2015 ሴፕቴምበር 9, ረቡዕ

ወሪድዬ ብሄረ ሮሜ /ቅዱስ ያሬድ/

                                                                                ካታኮምፕ

ቅዱስ ጳውሎስ የተሠየፈበት
                                                                                                        ቅዱስ ጴጥሮስ   የታሰረበት
 


 ቅዱስ ጳውሎስ የታሠረበት

 የቅዱሳን የተጋድሎ አደባባይ  ፡ ሐዋርያት ስለ ሃይማኖታቸው  እውነትን  መስክረው አንገታቸውን  ለሠይፍ  የሰጡባት   የተሰቀሉባት  የቅዱሳን በአት  የጸሎት ዋሻቸው   የተዋሕዶ  ሃይማኖት  የኪነ ጥበብ  ምድር የነበረች  ዛሬም እንኳን  ያ ሁሉ የቅዱሳን የገድል ውጤት  የሚታይባት  የዓለም ጎብኚዎች  የሚተሙባት  ምድረ ሮሜን  በመንፈስ  ተመርቶ  በርቀት ተመልክቶ  ወደ ሮሜ  ወረድኩ ወርጄ  ስለቤተ ክርስቲያን  ተናገርኩ በማለት ቅዱስ ያሬድ  ተናገረ  እኔም “ በከመ ሰማዕነ ከማሁ ርኢነ “  እንደ ሰማን እንዲሁ ተመለከትን” ተብሎ እንደ ተጻፈ   ቅዱስ ጳውሎስ አንገቱን የተሰየፈበት ቅዱስ  ጴጥሮስ  ቁልቁል የተሰቀለበት የቅዱሳን በአት  የጸሎት ዋሻቸው “ ካታኮምፕ “ የወቅቱ ነገሥታት  ቅዱሳኑን  ከአንበሳ ጋር  ያታገሉበት  ቦታ  ምን አደከማችሁ የቅዱሳን  የተጋድሎ አደባባይ  ነበረች ሮማ  የዛሬውን አያድርገውና፤፤ ሰሞኑን እያየሁ ነበረ  የቱሪስቱ ሰልፍ  ለካ ! የትም ሀገር  ሰልፍ አይቀሬ ነው ዓይነቱ ይለያያል እንጂ  አልኩና ዕድሜና ጤንነት  ለወንድም በለጠ እና ለባለቤቱ ቤተልሔም  እየተመኘሁ ከእነሱ ጋር በመዘዋወር   በጽሁፍ ያነበብኩትን  በዓይኔ ተመለከትኩ  የሮማንንም ካቶሊክ  ላመሰግን ወደድኩ /ባቲካንን/ ለምንም ይሁን ለምን  በጥንቃቄ  ይዛ ታስጎበኛለች  እኛ ብንሆን እስከ ዛሬ  አንጠብቀውም  ይልቁንም የሚሸጠውን  እንሸጠው ነበረ  ። ሀገራችን ብዙ የቅዱሳን ቦታዎች  አሉ ግን በአግባቡ አልያዝናቸውም  የቅዱሳኑ ቦታ በሙሉ በሌሎች ተይዞ ሲታይ ያሳዝናል ፤፤ ጌታችን ቅዱስ ጳውሎስን  እንዲህ በማለት ወደ ሮሜ ልኮታል

“አስተርአዮ እግዚእነ ለጳውሎስ ወይቤሎ ተአመን  በከመ ኮንከኒ ሰማእትዬ  በኢየሩሳሌም ከማሁ ሀለውከ ትኩነኒ  ሰማእትዬ በሮሜሂ “   ሥራ 23. 11

ጳውሎስ ሆይ  በኢየሩሳሌም ስለ እኔ እንደ መሰከርህ  እንዲሁ በሮሜም ትመሰክርልኝ ዘንድ ይገባልና አይዞህ አለው ።

 ይህ የጌታችንን ጥሪ በደስታ የተቀበለው ቅዱስ ጳውሎስ   ሄዶ መከራን በመቀበሉ ዛሬ ሮማውያን  የሱን  የገድል ውጤት ኢያሳዩ /ኢያስጎበኙ ይኖራሉ ።

