2015 ኤፕሪል 21, ማክሰኞ

ሰበር ዜና – ቅ/ሲኖዶስ ከነገ ሚያዝያ ፲፬ ቀን ጀምሮ የሰባት ቀናት ጸሎተ ምሕላ ዐወጀ፤ ቤተሰቦች የተሠው ክርስቲያኖችን ፎቶ፣ ስመ ክርስትና እና ሙሉ አድራሻ እንዲያቀርቡ አዘዘ – ‹‹ልጆቻችን የሃይማኖት ሰማዕትነትን የተቀበሉ የሃይማኖት መስተጋድላን ናቸው››


pat mat
  • ቅዱስ ሲኖዶስ በሊቢያ በግፍ የተሠው ክርስቲያኖች፣ ሃይማኖታችንን አንክድም በማለት የሃይማኖት ሰማዕትነትን የተቀበሉየሃይማኖት መስተጋድላን መኾናቸውን አረጋገጠ፤ ‹‹የልጆቻችን ሰማዕትነት በእግዚአብሔር መንግሥት ታላቅ ዋጋ ስላላቸው በዚኽ ከሐዘናችኹ እንድትጽናኑ ቤተ ክርስቲያን ታሳስባለች፡፡››
  • ነገ ወቅዱስ ፓትርያርኩ እና ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፣ መላው የአዲስ አበባ ገዳማት እና አድባራት አስተዳዳሪዎች፣ ሊቃውንት፣ ካህናት የሰንበት ት/ቤቶች ወጣቶች እንዲኹም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የየመምሪያው ሓላፊዎች እና ልዩ ልዩ ሠራተኞች በተገኙበት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ጸሎተ ፍትሐት እና ጸሎተ ወንጌል ይከናወናል 
  • ሥነ ሥርዐቱ በደቡብ አፍሪቃ በግፍ የተገደሉ ንጹሐን ኢትዮጵያውያንንም ይጨምራል

ነፍስህን ይማር በሉኝ


 ሁለት የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮች በአንድ ላይ  ያገለግላሉ  ሰባክያነ ውንጌል ናቸው  አንደኛው ለአገልግሎት ውደ ክፍለ ሀገር ወጥተው  ሲመለሱ የመኪና አደጋ ደረሰና ወደ 35 ሰዎች ህይወታቸው  ሲያልፍ ሰባኬ ወንጌሉ ተረፉ  ይህንን የሰማ በልደረባቸው  የስራ አጋሮቹን ጠርቶ  ከፊታቸው ቁጭ ብሎ  ነፍስህን ይማረው  በሉኝ  እኔ እደሆን  ለአገልግሎት መንቀሳቀሴ አይቀርም  አደጋውም  አይቀርምና መሞቴ ሰለማይቀር  ከወዲሁ  አይኔ እያየ ጆሮየ እየሰማ  ነፍስህን  ይማረው በሉኝ  አለ ይባላል ፡፡
 በጆሮአችን ስንሰማ የነበረውን  በመጽሐፍ ስናነብ ነበረውን  ሰማእትነት  በዐይን አይተናል  ድሮውኑ ክርስቲያን መሆን ሰማእትነት የሚያጎናጽፍ ስለሆነ  ሁላችንም አንገታችንን እንደ ሰጠን ለጊዜው እየቆጠርን ተግባራዊ ለሚሆነው ሰማእትነት መታደል የሚጠይቅ ቢሆንም ሃይማኖታዊ ዝግጅት ማድረግ ያስፈልጋል፤፤

ለነገሩ በቸልተኝነት አልፈነው ነው እንጂ  1999 ዓ.ም በጅማ  የነበረው ሰማእትነት  ትኩረት ስላልተሰጠው አሁን  ገና ዋጋ ያስከፍላል፡፡  በተለይ የሃይማኖት መሪዎችን፡ በነገራችን ላይ እስካሁን የግብጾችንም ጨምሮ  የሃይማኖት መሪዎች  ለሰማእትነት  አልተመረጡም  ምሥጢሩ ምን ይሆን ?

