2014 ኦገስት 11, ሰኞ

ኦ ፍና/ቆፍና ቅዱስ አማኑኤል ቤተክርስቲያን


ከአዲስ አበባ 185 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በመርሐቤቴ ወረዳ በዓላም ከተማ  የሚገኝ  በ4ኛው ክፍለ ዘመን በአባ ሰላማ ካሣቴ ብርሃን አማካይነት በአብርሃ ውአጽብሃ ነገሥታት  እንደታነጸ ይነገራል፡፡
ነገሩ እንዲህ ነው በ4ኛው ክ/ዘ ነገስታቱ አብርሃ ወአጽብሃ ከጳጳሱ አባ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን ጋር በመሆን አብያተ ክርስቲናትን በማሳነጽ  በማስፋፋት ላይ በነበሩበት  ጊዜ በመርሐቤቴ ሲያልፉ አሁን ቤተክርስቲያኑ የታነጸበት ቦታ  ጳጳሱ አባ ሰላማ አረፍ አሉ፡ እዚያው እያሉ ጌታችን የተወለደባትን  ቤተልሔምን በራእይ  አሳያቸው ከቦታውም ጋር አመሳስሎ ካሳያቸው በኋዋላ  ቤተ ክርስቲን መስራት እንዳለባቸው ተገነዘቡ፡፡ ይህ መንገድ በጣም ድንቅ ነው ሲሉ ኦ ፍና ብለው ጠሩት /ቆፍና ማለት፡  ቆፍ  ብሂል ቅሩበ እግዚአብሔር ማለት ነውና  እገዚአብሔር የቀረበው ቦታ ነው ሲሉ እንዲህ ሰይመውታል፡፡ከዚያ ተነሳ  በእውነት እግዚአብሔር ከኛ ጋር ነው  በማለት የቅዱስ አማኑኤል ቤተክርስቲያን እንዲታነጽ ወሰኑ፡፡አማኑኤል ማለት እገዚአብሔር ከኛ ጋር ነው ማለት ነውና፡፡ይህ ጥንታዊ ቤተ ክርስቲያን እጅግ በጣም የቆዩ ቅርሳቅርስ የሚገኙበት ታርካዊ  ጥንታዊ ነው ፡፡ ባሁኑ ሰዓት በቦታው የሚገኙትን ቅርሶች ለጎብኚዎች በሚመች መልኩ ላስቀመጥና ለጉብኝት ዝግጁ ላማድረግ የደብሩ ሰበካ ጉባዔ ከሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች ጋር በጋራ በመስራት ላይ መሆናቸውን የደብሩ አስተዳዳሪ ሊቀ ትጉሃን ጳውሎስ ገልጸዋል፡፡ ኦ ፍና ቅዱስ አማኑኤል በአሁኑ ሰዓት ኦ ፍና አምሳለ ቤተልሔም ቅዱስ አማኑኤል ቤተ ክርስቲያን በሚል በብፁዕ አቡነ ኤፍሬም የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ተሰይሞአል፡፡ ይህ ጥንታዊ ደብር ከርእሰ አድባራት ተድባበ ማርያም  ቤተ ክርስቲያን  ቀጥሎ መሠራቱ  ይታውቃል፡፡ቦታውን ከፍ አድርጎ ትራራ ላይ ለመሥራት ታስቦ በውቅቱ የነበሩት  ምእመናን  ከተለያ ቦታዎች አፈር አምጥተው ስለደለደሉት አራት አይነት አፈር በቦታው ይገኛል፡፡ ደብሩም በግራኝ አህመድ ጊዜ በመቃጠሉ ብዙ ቅርሶች የወደሙ ሲሆን በየጊዜው የተነሱ ነገሥታት መልሰው  አሳንጸውታል፡፡ ምእመናን!  ወደ ቦታው በመሄደ እንድትጎበኙ የደብሩ ሰበካ ጉባኤ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡


                                   በአውሮጳ   የካህናት አንድነት ማኅበር ሊቋቋም መሆኑ ታወቀ በ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከመላዋ አውሮጳ   የተውጣጡ ካህናት፡” የ...