ለአንክሮ

Ø የባቲካን የቅዱሳኑን ቦታዎችን አክብራ ለቱሪስት ምቹ አድርጋ  መጠቀሟ

Ø ከተማዋ /ሮም ማለቴ ነው በሙሉ የጥንት ሃይማኖታዊ መልኳን  ሳትለውጥ መቀጠሏ

           ማሳሰቢያ

Ø  ኢትዮጵያውያን  በሮማ  ላላችሁ  ሁላችሁም በሮማ ከተማ ያለውን  ታሪካዊ የቅዱሳንን  ቦታዎች  ያላያሁ ትኖራላችሁና  እንድታዩት አሳስባለሁ።               በሮሜ ላላችሁ ሁሉ ከእግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን ። ሮሜ . ፩ ፡ ፯

 

 የጉብኝት ሰልፍ


 

                                                                                                                                                                       


 




 

2015 ሴፕቴምበር 5, ቅዳሜ

የደቡብ ምሥራቅ እና ምዕራብ አውሮፓ ሀገረ ስብከት ፪ኛ ዙር ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባዔውን ትናንት ጀመረ



His_Grace_Abune_Mussie


 
ብፁዕ አቡነ ሙሴ
የደቡብ ደቡብ ምሥራቅና ምዕራብ አውሮፓ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
                                                                        

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን  የደቡብ ምሥራቅ እና ምዕራብ አውሮፓ ሀገረ ስብከት የ፪ኛ ዙር ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባዔውን ነሐሴ 29 /2007 ዓ ሞ  እንደሚጀምር  ታወቀ
በጀርመን  ፍራንክፈርት ለ፫ ቀናት በሚደረገው ጠቅላላ ጉባዔ ላይ በሀገረ ስብከቱ የሚገኙ ከ30 በላይ የሚሆኑ የአድባራት አስተዳዳሪዎች ፤  በማኅበረቅዱሳን የአውሮፓ ማእከል ተወካዮች  ምእመናን  እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ይሳተፋሉ . ጉባዔው ዓመታዊ የአድባራት  አገልግሎት  አፈጻጸም ሪፖርት እና የቀጣይ ዓመት ዕቅድ   ላይ የሚወያይ  ሲሆን  በገለልተኛ አቢያተክርስቲያናት ጉዳይም  ጠቅላላ ጉባዔው  አንድ ውሳኔ  እንደሚወስን ይጠበቃል  ጠቅላላ ጉባዔውን አስመልክቶ በፍራንክፈርት የሚገን አንድ ጋዜጣ እንደ ዘገበው  የከተማዋ ከንቲባ በተጋባዥነት በጉባዔው እንደ ሚገኙና የሀገረ ስብከቱ ሊቀጳጳስ የአቡነ ሙሴ  መንበረ ጵጵስና ለአገልግሎት ምቹ ይሆን ዘንድ ጠቅሶ  በከተማችን በንበረ ጵጵስና መኖሩ እድለኞች ያደርገናል ሲል ዘግቧ በመጨረሻም በሀገረ ስብከቱ ከፍተኛ የአገልግሎት አፈጻጸም ያገኙ አስተዳዳሪዎች በሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሙሴ  ሽልማት እንደሚበረከትላቸው  ለማወቅ ተችሏል  በሊቀ ጳጳሱ አቡነ ሙሴ በማግባባት ላይ የተመሠረተ  መንፈሳዊ የማስተዳደር ጥበብ የተነሳ ሀገረ ስብከቱ ሰላማዊና አድባራቱ የራሳቸው ቤተ ክርስቲያን እንዲኖራቸው የሚደረገው እንቅስቃሴ ምስክር ነው  በቅርቡ የራሳቸው ቤተ ክርስቲያን ለመግዛት ዝግጅታቸውን ያጠናቀቁ የሙኒክ ደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤልን የሚጠቀሱ ሲሆን የበርሊን ደብረ ገነት አማኑኤል ቤተ ክርስቲያን ደግሞ የራሳቸውን ቤተ ክርስቲያን ገዝተዋል ሌሎቹም ከፍተኛ እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ እንደሚገኙ የሀገረ ስብከቱ ያመለክታል





 

                                   በአውሮጳ   የካህናት አንድነት ማኅበር ሊቋቋም መሆኑ ታወቀ በ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከመላዋ አውሮጳ   የተውጣጡ ካህናት፡” የ...