2015 ሜይ 15, ዓርብ

ሰበር-ዜና የታላቁ ደብረ ሊባኖስ ገዳም የድጓው ሊቅ አለቃ መርዓዊ /የኔታ መኮንን አረፉ



ነገ ወደ መንገድ እሄዳለሁ ውዳሴ ማርያም እንዳታስታጉሉ፡፡

የኔታ መርዊ ሐሙስ ማታ ተማዎቻቸውን ካስተማሩ በኋላ  ከተናገሩት 

         
                                                                     
ደብረ ሊባኖስ ገዳም ሲነሳ አብረው የሚታወሱ ለረጅም ዘመናት ድጓ በማስተማር በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንን የፈሩ በምናኔያቸው ፤በማስተማር ብቃታቸው፡ በመኅሌት ቁመት ድካም የማያውቃቸው አለቃ መርዓዊ ዛሬ ግንቦት 7 /2007 ዓ.ም ማረፋችው ተሰማ፡፤ ይህ ዜና እንደተሰማ በተለይ በ አዲስ አበባ አድባራትና ገዳማት በማገልገል ላዪ የሚገኙ ሊቃውንት ልጆቻቸው ዛሬ ከሰዓት በኋላ ወደ ደብረ ሊባኖስ ገዳም ኢየተመሙ ይገኛሉ፡፡አለቃ መርዓዊ ከገዳሙ ህልውና ቀጥሎ በስስት ዓይን የሚታዩ ትሁት ፤መናኝ፤ ፤ ማኅሌታዊ፤ መምህር ነበሩ ፡፡
ማሳሰቢ
ይህን አሳዛኘ ዜና የሰማሁት  ለአገልግሎት ኮቦልቻ  እንደደረስኩ ነውና  ሙሉ ዝርዝር መረጃዎችን አጠናክረን እናደርሳለን፡፡
የሊቁ አባታችንን ነፍስ ከቅዱሳን ሊቃውንት አጠገብ ያኑርልን፡፡

                                   በአውሮጳ   የካህናት አንድነት ማኅበር ሊቋቋም መሆኑ ታወቀ በ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከመላዋ አውሮጳ   የተውጣጡ ካህናት፡” የ...