቋዮች የደረሰው ጥንታዊ ድርሰት ኖሯል። መኖሩየታወቀው የድርሰቱ አንድ ብጣሽ በግሪክኛው ተገኝቶ ነው። ይህ ተማሪ ያገኘውየግዕዝ ብጣሽ ብራና ግሪክኛው ውስጥ ያለውን የሚመሰክርና የጐደለውን የሚያሟላነው። ተማሪው ከማግኘቱ በፊት እንዲህ ያለ ድርሰት በግዕዝ መኖሩን ማንምአያውቅም ነበር። ይቺ ብጣሽ የብራና ጽሑፍ መገኘት ያደረገው አስተዋጽኦ በብጣሹመጠን የሚገመት አይደለም።

በግሌ ወደ አጋጠሙኝ ሁለት ጉዳዮች ልሻገር። አባ ባሕርይ መዝሙረ ክርስቶስንሲደርሱ ከጠቀሟቸው ብዙ መጻሕፍት ውስጥ አንዱ ከሊላ ወድምና የሚባለውመጽሐፍ እንደሆነ ነግረውናል። እኔም ድርሰቶቻቸውን ስተች አንሥቼዋለሁ።መጽሐፉ በብዙ ቋንቋዎች ተተርጒሞ ሳለ በግዕዝ ስላልተገኘ፥ ሊቃውንቱየመነኵሴውን ቃል መጠራጠር ጀምረው ነበር። ግን መጽሐፉ ራሱ ባይገኝም፥ የሐይቅገዳም መጽሐፉ እንደነበረው ማስረጃ አግኝቻለሁ፤ መዝገባቸው ከመዘገባቸውመጻሕፍት አንዱ ከሊላ ወድምና ነበረ። መጽሐፉን አይተውት ይሁን ወይም ስሙንከመዝገብ ላይ አግኝተውት ይሁን ባይታወቅም፥ ሊቀ ጠበብት አክሊለ ብርሃንከአዘጋጁት የመጻሕፍት መዝገብ ውስጥ አግብተውታል።


ሁለተኛው፥ ዮሴፍ ወአስኔት የሚባለውን መጽሐፍ የሚመለከት ነው። ይህምመጽሐፍ በብዙ ቋንቋዎች ተተርጕሞ ሲገኝ በግዕዝ አልተገኘም። ግን አባ ጊዮርጊስዘጋስጫ መጽሐፈ ምስጢር በሚባለው መጽሐፋቸው ውስጥ እመቤታችንን ንህብዘአስኔት (የአስኔት ንብብለዋታል። አስኔት ንብ እንደነበራት የሚነግረን ምንጭዮሴፍ ወአስኔት ብቻ ስለሆነ ደራሲው አባ ጊዮርጊስ መጽሐፉ እንደነበራቸው--ኢትዮጵያ እንደነበራት--ታምኖበታል። እዚህም ላይ ትንሽ አስተዋፅኦ አድርጌያለሁ።

ከእኛ ሊቃውንትም ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ሥላሴና ሊቀ ጠበብት አክሊለ ብርሃንምን ምን መጻሕፍት እንዳሉን በዝርዝር ጽፈዋል። ግን በቂ አይደለም። ምርምሩይቀጥላል። ምኞቴ በዚህ በተቀደሰ ተግባር ብዙ ወጣት ኢትዮጵያውያን እንዲሰማሩነው። አባቶቻችንን የማደንቀው ለግዕዝ ያንን ሁሉ የሃይማኖት መጽሐፍ የመቀበያችሎታ ማስታጠቃቸው ነው። ይህ የሚያመለክተው ግዕዝ ከአክሱም ዘመነ መንግሥትበፊት ዳብሮ እንደነበረ ነው። ለምሳሌ ግዕዝ ተቆጣ ለማለት ከአራት የማያንሱቃላት እንዳሉት በአጋጣሚ አይቻለሁ፤ መአከ (ተምእከ) መጐጸ(አመጐጸ) ተምዐ (ተምዕዐ) ተቈጥዐ

አማርኛ የሌለው አንዳንድ ቃላትም አጋጥመውኛል፤ ለምሳሌ፥ ሕልበት(nostril)ምንሀብ (factory). አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ ሕልበት መተርጐሚያ አማርኛቢያጡ፥ የአፍንጫ ጉንጭ አሉት።

