2014 ፌብሩዋሪ 4, ማክሰኞ

በቅዱስ ላልይበላ ደብር የተፈጠረው አለመግባባት በሰላም ተፈታ






በሀገራችን ታሪክ መቀዳሚነት ዓለምን በማስደነቅ የሚታወቀውና በዩኔስኮ ተመዝግቦ ሀገሪቱን በከፍተና ደረጃ የሚያስተዋውቀው የቅዱስ ላልይበላ ደብር በቀድሞው አሰተዳዳሪ አበ ገብረ ኢየሱስ አስተዳደር ፤ የከተማው ባለሃብት እና በከተማው የቱሪስት አስጎብኚ ማህበራት መካከል አለመግባባት ተፈጥሮ ረጅም ጊዜ የፈጀ መሆኑን የተለያዩ የዜና ምንጮች  ሲዘግቡት መቆታቸው ይታወቃል  ይሁን እንጂ በሶስት ተከፍለው ማለትም በደብሩ አስተዳደር፤ በከተማው ባለሀብት እና በከተማው ያሉ አስጎብኚ ማህበራት መካከል የአሰራር ክፍተቶች  እንደ ነበረና በተለይ በደብሩ የቀድሞ አስተዳደር አማካይነት የተፈጠሩ የአሰሠራር ችግሮች ስለነበሩ የደብሩ አስተዳዳሪ አባ ገብረ ኢየሱስ  ከስተዳዳሪነት ንዲነሱ ተደርጓል፡፡ ነገር ግን በወቅቱ የተከሰተውን አለመግባባትን ለመፍታት የከተማው አስተዳደር እና የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት የሰላም ኮሚቴ አዋቅሮ ስለነበር ኮሚቴው የሶስቱንም አካላት ችግሮች ካጠና በኋላ ለሶስቱም የሚስማማ የእርቀ ሰላም ሰነድ አዘጋጅቶ ጥር 25/2006ዓ.ም በዚያው በላልይበላ ጽርሐ ቤተ አብርሃም አዳራሽ የደብሩ ሊቃውንት፤ ሰበካ ጉባዔ፤ የከተማው ባለሃብት፤ አስጎብኚ ማህበራት በተገኙበት ለደብሩ አዲስ በተመደቡት አስተዳዳሪ መ/ር አባ ወልደ ትንሣኤ አስተባባሪነት በከተማው ከንቲባና እና በሰላም ኮሚቴው ከፍተኛ ጥረት ሁሉም አካላት እንዲታረቁ ሆኖአል፡፡ በእርቀ ሰነዱ ላይም የሚከተሉት ስምምነቶች ተካተዋል፡፡

                                                                 
                                                                   

                                                                   እርቀ  ሰላሙ ሲፈጸም

በደብሩ አስተዳደር
1 . በቀድሞው አስተዳዳሪ የተባረሩት ሊቃውንት ካህናትና ልዩልዩ ሠራተኞች እንዲመለሱ
2. በደብሩ ግልጽና ተጠያቂነት ያለው አሠራር እንዲኖር
3. የአብነት መምህራን  ሊቃውንቱ ከፍተኛ ትኩረት እንዲሰጣቸው
4.ደብሩ ልዩ ልዩ እቅዶችን እያቀደ ከህዝቡ ጋር እተመካከረ እንዲሠራ
5. የደብሩ ትኩረት ከቱሪስቱ ባለፈ ለአካባቢው ሕዝብ የሚሆን የልማት አውታር ቢቀርጽ እና ተግባራዊ  ቢያደርግ የሚሉት እና ሌሎችም ይገኙበታል፡፡
                          በከተማው ባለሀብት
1.    በደብሩ የሚፈጠረውን ማንኛውንም ችግሮችን ዝም ማለቱ ቀርቶ ችግሩን በጋራ መፍታት
2.   በልማት ሆነ በመሳሰሉት አገልግሎት ተሳታፊ እንዲሆኑ
3.   በከተማው የሚስተናገዱትን ቱሪስቶች በትብብር ማስተናገድና የመሳሰሉትን አካቶአል
                 የከተማው አስጎብኚ ማኅበራት

1.    የደብሩን ታሪክ በሚገባ አጥንተው ሳይጨመርና ሳይቀነስ ቱሪስቱን እንዲያስረዱ
2.   ሃይማኖታዊ ሥነ ምግባርን በተላበሰ መልኩ የማስጎብኘት ተግባራትን እንዲያከናውኑ
3.   የከተማውን ሰላም በማስፈን ረገድ ከፍተኛ ድርሻ ስላላቸው የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡ
4.   በገንዘባቸውም ሆነ በመሳሰሉት ደብሩን የመደገፍ ሥራ እንዲሰሩ እና የመሳሰሉትን እንዲተገብሩ በእርቀ ሰላሙ  ሰነድ ላይ ከተካተተው ውስጥ ጥቂቶቹ ናቸው፡፡ በአጠቃላይ ወደፊት ችግሮች ቢኖሩም በውይይት እንዲፈታ እና ሁሉም የቤተ ክርስቲያን ልጆች እንደ መሆናችን መጠን ለቤተ ክርስቲያናችን የሚገባንን ሁሉ ለመወጣት ዝግጁ ነን በማለት እርቀ ሰላሙ ተፈጽሟል፡፡

                                        
                                                    

                                                    የጉባኤው ተሳታፊዎች በከፊል

                                   በአውሮጳ   የካህናት አንድነት ማኅበር ሊቋቋም መሆኑ ታወቀ በ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከመላዋ አውሮጳ   የተውጣጡ ካህናት፡” የ...