2016 ሴፕቴምበር 28, ረቡዕ

ካህናት በደመራ ላይ
  በፊንላንድ ሄልሲንኪ ለመጀመሪያ ጊዜ የመስቀል ደመራ በዓል በአደባባይ ተከበረ                                                                 ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰሜን ምዕራብ አውሮፓ ሀገረ ስብከት በፊንላንድ የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት  ቤተክርስቲያን ለመጀምሪያ ጊዜ በአደባባይ የመስቀል ደመራ በዓል መስከረም 16. 2009 ዓ.ም ተከበረ::በዕለቱ የሄልሲንኪ ደብረ ሰላመ መድኃኔ ዓለም የኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን  ካህናት ዲያቆናት ምእመናን ከከተማው አስተዳደር ጀምሮ የባህል እና የሌሎችም ተቋማት ሓላፊዎች ጋዜጠኖች በቦታው ተገኝተዋል የፊንላንድ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን  እና የሌሎቹም ቤተ እምነት መሪዎች ታድመዋል  በሃገራችንም እንደተለመደው በዓበይት በዓላት ብቻ የሚገኙ ምእመናን በዚሁ በስደት ሀገር መኖራቸው የሚገርም ቢሆንም  ያን ዕለት  ተገኝተዋል በተለይ በስደት ያለ ሰው በጣም የሚከፋው ለጥምቀትና  ለመስቀል ደመራ በዓል ጊዜ ነው ይባላል ሁለቱም የአደባባይ በዓላት ናቸው  ያን ዕለት እቤቱ የሚቀር ሰው የለም በሀገር ቤት  ሄልሲንኪም  ያ ትዝ አለኝ ይህ ሁሉ ሰው ነበረ ከሚለው ጥያቄ ጋር የሚገርመው የፈረንጆቹ ደስታ ከ ሐበሻው ቢበልጥ እንጂ አያንስም  ነበረ  ከልብ የመነጨ ልዩ ደስታ ከፊታቸው ይነበባል  አንዳንዶቹም በሀገራችን እንዲህ ያለ ሃይማኖትና ሥርዓትና ሃይማኖት በመኖሩ መደሰታቸውን በመግለጥ  እስካሁን በፊንላንድ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይምኖት ቤተ ክርስቲያን ያለች ሲሆን   በቤተ ክርስቲያን ደረጃ ከተመሠረተች  አምስት ዓመታት ያህል አስቆጥራለች የሄልሲንኪ ደብረ ሰላመ መድኃኔ ዓለም የኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን  በዚሁ ከተማ ይገኛል የካህናቱና       የምእመናኑ ፍቅር የተለየ ነው ያዝልቅልን እንጂ  የደመራውንም በዓልም በደስታ በጋራ  ማክበራችን  በፈረንጆች ዘንድ ልዩ ትዝታን ፈጥሯል

                       ቢያደርሰን ቢያደርሳችሁ ለሚቀጥለው ዓመት  ጸልዩ
  በፊንላንድ ሄልሲንኪ ለመጀመሪያ ጊዜ የመስቀል ደመራ በዓል በአደባባይ ተከበረ   ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰሜን ምዕራብ አውሮፓ ሀገረ ስብከት በፊንላንድ የሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት  ቤተክርስቲያን ለመጀምሪያ ጊዜ በአደባባይ የመስቀል ደመራ በዓል መስከረም 16. 2009 ዓ.ም ተከበረ::በዕለቱ የሄልሲንኪ ደብረ ሰላመ መድኃኔ ዓለም የኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን  ካህናት ዲያቆናት ምእመናን ከከተማው አስተዳደር ጀምሮ የባህል እና የሌሎችም ተቋማት ሓላፊዎች ጋዜጠኖች በቦታው ተገኝተዋል የፊንላንድ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን  እና የሌሎቹም ቤተ እምነት መሪዎች ታድመዋል  በሃገራችንም እንደተለመደው በዓበይት በዓላት ብቻ የሚገኙ ምእመናን በዚሁ በስደት ሀገር መኖራቸው የሚገርም ቢሆንም  ያን ዕለት  ተገኝተዋል በተለይ በስደት ያለ ሰው በጣም የሚከፋው ለጥምቀትና  ለመስቀል ደመራ በዓል ጊዜ ነው ይባላል ሁለቱም የአደባባይ በዓላት ናቸው  ያን ዕለት እቤቱ የሚቀር ሰው የለም በሀገር ቤት  ሄልሲንኪም  ያ ትዝ አለኝ ይህ ሁሉ ሰው ነበረ ከሚለው ጥያቄ ጋር የሚገርመው የፈረንጆቹ ደስታ ከ ሐበሻው ቢበልጥ እንጂ አያንስም  ነበረ  ከልብ የመነጨ ልዩ ደስታ ከፊታቸው ይነበባል  አንዳንዶቹም በሀገራችን እንዲህ ያለ ሃይማኖትና ሥርዓትና ሃይማኖት በመኖሩ መደሰታቸውን በመግለጥ  እስካሁን በፊንላንድ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይምኖት ቤተ ክርስቲያን ያለች ሲሆን   በቤተ ክርስቲያን ደረጃ ከተመሠረተች  አምስት ዓመታት ያህል አስቆጥራለች የሄልሲንኪ ደብረ ሰላመ መድኃኔ ዓለም የኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን  በዚሁ ከተማ ይገኛል የካህናቱና       የምእመናኑ ፍቅር የተለየ ነው ያዝልቅልን እንጂ  የደመራውንም በዓልም በደስታ በጋራ  ማክበራችን  በፈረንጆች ዘንድ ልዩ ትዝታን ፈጥሯል

                       ቢያደርሰን ቢያደርሳችሁ ለሚቀጥለው ዓመት  ጸልዩ

                                   በአውሮጳ   የካህናት አንድነት ማኅበር ሊቋቋም መሆኑ ታወቀ በ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከመላዋ አውሮጳ   የተውጣጡ ካህናት፡” የ...