የግዕዝን ችሎታ ብናውቅ ኖሮ፥ bank የሚለው የእንግሊዝኛ ቃል አማርኛ ውስጥአይገባም ነበር። ባንክ በመሠረቱ የገንዘብ መለዋወጫ ጠረጴዛ (bench)ነው።የሉቃስን ወንጌል ስናነብ ምዕራፍ ፲፱ ላይ ጌታችን የሰጠን አንድ ምሳሌ እናገኛለን።እንደምሳሌው፥ አንድ ጌታ ከአሽከሮቹ ለዓሥሩ ነግደው እንዲያተርፉለት ዓሥርምናናት ከፋፍሎ ሰጥቷቸው ነበር። በመጨረሻ ሁሉም ገንዘቡን ከነትርፉ ለጌታቸውሲያስረክቡ፥ አንዱ ብቻ የወሰደውን ሳይነግድበት ሳያተርፍበት እንዳለ ከትቶ እንዳለለጌታው መልሶ ሰጠው። ጌታው አዝኖና ተቆጥቶ እንዲህ አለው፤

“ወለምንት ኢያግባእከ ወርቅየ ውስተ ማእድ”
([ላለመነገድህ ምክንያት ካለህ] ታዲያ ገንዘቤን ለምን ከማእድ አላስገባህም?”
ምንጩ ግሪክኛው የሚለውም “ትራፔዛ” (ጠረጴዛነው። ታዲያ የአማርኛው ትርጕምከላይ እንዳመለከትኩት መሆን ሲገባው፥ የመጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር ትርጉም “ባንክ”፥የኦርቶዶክሶቹ “ለዋጮች” ይላል። ግን ቀደም ብሎ “ማእድ” እንዳለ ከግዕዝ ወደአማርኛ ቢተላለፍ ኖሮ “ባንክ” የሚለውን የእንግሊዝኛ ቃል ምንም ሳይጕድልብንልናስቀረው እንችል ነበር።

የዮሐንስ ወንጌልን ሳነብና  ምዕ 19 . 24 ላይ ስደርስ ደግሞ፥ ስለ ግዕዝ የቃላትብልጽግናና ስለአባቶች ጥንቃቄ የገረመኝና እኛን ልጆቻቸውን የሚወቅስ ነገርአጋጠመኝ፤ ጥቅሱን እንዳለ ልጥቀሰው፤
 
ወሐራሰ ሶበ ሰቀልዎ ለኢየሱስ ነሥኡ አልባሲሁ ወረሰይዎ አርባዕተ ክፍለ ለአሐዱሐራ ክፍለ። ወክዳኖሂ እልታኀ ዘአልቦ ርፍአት ዘእምላዕሉ እኑም ኵለንታሁ።ወተባሀሉ በበይናቲሆሙ ኢንግምድ ወኢንስጥጥ አላ ንትፋሰስ ለዘረከቦ ይርከቦ። ከመይብጻሕ ቃለ መጽሐፍ ዘይቤ። ተካፈሉ አልባስየ ለርእሶሙ ወተዓፀው ዲበ ዐራዝየ።

ወታደሮቹ ኢየሱስን ከሰቀሉት በኋላ፥ ልብሱን ወስደው ለእያንዳንዱ ወታደር አንድ ክፍል እንዲደርስ አራት ቦታ ከፈሉት። መርፌ ስላልነካው ከላይ እስከታች አንድ ወጥ ሆኖ ስለተሠራው ስለ ፈርጅ ቀሚሱ ግን እርስ በርሳቸው (እንዲህ) ተባባሉ፥ “ዕጣ እንጣጣልና ለደረሰው ይድረሰው እንጂ አንቅደደው”። ይህም፥ “ልብሶቼን ለራሳቸው ተከፋፈሉት፤ በቀሚሴም ላይ ዕጣ ተጣጣሉ” ያለው የመጽሐፍ ቃል ይፈጸም ዘንድ ነው።)
እንግሊዝኛውም እንደ አማርኛው ከሁለቱም ቦታ “ዕጣ ተጣጣሉ”(cast lotsነውየሚለው።
. . . So they said to one another, Let us not tear it, but cast lots for it to see who will get it. This was to fulfill what the scripture says, They divided my clothes among themselves, and for my clothing they cast lots.

በግዕዝ ግን አነጋገሩ የተገለጠው በሁለት የተለያዩ ሐረጎች መሆኑን ልብ እንበል፤ ተፋሰሱ  ተዐፀዉ ለምን እንዲህ ሆነ ብየ የግሪኩን ምንጭ ባየው፥ እውነትምሁለቱ ሐረጎች በግሪክኛውም የተለያዩ ናቸው፡ lachomen እና ebalon kleeron


