2016 ሴፕቴምበር 28, ረቡዕ

ካህናት በደመራ ላይ
  በፊንላንድ ሄልሲንኪ ለመጀመሪያ ጊዜ የመስቀል ደመራ በዓል በአደባባይ ተከበረ                                                                 ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰሜን ምዕራብ አውሮፓ ሀገረ ስብከት በፊንላንድ የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት  ቤተክርስቲያን ለመጀምሪያ ጊዜ በአደባባይ የመስቀል ደመራ በዓል መስከረም 16. 2009 ዓ.ም ተከበረ::በዕለቱ የሄልሲንኪ ደብረ ሰላመ መድኃኔ ዓለም የኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን  ካህናት ዲያቆናት ምእመናን ከከተማው አስተዳደር ጀምሮ የባህል እና የሌሎችም ተቋማት ሓላፊዎች ጋዜጠኖች በቦታው ተገኝተዋል የፊንላንድ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን  እና የሌሎቹም ቤተ እምነት መሪዎች ታድመዋል  በሃገራችንም እንደተለመደው በዓበይት በዓላት ብቻ የሚገኙ ምእመናን በዚሁ በስደት ሀገር መኖራቸው የሚገርም ቢሆንም  ያን ዕለት  ተገኝተዋል በተለይ በስደት ያለ ሰው በጣም የሚከፋው ለጥምቀትና  ለመስቀል ደመራ በዓል ጊዜ ነው ይባላል ሁለቱም የአደባባይ በዓላት ናቸው  ያን ዕለት እቤቱ የሚቀር ሰው የለም በሀገር ቤት  ሄልሲንኪም  ያ ትዝ አለኝ ይህ ሁሉ ሰው ነበረ ከሚለው ጥያቄ ጋር የሚገርመው የፈረንጆቹ ደስታ ከ ሐበሻው ቢበልጥ እንጂ አያንስም  ነበረ  ከልብ የመነጨ ልዩ ደስታ ከፊታቸው ይነበባል  አንዳንዶቹም በሀገራችን እንዲህ ያለ ሃይማኖትና ሥርዓትና ሃይማኖት በመኖሩ መደሰታቸውን በመግለጥ  እስካሁን በፊንላንድ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይምኖት ቤተ ክርስቲያን ያለች ሲሆን   በቤተ ክርስቲያን ደረጃ ከተመሠረተች  አምስት ዓመታት ያህል አስቆጥራለች የሄልሲንኪ ደብረ ሰላመ መድኃኔ ዓለም የኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን  በዚሁ ከተማ ይገኛል የካህናቱና       የምእመናኑ ፍቅር የተለየ ነው ያዝልቅልን እንጂ  የደመራውንም በዓልም በደስታ በጋራ  ማክበራችን  በፈረንጆች ዘንድ ልዩ ትዝታን ፈጥሯል

                       ቢያደርሰን ቢያደርሳችሁ ለሚቀጥለው ዓመት  ጸልዩ
  በፊንላንድ ሄልሲንኪ ለመጀመሪያ ጊዜ የመስቀል ደመራ በዓል በአደባባይ ተከበረ   ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰሜን ምዕራብ አውሮፓ ሀገረ ስብከት በፊንላንድ የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት  ቤተክርስቲያን ለመጀምሪያ ጊዜ በአደባባይ የመስቀል ደመራ በዓል መስከረም 16. 2009 ዓ.ም ተከበረ::በዕለቱ የሄልሲንኪ ደብረ ሰላመ መድኃኔ ዓለም የኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን  ካህናት ዲያቆናት ምእመናን ከከተማው አስተዳደር ጀምሮ የባህል እና የሌሎችም ተቋማት ሓላፊዎች ጋዜጠኖች በቦታው ተገኝተዋል የፊንላንድ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን  እና የሌሎቹም ቤተ እምነት መሪዎች ታድመዋል  በሃገራችንም እንደተለመደው በዓበይት በዓላት ብቻ የሚገኙ ምእመናን በዚሁ በስደት ሀገር መኖራቸው የሚገርም ቢሆንም  ያን ዕለት  ተገኝተዋል በተለይ በስደት ያለ ሰው በጣም የሚከፋው ለጥምቀትና  ለመስቀል ደመራ በዓል ጊዜ ነው ይባላል ሁለቱም የአደባባይ በዓላት ናቸው  ያን ዕለት እቤቱ የሚቀር ሰው የለም በሀገር ቤት  ሄልሲንኪም  ያ ትዝ አለኝ ይህ ሁሉ ሰው ነበረ ከሚለው ጥያቄ ጋር የሚገርመው የፈረንጆቹ ደስታ ከ ሐበሻው ቢበልጥ እንጂ አያንስም  ነበረ  ከልብ የመነጨ ልዩ ደስታ ከፊታቸው ይነበባል  አንዳንዶቹም በሀገራችን እንዲህ ያለ ሃይማኖትና ሥርዓትና ሃይማኖት በመኖሩ መደሰታቸውን በመግለጥ  እስካሁን በፊንላንድ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይምኖት ቤተ ክርስቲያን ያለች ሲሆን   በቤተ ክርስቲያን ደረጃ ከተመሠረተች  አምስት ዓመታት ያህል አስቆጥራለች የሄልሲንኪ ደብረ ሰላመ መድኃኔ ዓለም የኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን  በዚሁ ከተማ ይገኛል የካህናቱና       የምእመናኑ ፍቅር የተለየ ነው ያዝልቅልን እንጂ  የደመራውንም በዓልም በደስታ በጋራ  ማክበራችን  በፈረንጆች ዘንድ ልዩ ትዝታን ፈጥሯል

