2018 ኦክቶበር 2, ማክሰኞ


                                   በአውሮጳ  የካህናት አንድነት ማኅበር ሊቋቋም መሆኑ ታወቀ


ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከመላዋ አውሮጳ  የተውጣጡ ካህናት፡” የካህናት አንድነት ማኅበር “ ሊያቋቁሙ እንደሆነ ታወቀ   መስከረም 25 እና  26/ 2011 ዓ.ም በጀርመን ፍራንክፈርት የምሥረታ መርሐ ግብሩን የሚያካሂደው የካህናት አንድነት ማኅበሩ  ከታላቋ ብሪታንያ ጨምሮ ከሁሉም የአውሮጳ ሀገራት በየደብሩ የሚያገለግሉ ካህናት ዲያቆናት እና ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን  በአንድነት የሚያቋቁሙት ማኅበር መሆኑ  ምንጮች ገልጠዋል።
የካህናት አንድነት ማኅበር ማቋቋም ያስፈለገው አሁን በቅርቡ  የተገኘው የሲኖዶስ አንድነት/የቤተ ክርስቲያን አስተዳደር አንድነት/ ከዚህ በፊት እንደተፈጠረው ዓይነት መከፋፈል ዳግም እንዳይፈጠር እና  ዘመኑን የዋጀና በዚህ ዘመን ቤተ ክርስቲያን የሚገጥማትን  የሉላዊነትን ተጽዕኖ  ተቋቁማ ልጆቿ ምእመናንን በሚገባ መምራት ይቻል ዘንድ  ከፍተኛ እገዛ የሚያደርግ በመሆኑ የካህናት አንድነቱ ማኅበር መቋቋም ወሳኝ መሆኑ  ታምኖበታል። አገልጋዩ ካህናት የምእመናንን አንድነት መጠበቅና የኖላዊነት ተግባራቸውንም  ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመወጣት  እንደሚያስችልም  ታስቦ መሆኑን ምንጮች ገልጠዋል ። የካህናት አንድነት ማኅበር መቋቋሙ የምእመናንን አንድነት ለመጠበቅ ዓይነተኛ አስተዋጸኦ የሚያበረክት መሆኑ የሚታወቅ ነው። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ለሀገር ሰላምና አንድነት ለኪነ ጥበባት ለሕግና አስተዳደር በራሱ የሚተማመን መንፈሰ ለዕልናው ከፍ ያለ ትውልድ የመፈጠር ከፍተኛ ተግባሯን አጠናክራ ትቀጥል ዘንድ የአገልጋዮቿ  ካህናት  አንድነት ወሳኝ  መሆኑ ስለታመነበት ይህ የካህናት አንድነት ማኅበር  መቋቋም አስፈልጓል ተብሏል ።
በምሥረታ ጉባኤው  ከተለያዩ የአውሮጳ ሀገራት ወደ ጀርመን ፍራንክፈርት ከ መስከረም 24/2011 ጀምሮ ወደ ፍራንክፈርት እንደሚገቡ ታውቋል
በምሥረታው መጨረሻም ላይ ታዋቂ እመናን የሰንበት ት.ቤቶች ተወካዮች እና ይህንኑ ዜና የሚዘግቡ የተለያዩ ሚዲያዎች እንደሚገኙ ታውቋል
ከዚህ ቀደም የካህናት አንድነት ማኅበር በአሜሪካ የተቋቋመ መሆኑ ይታወቃል

                                   በአውሮጳ   የካህናት አንድነት ማኅበር ሊቋቋም መሆኑ ታወቀ በ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከመላዋ አውሮጳ   የተውጣጡ ካህናት፡” የ...