* * * * * * * *
ባሁኑ ሰዓት ጥሪየ አድርጌ የያዝኩት አባቶቻችን ከውጪው ዓለም ምን ተረጐሙልን፥እነሱስ በተረጐሙት ላይ ምን አከሉበት የሚሉትን ሁለቱን ጥያቄዎች መመለስን ነው።አምሳያቸው እውጪ አገር ካለ ከውጪ የተተረጎሙ ናቸው ማለት አያስቸግርም።ደንቃራ የሆነብኝ አንዳንዶቹን የግዕዝ መጻሕፍት ከምዕራቡ ዓለምና ከመካከለኛውምሥራቅ ጠፍተው ነው እንጂ፣ ትርጕም ናቸው የሚለው አነጋገር ነው። እርግጥከሌላው ዘንድ ጠፍተው እኛ ዘንድ የተገኙ አሉ። ይኸም ቢሆን አባቶቻችንና ቤተክርስቲያናችንን የሚያስመሰግን ነው።

ቢሆንም እኛ ተቀባዮች ብቻ ባንሆን እንመርጣለን፤ ለነገሩ ተቀባዮች ብቻምአይደለንም። ይኸንንም ለማሳየት ለዛሬው ንግግሬ ሁላችሁም በምታውቁትበመጽሐፈ ቅዳሴያችን ላይ አተኩራለሁ። 

የዶክተር ገብረ ጻድቅ ደገፉና የኔ መምህር ቄስ ማርቆስ ዳውድ የመጽሐፈ ቅዳሴውንእንግሊዝኛ ሲያሳትሙ፥ እመቅድሙ ውስጥ እንዲህ ብለው ጽፈዋል፤
 
It is said by the Ethiopian Church authorities that they received their liturgy of fourteen Anaphoras from the Church of Egypt. The Church of Egypt confirms this but has, unfortunately, lost most of the fourteen.
 
(በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ባለሥልጣኖች ዘንድ ዓሥራ አራቱን የቅዳሴ መጻሕፍታቸውን ከግብፅ ቤተ ክርስቲያን እንደወሰዱ ይነገራል። የግብፅ ቤተ ክርስቲያን ይኸንን ታረጋግጣለች። ግን መጥፎ ዕድል ሆኖ ከዓሥራ አራቶቹ አብዛኛዎቹ ጠፍተውባታል።
 የግብፅ ቤተ ክርስቲያን የጠፉባት የቅዳሴ መጻሕፍት ቍጥር የሚታወቀው ኢትዮጵያውስጥ ባሉት መጻሕፍት ቍጥር መሆኑ ነው። እንዲህ ከሆነ፥ ከዓሥራ አራት ሊበልጡነው። ምክንያቱም ቄሱ አልሰሙም እንጂ፥ ቅዳሴዎቹ ወደኻያ ይጠጋሉ። መምህሬ ቄስማርቆስ ዳውድ ይህን መቅድም ሲጽፉና ትርጕሙን ሲያሳትሙ እያወቁ ሁለት በደልፈጽመዋል፤ (1) “የግብፅ ቤተ ክርስቲያን ይኸንን ታረጋግጣለች” ያሉት ማስረጃሳይኖራቸው ነው። (2) መጽሐፈ ቅዳሴውን የተረጐመላቸው አብሮ አደግ ወዳጄናጓደኛየ ዶክተር ገብረ ጻድቅ ደገፉ ነው። ግን እኝህ መንፈሳዊ አባትና መምህር ይኸንንሐቅ ጨቁነውታል፤ የገብረ ጻድቅን ስም ለምስጋና እንኳን አላነሡትም።

ከታተመው መጽሐፈ ቅዳሴ ውስጥ ያሉት የቅዳሴ ጸሎቶች (አኰቴተ ቍርባንዓሥራአራት የሆኑት ለኅትመት የተመረጠው የብራና ቅጂ ውስጥ ያሉት ዓሥራ አራትስለነበሩ ነው። ካህናቱ እንደምታስታውሱት፥ ቅዳሴ ጎርጎርዮስ (ነአኵቶ ለገባሬሠናያት--ነአኵተከ እግዚኦን አይደለምየሚያነሣው ሊቀ ጳጳሱን አባ ዮሐንስን(፲፮ኛው 1676-1718) እና ጳጳሱን አባ ሲኖዳን (1671-1693) ነው። የእትሙምንጭ የተቀዳው በነሱ ዘመን 1676 እና 1693 መካከል በነበረው ዘመን ነውማለት ነው።

ያደረግሁት ምርምር ጥሩ ዕድል ሆኖ ከዓሥራ አራቶቹ አብዛኛዎቹ ከግብፅ ቤተክርስቲያን የመጡ ሳይሆኑ፥ የአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ድርሰቶች መሆናቸውንአረጋግጦልኛል። አባ ጊዮርጊስ በአፄ ዳዊትና በአፄ ዘርአ ያዕቆብ ዘመን የኖሩ ብዙመጻሕፍት የደረሱ ታላቅ የቤተ ክርስቲያን ሊቅ ናቸው። ከድርሰቶቻቸው ውስጥኆኅተ ብርሃን፣ አርጋኖነ ውዳሴ (= አርጋኖነ ድንግል) ውዳሴ መስቀል፤ መጽሐፈብርሃን፣ ጸሎተ ፈትቶ፣ ፍካሬ ሃይማኖት፣ መጽሐፈ ምስጢር የሚባሉ መጻሕፍትይገኛሉ።