                       ቢያደርሰን ቢያደርሳችሁ ለሚቀጥለው ዓመት  ጸልዩ

2016 ሴፕቴምበር 23, ዓርብ

 የመስቀል ደመራ በዓል ለመጀምሪያ ጊዜ በፊንላንድ ሄልሲንኪ  በአደባባይ  እንደሚከበር ተገለጸ

ፊንላንድ በሰሜን አውሮፓ ሀገሮች መካከል አንዷ ናት 5.5 ሚሊየን ሕዝብ እንድሚኖርባት የሚነገርላት ፊንላንድ ወደ ሰሜን ዋልታ ጠጋ ያለች ሀገር በመሆኗ በቅዝቃዜዋም ትታወቃለች  ነዋሪዎቿ በሥነ ምግባራቸውና  በዝምታቸው ይታወቃሉ። ረዘም ያለ ጊዜ በሀገሪቷ የቆዩ የውጪ ዜጎችም ይህንኑ ጠባይ ይጋሩታል   በሃይማኖት በኩል ሲታይ በሀገሪቱ 2 % ያህሉ የፊንላንድ ኦርቶዶክስ  ሃይማኖት ተከታይ ሲሆኑ የቀሩት በአብዛኛው ሉተራውያን  ናቸው  የውጪ ዜጎች ሁሉም  አኃት አቢያተ ክርስቲያናት ቢኖሩም ክፍተኛ እንቅስቃሴ ያላቸው  ግን  የኢትዮጵያና እና የኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ተከታዮች ናቸው   በፊንላንድ ዋና ከተማ  ሄሊሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን እና የደብረ ሰላም መድኃኔዓለም  የኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አቢያተ ክርስቲያናት  ይገኛሉ ። ሁለቱም አድባራት መንፈሳዊ እና ምኅበራዊ አገልግሎቶችን በጋራ ይፈጽማሉ ። በሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ለመጀመሪያ ጊዜ  በ2009 ዓ.ም መስከረም 16 ቀን በሀገሪቱ ሰዓት አቆጣጠር  ከ 1730  ጀምሮ እንደ ሀገራችን ሁሉ በአደባባይ / መስቀል አደባባይ / ይከበራል  የፊንላንደ ኦርቶዶክስ የከተማው ከንቲባ ልዩ ልዩ መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት መጋበዛቸው ተገልጧል በአሁን ሰዓት ምእመናኑ በዝግጅት ላይ ይገኛሉ ምንም በስደት ሀገር ብንኖርም  ልክ እንደ ሀገራችን ሕዝቡ የሀገር ባህል ልብሱን ለብሶ ሕፃናትም ሁሉ ተሰልፈው በዝማሬ የደመራው ሥነ ሥረዓት  በልዩ  ሁኔታ እንደሚከበር  ይጠበቃል ።                                                       እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ አደረሳችሁ

                                   በአውሮጳ   የካህናት አንድነት ማኅበር ሊቋቋም መሆኑ ታወቀ በ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከመላዋ አውሮጳ   የተውጣጡ ካህናት፡” የ...