2015 ሴፕቴምበር 5, ቅዳሜ

የደቡብ ምሥራቅ እና ምዕራብ አውሮፓ ሀገረ ስብከት ፪ኛ ዙር ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባዔውን ትናንት ጀመረ



His_Grace_Abune_Mussie


 
ብፁዕ አቡነ ሙሴ
የደቡብ ደቡብ ምሥራቅና ምዕራብ አውሮፓ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
                                                                        

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን  የደቡብ ምሥራቅ እና ምዕራብ አውሮፓ ሀገረ ስብከት የ፪ኛ ዙር ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባዔውን ነሐሴ 29 /2007 ዓ ሞ  እንደሚጀምር  ታወቀ
በጀርመን  ፍራንክፈርት ለ፫ ቀናት በሚደረገው ጠቅላላ ጉባዔ ላይ በሀገረ ስብከቱ የሚገኙ ከ30 በላይ የሚሆኑ የአድባራት አስተዳዳሪዎች ፤  በማኅበረቅዱሳን የአውሮፓ ማእከል ተወካዮች  ምእመናን  እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ይሳተፋሉ . ጉባዔው ዓመታዊ የአድባራት  አገልግሎት  አፈጻጸም ሪፖርት እና የቀጣይ ዓመት ዕቅድ   ላይ የሚወያይ  ሲሆን  በገለልተኛ አቢያተክርስቲያናት ጉዳይም  ጠቅላላ ጉባዔው  አንድ ውሳኔ  እንደሚወስን ይጠበቃል  ጠቅላላ ጉባዔውን አስመልክቶ በፍራንክፈርት የሚገን አንድ ጋዜጣ እንደ ዘገበው  የከተማዋ ከንቲባ በተጋባዥነት በጉባዔው እንደ ሚገኙና የሀገረ ስብከቱ ሊቀጳጳስ የአቡነ ሙሴ  መንበረ ጵጵስና ለአገልግሎት ምቹ ይሆን ዘንድ ጠቅሶ  በከተማችን በንበረ ጵጵስና መኖሩ እድለኞች ያደርገናል ሲል ዘግቧ በመጨረሻም በሀገረ ስብከቱ ከፍተኛ የአገልግሎት አፈጻጸም ያገኙ አስተዳዳሪዎች በሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሙሴ  ሽልማት እንደሚበረከትላቸው  ለማወቅ ተችሏል  በሊቀ ጳጳሱ አቡነ ሙሴ በማግባባት ላይ የተመሠረተ  መንፈሳዊ የማስተዳደር ጥበብ የተነሳ ሀገረ ስብከቱ ሰላማዊና አድባራቱ የራሳቸው ቤተ ክርስቲያን እንዲኖራቸው የሚደረገው እንቅስቃሴ ምስክር ነው  በቅርቡ የራሳቸው ቤተ ክርስቲያን ለመግዛት ዝግጅታቸውን ያጠናቀቁ የሙኒክ ደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤልን የሚጠቀሱ ሲሆን የበርሊን ደብረ ገነት አማኑኤል ቤተ ክርስቲያን ደግሞ የራሳቸውን ቤተ ክርስቲያን ገዝተዋል ሌሎቹም ከፍተኛ እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ እንደሚገኙ የሀገረ ስብከቱ ያመለክታል





 

                                   በአውሮጳ   የካህናት አንድነት ማኅበር ሊቋቋም መሆኑ ታወቀ በ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከመላዋ አውሮጳ   የተውጣጡ ካህናት፡” የ...