2015 ኦገስት 5, ረቡዕ

በእንተ ሙኒክ ደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያንና ሊቀ ብርሃናት ቆሞስ አባ ገብረ ሕይወት ፍስሐ [ጀርመን ]


ምእመናን  ከአንዱ ሀገር ወደ  ሌላው ሀገር በተለያየ ምክንያት  መሰደዳቸው አይቀሬ  ነው:: ታዲያ ሲሰደዱ በሄዱበት  ሀገር  ሁሉ ቤተክርስቲያን ያስፈልጋቸዋል :: ምንም አያጠያይቅም  የተመቻቹ  ሁኔታዎችም  አሉ :: ቤተክርስቲያን መግዛት ይቻላል :; ምናልባት የሀገረ ስብከቶች   ወጥ የሆነ መዋቅር አለመኖር  የምእመናኑ  አንድ ሐሳብ አለመሆን  ወዘተ  ችግሮች  ውጤታማ  የሆነ መንፈሳዊ አገልግሎት ለመስጠት  ችግሮች ይታያሉ :: የህዝቡ መንፈሳዊ  ተነሳሽንት  ግን ይበል የሚያሰኝ ነው :: በተለይ አንዳንድ  አድባራት ቤተክርስቲያን ለመግዛት  የሚያደርጉት እንቅስቃሴ  በጣም ግሩም ነው :;ለዛሬ የማካፍላችሁ  ስለሙኒክ ደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል  ቤተክርስቲያን ነው  [ጀርመን ] ሙኒክ /ሙንሽን  ማለት  የመነኮሳት  ከተማ  ማለት ነው :: ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን አለ  በዚያ የሚኖሩ ምእመናን በጣም  ጠንካሮች  ናቸው :: “ጓደኛህን ንገረኝና ማንነትህን  ልንገርህ”  እንደተባለው  የሕዝቡ  ጥንካሬ  የቤተክርስቲያን  ግዥ እንቅስቃሴውን  ልነግራችሁ  አልችልም;;  ምስጢሩ  ደግሞ ልንገራችሁ ?  ; የሊቀ ብርሃናት ቆሞስ  አባ ገብረ ሕይወት ፍስሐ  ከፍተኛ  እንቅስቃሴ  ውጤት ነዋ !
ሊቀ ብርሃናት  ቆሞስ አባ ገብረ ሕይወት ፍስሐ   በጀርመን  የሙኒክ  ደብረ ብሥራት  ቅዱስ  ገብርኤል ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ  ናቸው:: ሀገር ቤት /  ኢትዮጵያ አዲስ አበባ  ኢያሉ  በተለያዩ  አድባራት  በአስተዳዳሪነት  ለረጅም ጊዜያት  አገልግለዋል::

ሊቀ ብርሃናት አባ ገብረ ሕይወት  የቅዳሴ መምህር  ናቸው  አቋቋም አዋቂ ማኅሌታዊ ናቸው  ከሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ  መንፈሳዊ ኮሌጅ  በዲፕሎማ  ; ከቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ  የመጀመሪያ ድግሪ አግኝተዋል ሙኒክ ከሚገኘው  ሉድቪግ ማክስሚልያንስ  ዩኒቨርሲቲ  የጀርመንኛ  ቋን ቋ  ሰርተፍኬት ተቀብለዋል አሁንም በመማር ላይ ይገኛሉ :: ሲቀድሱ ማኅሌት ሲቆሙ  ሲያስተምሩ  ሕዝቡን  ለበጎ ነገር  ሲያስተባብሩ  በተለይ ቤተክርስቲያን ለመግዛት  በሚያደርጉት የማስተባበር  የማስተዳድር  ልዩ ስጦታቸ  በሀገር ቤትም ሆነ በዚሁ በጀርመን በሀገረ ስብከቱም  ሆነ በሕዝቡ ዘንድ የተመሰከረላቸው ናቸው አስቀዳሹ ሁሉ ሳይቀር መልክዐ ውዳሴውን  በሚገባ አሰልጥነዋል  ለድቁናም የበቁ ደቀመዛሙርትም  አፍርተዋል 
በቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ሊቀብርሃናት ሊቀብርሃናት  ደከመኝ ሰለቸኝ ማለት አያውቁም :: ታዲያ እንዲህ ያሉ አባቶች ከአገልግሎት  ፍላጎት እስክ  ብቃት  .ከብቃት እስከ ውጤታማንት  የተዋጣላቸው አባቶቻች  ጥቂቶች  ቢሆኑም  ምእመናኑ እንደነዚህ  ያሉ አባቶችን  ከጎናቸው በመቆም  አብሮ ማገልገል ይገባል :: በሙኒክ ደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል  ቤተክርስቲያንን  ለመግዛት  እየተደረገ  ያለው እንቅስቃሴ  በጣም የሚበረታታ  ነው :: 

                                   በአውሮጳ   የካህናት አንድነት ማኅበር ሊቋቋም መሆኑ ታወቀ በ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከመላዋ አውሮጳ   የተውጣጡ ካህናት፡” የ...