በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አስተምህሮ መሠረት የሚቀርቡ መንፈሳዊ ትምህርቶች ፤መረጃዎች እና የመሳሰሉት የሚስተናገዱበት ገጽ ነው
ዓርብ 18 ሴፕቴምበር 2015
ረቡዕ 9 ሴፕቴምበር 2015
ወሪድዬ ብሄረ ሮሜ /ቅዱስ ያሬድ/
ካታኮምፕ
ቅዱስ ጳውሎስ የታሠረበት
ቅዱስ ጳውሎስ የታሠረበት
የቅዱሳን የተጋድሎ አደባባይ ፡ ሐዋርያት ስለ ሃይማኖታቸው እውነትን መስክረው
አንገታቸውን ለሠይፍ የሰጡባት
የተሰቀሉባት የቅዱሳን በአት የጸሎት ዋሻቸው
የተዋሕዶ ሃይማኖት የኪነ ጥበብ
ምድር የነበረች ዛሬም እንኳን ያ ሁሉ የቅዱሳን የገድል ውጤት የሚታይባት
የዓለም ጎብኚዎች የሚተሙባት ምድረ ሮሜን
በመንፈስ ተመርቶ በርቀት ተመልክቶ
ወደ ሮሜ ወረድኩ ወርጄ ስለቤተ ክርስቲያን
ተናገርኩ በማለት ቅዱስ ያሬድ ተናገረ እኔም “ በከመ ሰማዕነ ከማሁ ርኢነ “ እንደ ሰማን እንዲሁ ተመለከትን” ተብሎ እንደ ተጻፈ ቅዱስ ጳውሎስ አንገቱን የተሰየፈበት ቅዱስ ጴጥሮስ ቁልቁል
የተሰቀለበት የቅዱሳን በአት የጸሎት ዋሻቸው “ ካታኮምፕ “ የወቅቱ
ነገሥታት ቅዱሳኑን ከአንበሳ ጋር ያታገሉበት ቦታ ምን አደከማችሁ የቅዱሳን የተጋድሎ አደባባይ
ነበረች ሮማ የዛሬውን አያድርገውና፤፤ ሰሞኑን እያየሁ
ነበረ የቱሪስቱ ሰልፍ ለካ ! የትም ሀገር
ሰልፍ አይቀሬ ነው ዓይነቱ ይለያያል እንጂ አልኩና ዕድሜና
ጤንነት ለወንድም በለጠ እና ለባለቤቱ ቤተልሔም እየተመኘሁ ከእነሱ ጋር በመዘዋወር በጽሁፍ ያነበብኩትን
በዓይኔ ተመለከትኩ የሮማንንም ካቶሊክ ላመሰግን ወደድኩ /ባቲካንን/ ለምንም ይሁን ለምን በጥንቃቄ ይዛ
ታስጎበኛለች እኛ ብንሆን እስከ ዛሬ አንጠብቀውም
ይልቁንም የሚሸጠውን እንሸጠው ነበረ ። ሀገራችን ብዙ የቅዱሳን ቦታዎች አሉ ግን በአግባቡ አልያዝናቸውም የቅዱሳኑ ቦታ በሙሉ በሌሎች ተይዞ ሲታይ ያሳዝናል ፤፤ ጌታችን ቅዱስ ጳውሎስን እንዲህ በማለት ወደ ሮሜ ልኮታል
“አስተርአዮ እግዚእነ ለጳውሎስ ወይቤሎ ተአመን በከመ ኮንከኒ ሰማእትዬ በኢየሩሳሌም ከማሁ ሀለውከ ትኩነኒ ሰማእትዬ በሮሜሂ “
ሥራ 23. 11
ጳውሎስ ሆይ በኢየሩሳሌም ስለ እኔ እንደ መሰከርህ እንዲሁ በሮሜም ትመሰክርልኝ ዘንድ ይገባልና አይዞህ አለው ።
ይህ የጌታችንን ጥሪ በደስታ የተቀበለው ቅዱስ ጳውሎስ ሄዶ መከራን በመቀበሉ ዛሬ ሮማውያን የሱን የገድል
ውጤት ኢያሳዩ /ኢያስጎበኙ ይኖራሉ ።
ለአንክሮ
Ø የባቲካን የቅዱሳኑን ቦታዎችን አክብራ ለቱሪስት ምቹ
አድርጋ መጠቀሟ
Ø ከተማዋ
/ሮም ማለቴ ነው በሙሉ የጥንት ሃይማኖታዊ መልኳን ሳትለውጥ መቀጠሏ
ማሳሰቢያ
Ø ኢትዮጵያውያን በሮማ ላላችሁ
ሁላችሁም በሮማ ከተማ ያለውን ታሪካዊ የቅዱሳንን ቦታዎች ያላያሁ
ትኖራላችሁና እንድታዩት አሳስባለሁ። በሮሜ ላላችሁ ሁሉ ከእግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ
ይሁን ። ሮሜ . ፩ ፡ ፯