ደራሲያቸው ያልተረጋገጠውን አኰቴተ ቁርባኖች የመረመርኩትና የጥናቴን ውጤትለኅትመት የላክሁት እነዚህ መጻሕፍት የተጻፉበትን ስልት መሣሪያ በማድረግ ነው።ምርምሬን የጀመርኩት ውበቱን ምዕራባውያን በመሰከሩለት ድርሰታቸው አርጋኖነውዳሴ ነው። ግን መጀመሪያ አርጋኖነ ውዳሴ የአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ እንጂ፥እንደሚታመንበት የአርመናዊው ጊዮርጊስ (Giorgis the Armenian)እንዳይደለ ማስመስከር ነበረብኝ። ያስመሰከርኩበት ጥናት የምዕራባውያን ሊቃውንትቀንድ የሆነ ሊቅ፥ The erroneous dating of the Arganonä Wəddase . . . as well as its false attribution to un unknown Giorgis the Armenian have been conclusively refuted ሲል ፍርዱን መዝግቧል።

ይኸ በራሱ አንድ አስደሳች የድካም ውጤት ነው። እርግጥ በኛ ዘንድ አርጋኖነ ውዳሴየአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ መሆኑን የሚጠራጠር የለም። ግን የኢትዮጵያ ታሪክ በምዕራቡዓለም በሰፊው ስለሚጻፍ፥ ልጆቻችንም እነሱ ዘንድ ስለሚማሩ፥ ታሪካችንንበተገኘበት ቦታና ጊዜ ሁሉ ማስተካከል ግዴታችን ነው። ከቅዳሴዎቹ አብዛኞቹ የአባጊዮርጊስ ዘጋስጫ መሆናቸውን ለማሳየት የምጥረውም ከግብፅ ቤተ ክርስቲያን የመጡናቸው ተብሎ በሀገራችን ሳይቀር ተቀባይነት ያገኘውን የተሳሳተ እምነት ለማስቀረትነው። አርጋኖነ ውዳሴ የአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ መሆኑ ከተረጋገጠ የአጻጻፋቸው ስልትምን እንደሚመስል ላሳይ። በድርሰቶቻቸው ላይ ሁሉ በተለይ ከዚህ በታች ያሉትባሕርዮች ጎልተው ይታያሉ፤
1. ይዞታቸው እንደ መጽሐፈ ምስጢር ነገረ መለኮት ማስተማሪያ ናቸው፤
2. በጀመሩበት ቃል ብዙ አረፍተ ነገሮች ያከታትሉበታል፤
3. በአረፍተ ነገሩ መጀመሪያ ሐረግ ላይ ያለውን ሐሳብ በሁለተኛው ሐረግያጠነክሩታ፤
4. በአረፍተ ነገሩ መጀመሪያ ሐረግ ላይ ያለውን ሐሳብ በሁለተኛው ሐረግያፈርሱታል፤
5. አረፍተ ነገሮቹ ቤት የሚመቱ የማይመቱም ቅኔዎች ናቸው፤
6. ካለው ግስ ላይ አዳዲስ ቃላት ይፈጥራሉ፤
7. ለኛ ባልታወቁ የውጪ ቃላት ይጠቀማሉ፤

እነዚህ የአጻጻፍ ባሕርዮች በብዙዎቹ ቅዳሴዎች ላይ ይታያሉ።
ቅዳሴ በመሠረቱ ከጸሎተ ሃይማኖት አልፎ ነገረ መለኮት መተቻ አይደለም። ብዙዎቹቅዳሴዎቻችን ግን እንደ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ድርሰቶች እንደ መጽሐፈ ምስጢር እናእንደ ፍካሬ መለኮት መለኮትን በሰፊው ይተቻሉ። ሁሉንም የአባ ጊዮርጊስን የአጻጻፍባሕርዮች ለማሳየት ከሁሉም ምሳሌ መስጠት መጽሐፈ ቅዳሴውን መገልበጥይሆናል። ግዕዝ የማያውቀውንም ያሰለቸዋል። ሆኖም ከዚህ በታች ያሉትን ብቻእንመልከት፤

