2015 ፌብሩዋሪ 18, ረቡዕ

21 የግብጽ ኮፕት ክርስቲያኖች ሰማእትነት ተቀበሉ


አትም ኢሜይል
የካቲት 10 ቀን 2007 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
egypt copts21 የግብጽ ኮፕት ክርስቲያኖች ራሱን ኢስላሚክ ስቴት /ISIS/ እያለ በሚጠራው አሸባሪ ቡድን በምሥራቃዊ ሊቢያ ሲርት ውስጥ የካቲት 8 ቀን 2007 ዓ.ም. ሰማእትነት ተቀበሉ፡፡

አሸባሪ ቡድኑ በላከው የአምስት ደቂቃ የምሥል ወድምጽ መረጃ አጋቾቹ ሰውነታቸውን በጥቁር አልባሳት በመሸፈን፤ ታጋቾቹን ደግሞ ብርቱካናማ ልብስ በማልበስ ወደ የባሕር ዳርቻ በመውሰድና በጉልበታቸው በማንበርከክ ጭካኔ በተሞላበት ሁኔታ አንገታቸውን ቀልተዋቸዋል፡፡

በእምነታቸው ምክንያት የታገቱት እነዚህ የኮፕት ክርስቲያኖች ለሥራ ፍለጋ ከግብጽ ወደ ሊቢያ የሔዱ ሲሆን፤ በታጣቂዎቹ መታገታቸውን ቢቢሲ እና የተለያዩ ዓለም አቀፍ የመረጃ ምንጮች ዘግበዋል፡፡

የክርስቲያኖቹ መገደል ከፍተኛ ቁጣን የቀሰቀሰ ሲሆን፤ የተለያዩ የሃይማኖት ተቋማት፤ የሀገራት መሪዎች እንዲሁም የተለያዩ የመንግሥታት ሓላፊዎች ተቃውሟቸውን እየገለጹ ይገኛሉ፡፡

የግብጹ ፕሬዚዳንት አብዱልፈታህ አልሲሲ በሀገሪቱ ቴሌቪዥን ቀርበው በሰጡት መግለጫ “በክርስቲያኖቹ ግድያ ጊዜውን የጠበቀ አጸፋ ለመመለስና አስፈላጊውን እርምጃ ለመውሰድ ያሉንን አማራጮች ሁሉ እንድንጠቀም እንገደዳለን” ብለዋል፡፡
 

በተያያዘ ዜና የግብጽ ኮፕት ቤተ ክርስቲያን የክርስቲያኖቹን ሰማእትነት ለማዘከር በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገር በሚገኙ አብያተ ክርስቲያናቷ ለሰባት ቀናት የሚቆይ ጾም፤ ጸሎትና ቅዳሴ እንዲደረግ አውጃለች፡፡

                                   በአውሮጳ   የካህናት አንድነት ማኅበር ሊቋቋም መሆኑ ታወቀ በ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከመላዋ አውሮጳ   የተውጣጡ ካህናት፡” የ...