ታላቁ ሊቅ ሊቀ ጉባዔ ቀለመወርቅ ገብረ ዮሐንስ አረፉ



ሊቀ ጉባዔ ቀለመወርቅ   በ1927 ዓ.ም ነሐሴ 5 ቀን  በቀድሞው ጎንደር ከ/ሀገር  እስቴ ወረደ  ከአባተቸው  ገብረ ዮሐንስና ከእናታቸው ወ/ሮ ጠጅቱ  ተወለዱ ፡፡ዕድሜያቸው ለትምህርት እንደደረሱ በአካባቢያቸው  ከሚገኙ መምህራን  ዳዊት ፤ ውዳሴማርያም  አጠቃላይ ንባብ በሚገባ ተምረዋል ፡፡ በመቀጠልም ወደ ደብረ ታቦር ሄደው ዲቁናን  ከብፁዕ አቡነ ሚካኤል ዘግሸን ተቀብለዋል ፡፡ ወደጎጃም በመጓዝ  ቅኔን ከነ አገባቡ በሚገባ ተምረዋል  በ1946 ዓ.ም ወደ አዲስ አበባ ሄደው  ጽርሐ አርያም ቅ. ሩፋኤል  ተመድበው አገልግለዋል  ፡፡በ1951 ዓ.ም መጋቤ ብሉይ ቶማስ ደብረ ጽጌ ቅ/ ማርያም ተመድበው ሲሄዱ አብረው በመሄድ  በዚሁ ገዳም እንደገና ቅኔ ፤ መጻሕፍተ ብሉያት ፤ባሕረ ሓሳብ  ከየኔታ አምሳሉ ክብረ በዓል የተማሩ ሲሆን የኔታ አምሳሉ ሲልቁ ከየኔታ ቀለመወርቅ አቋቋም፣ ክበረ በዓል እና መዝሙር በሚገባ ተምረዋል ፡፡ ከ1956 ዓ.ም ከሰዋስወ ብርሃን ቅ/ ጳውሎስ ማሰልጠኛ በመጡ በአባ ገ/ሚካኤልና በመምህር ገ/ወልድ(የአሁኑ አቡነ ኤርምያስ) የስብከት ዘዴ እና የመሳሰሉትን ስልጠናዎች ሰልጥነዋል(በቦታው)፤ አያይዘውም በ1978 ዓ.ም ወደ ዘዋይ ገዳም ገብተው ለ3 ወራት ያህል የስብከት ዘዴ እና የመሳሰሉትን ተጨማሪ ሥልጠናን ወስደዋል ::  
 ፡ በ1959 ዓ.ም ወደ ደብረ ጽጌ ገዳም ተመልሰው  በሊቀ  ጉባዔነት ፤ በንባብ መምህርነት ፡ የገዳሟ አስጎብኚ በመሆን ሃይማኖተ አበውን በማስነበብ ፤ በሰባኬ ወንጌልነት፤ አገልግለዋል ፡፡ በተለይ የጻድቁ አቡነ ሀብተማርያምን ገድል            ለ28  ዓመታት/ ለ4 ሱባኤያት) በመተርጎም  የጻድቁን ታሪክ ለህዝቡ በማስተዋወቅ ግንባር ቀደም ተጠቃሽ ናቸው፡፡ በአጠቃላይ በደብረ ጽጌ ገዳም ብቻ ለ56 ዓመታት ያህል ቤተ ክርስቲያንን አገልግለዋል  ሊቀ ጉባዔ  ቀለመወርቅ ፤ቅን ፤ሰው ወዳጅ፤ ዘመኑን የዋጁ ሰባኬ ወንጌል የማንኛውን ጥያቄ መላሽና  የሚጠቀሱ መጽሐፍ ነበሩ፡፡ ባደረባቸው ህመም ምክንያት በህክምና ሲረዱ ቆይተው ሚያዝያ 11  ቀን በ80 ዓመታቸው  አርፈው  ሥርዓተ ቀብራቸው  በተለያየ ቦታ የሚገኙ ሊቃውንት  ልጆቻቸው  ወዳጅ ዘመዶቻቸው  በተገኙበት  ሚያዝያ 12  /2007 ዓ.ም  በደብረ ሊባኖስ ገዳም  ተፈጽሟል ፡፡ሊቀ ጉባዔ ባለትዳርና  የሦስት ወንዶችና  ሦስት ሴቶች ልጆች አባት ናቸው ፡፡ የአባታችንን ነፍስ  ከቅዱሳን ዕቅፍ ያኑርልን፡፡

                                   በአውሮጳ   የካህናት አንድነት ማኅበር ሊቋቋም መሆኑ ታወቀ በ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከመላዋ አውሮጳ   የተውጣጡ ካህናት፡” የ...