ከአርጋኖነ ውዳሴ ለምሳሌ
ኪያኪ፡ ረከብኩ፡ ምጒያየ፡ እሙስና፡ (ከብልሸት መሸሻ አንቺን አገኘሁ ፡)
ኪያኪ፡ ረከብኩ፡ ምጒያየ፡ እምአፈ፡ አናብስት፡ (ከአንበሶች አፍ መሸሻ አንቺን አገኘሁ፡)
ኪያኪ፡ ረከብኩ፡ ምጒያየ፡ እምአፈ፡ ተኵላተ፡ ዐረብ፡ (ከዐረብ ተኵላ አፍ መሸሻ አንቺን አገኘሁ፡)
ኪያኪ፡ ረከብኩ፡ ምጒያየ፡ እምቃለ፡ ዘይጽዕል፡ (ከተሳዳቢ ቃል መሸሻ አንቺን አገኘሁ፡)
ኪያኪ፡ ረከብኩ፡ ምጒያየ፡ እምእደ፡ ኵሎሙ፡ ጸላእትየ፡ (ከጠላቶቼ ሁሉ እጅ መሸሻ አንቺን አገኘሁ፡)

(1) ከቅዳሴ ማርያም፤

አኮ ዘቦቱ ለመለኮት ክበብ . . . አላ መንክር. . .  (መለኮቱ ክበብ የለውም . . . አስደናቂ እንጂ . . .።)
አኮ ዘቦቱ ለመለኮት ግድም ወኑኅ . . . አላ ምሉእ . . . (መለኮቱ አግድሞሽና ርዝመት የለውም . . . በሁሉም ዘንድ የሞላ ነው እንጂ . . .)
አኮ ዘቦቱ ለመለኮት ምስፋሕ . . . አላ ውስተ ኵሉ . . (መለኮቱ መስፋፊያ ቦታ የለውም . . ግዛቱ በሀገሮች ሁሉ ነው እንጂ . . .)
አኮ ዘቦቱ ለመለኮት ዘበላዕሉ ጠፈር . . . አላ ጠፈር ውእቱ . . . (መለኮት በላዩ ጠፈር የለበትም . . . እሱ እራሱ ጠፈር ነው ኢንጂ . . .)

ይህ ጥቅስ (1)ነገረ መለኮት ነው፤ (2) አረፍተ ነገር በጀመረበት ቃል (አኮአረፍተነገር ይደጋግማል፤ (3) በመጀመሪያው ሐረግ ውስጥ ያለውን ሐሳብ በሁለተኛውሐረግ ያፈርሰዋል (አላ)

(2) ከቅዳሴ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ፤

አልብከ ጽንፍ ወአልብከ ማኅለቅት፤ (ዳርቻ የለህም፥ መጨረሻም የለህም፤)
አልቦ ዘረከቦ ወአልቦ ዘይረክበከ፤ . . . (ያገኘው የለም፥ የሚያገኝህም የለም . . .፤)
አልብከ ጥንት . . . (መጀመሪያ [origin] የለህም. . .፤)
ፈጠርከ፡ ኵሎ፡ እንዘ፡ ኢትትቀነይ፤ (ሳትገዛ ሁሉን ፈጠርክ፤)
ትጸውር፡ ኵሎ፡ እንዘ፡ ኢትደክም፤ (ሳትደክም ሁሉን ትሸከማለህ፤)
ትሴሲ፡ ለኵሉ፡ እንዘ፡ ኢታሐጽጽ፤ (ሳታጓድል ሁሉን ትመግባለህ፤)
ትሔሊ፡ ለኵሉ፡ እንዘ፡ ኢታረምም። (ዝም ሳትል ለሁሉ ታስባለህ፤)
ትሁብ፡ ለኵሉ፡ እንዘ፡ ኢትቀብል  (ሳትጐድል ለሁሉ ትሰጣለህ፤)
ታረዊ፡ ለኵሉ፡ እንዘ፡ ኢትነጽፍ፤ (ሳትጠግ ሁሉን ታጠጣለህ፤) 8

ትዜከር፡ ኵሎ፡ እንዘ፡ ኢትረስዕ። (ሳትረሳ ሁሉን ታስታውሳለህ፤)
ተዐቅብ፡ ኵሎ፡ እንዘ፡ ኢትነውም፤ (ሳትተኛ ሁሉን ትጠብቃለህ፤)
ትሰምዕ፡ ኵሎ፡ እንዘ፡ ኢትጸመም፤ (እምቢ ሳትል ሁሉን ትሰማለህ፤)
ተኀድግ፡ ለኵሉ፡ እንዘ፡ ኢትነሥእ። (ሳትወስድ ለሁሉ ትተዋለህ።)
በተለይ እነዚህን ቀጥሎ የጠቀስኳቸውን ሁለት ጥቅሶች ብናስተያያቸው ሁሉምከአንድ ሰው አእምሮ የወጡ ከመሆናቸው ላይ እንደርሳለን፤

(ከዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ፤
ነሥአ፡ ኅብስተ፡ በእደዊሁ፡ ቅዱሳት፡ ወብፁዓት፡ ሕፄሃ፡ ለመርዓትከ፡ ወኅዳጋቲሃ፡ለእንተ፡ ኀደጋ፡ ምኵራብ።
(በቅዱሳትና ብፁዓት እጆቹ ኅብስት አነሣ። [ኅብስቱ] ለሙሽራህ [ለምእመናንህ/ለቤተ ክርስቲያንህ] ማጫ፥ ለፈታሃት ለምኵራብ መፋቻ ሆኗል።)

(ከውዳሴ መስቀል፤
መስቀል፡ ዘኮነ፡ ሕፄሃ፡ ለመርዓትከ፡ ወኅዳጋቲሃ፡ ለእንተ፡ ደኃርካ፡ በምኵራብ።
(መስቀል የሙሽራህ [የቤተ ክርስቲያንህ] ማጫ በምኵራብ ለፈታሃት [ለሕዝበ አይሁድ] መፍቻ ሆኗል።)

(ከዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ፤
ኅሩም፡ አንተ፡ ወሀሎከ፡ አብ፡ ቅዱስ።
ኅሩም፡ አንተ፡ ወሀሎከ፡ ወልድ፡ ቅዱስ።
ኅሩም፡ አንተ፡ ወሀሎከ፡ መንፈስ፡ ቅዱስ።

(ከመጽሐፈ ምስጢር፤
ኅሩም፡ አብ፡ ዘኢያስተርኢ፡ በህላዌሁ፡ ዘእንበለ፡ ዳእሙ፡ በራእየ፡ ትንቢት፡ለነቢያቲሁ።
ኅሩም፡ ወልድ፡ ዘኢያስተርኢ፡ በመለኮቱ፡ ዘእንበለ፡ ዳእሙ፡ በትስብእቱ።
ኅሩም፡ መንፈስ፡ ቅዱስ፡ ዘኢያስተርኢ፡ በካልእ፡ ግርማሁ፡ ዘእንበለ፡ ዳእሙ፡ በንጻሬ፡ዘይትፈቀድ፡ በዘይረድኦሙ፡ ለቅዱሳን።

እነዚህ  (እና  (የተጠቀሱ ኀይለ ቃሎች ከአንድ ሰው እንጂ ከተለያዩ ሰዎችአእምሮ የወጡ አይደሉም።

(3) ከአትናቴዎስ ቅዳሴ፤

ሰብእሰ፡ እንዘ፡ ክቡር፡ ውእቱ፡ . . . (የሰው ልጅ ክቡር ሆኖ ሳለ . . . )
ሰብእሰ፡ እንዘ፡ ንጉሥ፡ ውእቱ፡ . . . (የሰው ልጅ ንጉሥ ሆኖ ሳለ . . . )
ሰብእሰ፡ እንዘ፡ ባዕል፡ ውእቱ፡ . . . (የሰው ልጅ ሀብታም ሆኖ ሳለ . . . )
ሰብእሰ፡ እንዘ፡ ልቡስ፡ ውእቱ፡ . . . (የሰው ልጅ ብርሃን የለበሰ ሆኖ ሳለ . . . )
ሰብእሰ፡ እንዘ፡ መላኪ፡ ውእቱ፡ . . . (የሰው ልጅ ገዢ ሆኖ ሳለ . . . )
ኦአዳም፡ ምንተኑ፡ ረሰይናክ፡ . . . (አዳም ሆይ ምን አደረግንህ . . .?)
ኦአዳም፡ ምንተኑ፡ ረሰይናክ፡ . . . (አዳም ሆይ ምን አደረግንህ . . .?)
ኦሔዋን፡ ምንተኑ፡ ረሰይናኪ፡. . . (ሔዋን ሆይ ምን አደረግንሽ . . .?)
ኦአዳም፡ ወሔዋን፡ እስመ፡ አኮ፡ . . . (አዳምና ሔዋን ሆይ ልንነቅፋችሁ አይቻልም. . .)
ኦአዳም፡ ወሔዋን፡ አንትሙሰ፡ . . . (አዳምና ሔዋን ሆይ እናንተስ . . .)
ኦአዳም፡ ወሔዋን፡ አንትሙሰ፡ . . . (አዳምና ሔዋን ሆይ እናንተስ . . .)
ኦ፡ ዛቲ፡ ዕለት፡ ቀዳማዊት፡ ይእቲ፡ ወአኮ፡ ደኃራዊት፡ . . .
ኦ፡ ዛቲ፡ ዕለት፡ ደኃራዊት፡ ይእቲ፡ እንተ፡ ትሰፍን፡ ለዓለም።. . .
ኦ፡ ዛቲ፡ ዕለት፡ ለአብርሃም፡ ተከሥተት፡ . . .
ኦ፡ ዛቲ፡ ዕለት፡ ለሙሴ፡ በደብረ፡ ሲና፡ ተከሥተት፡ . . .
ኦ፡ ዛቲ፡ ዕለት፡ በነቢያት፡ ተዐውቀት፡ . . .
ኦ፡ ዛቲ፡ ዕለት፡ ቅድስቱ፡ ለአብ፡ ቡርክቱ፡ ለወልድ፡ ልዕልቱ፡ መንፈስ፡ ቅዱስ።
ኦ፡ ባዕዳት፡ ዕለታት፡ እንተ፡ ባቲ፡ ተአመርክን፡ . . .
ኦ፡ ዛቲ፡ ዕለት፡ እንተ፡ ባቲ፡ ብሊት፡ ተፀርዐት፡ ወሐዳስ፡ ጸንዐት።
ኦ፡ ዛቲ፡ ዕለት፡ እንተ፡ ባቲ፡ ሙቁሓን፡ ተፈትሑ፡ ወአግብርት፡ ግዕዙ።
ኦ፡ ዛቲ፡ ዕለት፡ እንተ፡ ባቲ፡ ምዝቡር፡ ተሐንጸ፡ ወሰይጣን፡ ተኀጕለ።

(4) ቅዳሴ ኤጲፋንዮስ፤

አልቦ፡ ጥንት፡ ለህላዌሁ፤ (አነዋወሩ መጀመሪያ የለውም፤)
ወአልቦ፡ ማኅለቅት፡ ለክዋኔሁ፤ (አኳኋኑም መጨረሻ የለውም፤)
አልቦ፡ ኍልቍ፡ ለመዋዕሊሁ፤ (ዘመኑ ቍጥር የለውም፤)

ወአልቦ፡ ሐሳብ፡ ለዓመታቲሁ። (ዓመቶቹም ልክ ቍጥር የለውም፤)
ወአልቦ፡ ርስዓን፡ ለውርዛዌሁ፤ (ጕልምስናውም እርጅና የለውም፤)
ወአልቦ፡ ድካም፡ ለጽንዐ፡ ኃይሉ፤ (የኀይሉ ጥንካሬ ድካም የለውም፤)
ወአልቦ፡ ሙስና፡ ለመልክኡ፤ (መልኩም ብልሹነት የለውም፤)
ወአልቦ፡ ጽልመት፡ ለብርሃነ፡ ገጹ። (የፊቱም ብርሃን ጨለማ የለውም፤)
አልቦ፡ ድንጋግ፡ ለባሕረ፡ ጥበቡ፤ (የጥበብ ባሕሩ ዳርቻ የለውም፤)
ወአልቦ፡ መስፈርት፡ ለሣህለ፡ ትእዛዙ፤ (የትእዛዙም ምህረት ልክ የለውም፤)
አልቦ፡ ዐቅም፡ ለስፍሐ፡ መንግሥቱ፤ (የመንግሥቱ ስፋት መጠን የለውም፤)
ወአልቦ፡ ወሰን፡ ለራኅበ፡ ምኵናኑ። (የግዛቱም ስፋት ወሰን የለውም፤)

ከዚያ ይህ ይቀጥላል፤
ሥውር፡ ውእቱ፡ (ሥውር ነው)
ወምጡቅ፡ ውእቱ፡ (ምጡቅ ነው)
ነዋኅ፡ ውእቱ፡ (ረጂም ነው)
ቀላይ፡ ውእቱ፡ (ጥልቅ ባሕር ነው)
ልዑል፡ ውእቱ፡ (ልዑል ነው)
ወእሙቅ፡ ውእቱ፡ (ጥልቅ ነው)
ጽኑዕ፡ ውእቱ፡ (ጠንካራ ነው)
መዋዒ፡ ውእቱ፡ (አሸናፊ ነው)
ጠቢብ፡ ውእቱ፡ (ጥበበኛ ነው)
ማእምር፡ ውእቱ፡ (ዐዋቂ ነው)
ኃያል፡ ውእቱ፡ (ኀይለኛ ነው)
ተባዕ፡ ውእቱ፡ (ጀግና ነው)
ክቡር፡ ውእቱ፡ (ክቡር ነው)
ከሀሊ፡ ውእቱ፡ (ቻይ ነው)
ዋሕድ፡ ውእቱ፡ (አንድዬ ነው)
ወብሑት፡ ውእቱ፡ (ብቸኛ ነው)
መንክር፡ ውእቱ፡ (አስደናቂ ነው)
ከዚህ በታች ያለውን በማነጻጸ የእግዚአብሔርን አገላለጽ እንመልከት፤
ኄር፡ ዘእንበለ፡ እከይ፤ (ክፋት የለለበት ደግ፤) 11

ወየዋህ፡ ዘእንበለ፡ በቀል፤ (በቀል የሌለበት የዋህ፤)
ወዕጉሥ፡ ዘንበለ፡ መዓት፤ (ቁጣ የሌለበት ታጋሽ፤)
ጻድቅ፡ ዘእንበለ፡ ኃጢአት፤ (ኀጢአት የሌለበት ጻድቅ፤)
ወንጽሕ፡ ዘእንበለ፡ ርስሐት፤ (እድፍ የሌለበት ንጹሕ፤)
ወራትዕ፡ ዘእንበለ፡ ጥውየት፤ (ጠማማነት የሌለበት ቅን፤)
ወሃቢ፡ ዘእንበለ፡ ክልአት፤ (ንፍገት የሌለበት ሰጪ፤)
ወጸጋዊ፡ ዘእንበለ፡ ደንፅዎ፤ (ስስት የሌለበር ለጋሽ፤)
ሠራዬ፡ ኃጢአት፡ ዘእንበለ፡ በቀል፡ ወቂም፤ (በቀልና ቂም የሌለበት ኀጢአት ይቅር ባይ፤)
መጽያሕት፡ ዘእንበለ፡ ማዕቀፍ፤(እንቅፋት የሌለበት ጥርጊያ ጎዳና፤)
ወዐሠር፡ ንጹሕ፡ ዘእንበለ፡ አሥዋክ። (እሾኽ የሌለበት ንጹሕ ፈለግ፤)

ቅዳሴ ማርያምና ቅዳሴ ዲዮስቆሮስ የአባ ጊዮርጊስ ድርሰቶች ለመሆናቸው ምንምጥርጥር የለውም። ቅዳሴ ያዕቆብ ዘሥሩግና ቅዳሴ ቄርሎስም የሳቸው ሳይሆኑአይቀሩም።

ሌላው የአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ሥራ መታወቂያ ካለው ግስ ላይ አዳዲስ ቃላትይፈጥራሉ። በቅዳሴ ማርያም ውስጥ የሚገኙ ቃላት “አማዕበለ” (ማዕበል አነቃነቀ)“መስግዲ” (አሰግድ) “መትሐቲ” (ዝቅ አርጌ) “መቅንዪ” (አስገዥየአባ ጊዮርጊስፍጥረቶች ናቸው።

ለኛ ባልታወቁ የውጪ ቃላት ይጠቀማሉ ብያለሁ። በሥነ ጽሑፍ ውስጥ ፒላስ”(ድንኳንየሚለው ቃል የተገኘው ሦስት ቦታ ብቻ ነው፤ 1. በመጽሐፈ ምስጢር፤ 2.በአርጋኖነ ውዳሴ፤ 3. በቅዳሴ ቄርሎስ፤

 
ሜሎስ (እሳታዊየሚለው ቃል የተገኘው ሦስት ቦታ ብቻ ነው፤ 1. በመጽሐፈምስጢር፤ 2. በቅዳሴ ያዕቆብ ዘሥሩግ፤ (3) በቅዳሴ ቄርሎስ፤

እመቤታችን ታቦት ዘዶርታቦተ ዶር የተባለችው 1. ቅዳሴ ማርያም 2.በመጽሐፈ ምስጢር ውስጥ ብቻ ነው።

የግዕዝ ሥነ ጽሑፍ ቅርሳችን ተዝረክርኳል። እስካሁን የደረሱለት ምዕራባውያን ብቻናቸው። የኛ ዝምታና ቍጭትአልባነት ባለማወቅና አስታዋሽ በማጣት ይመስለኛል።ቢያውቅና አስታዋሽ ቢያገኝ ቍጥሩ ከአምሳ ሚሊዮን የማያንስ ሕዝብ የማንነቱመታወቂያ ቅርሱ ሲወድም ዝም ብሎ አያይም። ሳንውል ሳናድር የኢትዮጵያ ሥነጽሑፍ ቅርስ ድርጅት ማቋቋም አለብን። ድርጅቱ መጻሕፍቱ የሚጠበቁበትን ዘዴይፈልጋል፤ ለሚመረምሯቸው ተማሪዎች የገንዘብ እርዳታ ይሰጣል።

ስላዳመጣችሁኝ ከልብ አመሰግናለሁ።

                                   በአውሮጳ   የካህናት አንድነት ማኅበር ሊቋቋም መሆኑ ታወቀ በ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከመላዋ አውሮጳ   የተውጣጡ ካህናት፡” የ...