ቅዳሜ 5 ሴፕቴምበር 2015
የደቡብ ምሥራቅ እና ምዕራብ አውሮፓ ሀገረ ስብከት ፪ኛ ዙር ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባዔውን ትናንት ጀመረ
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የደቡብ ምሥራቅ እና ምዕራብ አውሮፓ ሀገረ ስብከት የ፪ኛ ዙር ዓመታዊ ጠቅላላ
ጉባዔውን
ነሐሴ 29 /2007 ዓ ሞ እንደሚጀምር ታወቀ
በጀርመን ፍራንክፈርት ለ፫ ቀናት በሚደረገው ጠቅላላ ጉባዔ ላይ በሀገረ ስብከቱ የሚገኙ ከ30 በላይ የሚሆኑ የአድባራት አስተዳዳሪዎች ፤ በማኅበረቅዱሳን የአውሮፓ ማእከል ተወካዮች ምእመናን እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ይሳተፋሉ . ጉባዔው ዓመታዊ የአድባራት አገልግሎት አፈጻጸም ሪፖርት እና የቀጣይ ዓመት ዕቅድ ላይ የሚወያይ ሲሆን በገለልተኛ አቢያተክርስቲያናት ጉዳይም ጠቅላላ ጉባዔው አንድ ውሳኔ እንደሚወስን ይጠበቃል ጠቅላላ ጉባዔውን አስመልክቶ በፍራንክፈርት የሚገን አንድ ጋዜጣ እንደ ዘገበው የከተማዋ ከንቲባ በተጋባዥነት በጉባዔው እንደ ሚገኙና የሀገረ ስብከቱ ሊቀጳጳስ የአቡነ ሙሴ መንበረ ጵጵስና ለአገልግሎት ምቹ ይሆን ዘንድ ጠቅሶ በከተማችን በንበረ ጵጵስና መኖሩ እድለኞች ያደርገናል ሲል ዘግቧ በመጨረሻም በሀገረ ስብከቱ ከፍተኛ የአገልግሎት አፈጻጸም ያገኙ አስተዳዳሪዎች በሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሙሴ ሽልማት እንደሚበረከትላቸው ለማወቅ ተችሏል በሊቀ ጳጳሱ አቡነ ሙሴ በማግባባት ላይ የተመሠረተ መንፈሳዊ የማስተዳደር ጥበብ የተነሳ ሀገረ ስብከቱ ሰላማዊና አድባራቱ የራሳቸው ቤተ ክርስቲያን እንዲኖራቸው የሚደረገው እንቅስቃሴ ምስክር ነው በቅርቡ የራሳቸው ቤተ ክርስቲያን ለመግዛት ዝግጅታቸውን ያጠናቀቁ የሙኒክ ደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤልን የሚጠቀሱ ሲሆን የበርሊን ደብረ ገነት አማኑኤል ቤተ ክርስቲያን ደግሞ የራሳቸውን ቤተ ክርስቲያን ገዝተዋል ሌሎቹም ከፍተኛ እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ እንደሚገኙ የሀገረ ስብከቱ ያመለክታል
በጀርመን ፍራንክፈርት ለ፫ ቀናት በሚደረገው ጠቅላላ ጉባዔ ላይ በሀገረ ስብከቱ የሚገኙ ከ30 በላይ የሚሆኑ የአድባራት አስተዳዳሪዎች ፤ በማኅበረቅዱሳን የአውሮፓ ማእከል ተወካዮች ምእመናን እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ይሳተፋሉ . ጉባዔው ዓመታዊ የአድባራት አገልግሎት አፈጻጸም ሪፖርት እና የቀጣይ ዓመት ዕቅድ ላይ የሚወያይ ሲሆን በገለልተኛ አቢያተክርስቲያናት ጉዳይም ጠቅላላ ጉባዔው አንድ ውሳኔ እንደሚወስን ይጠበቃል ጠቅላላ ጉባዔውን አስመልክቶ በፍራንክፈርት የሚገን አንድ ጋዜጣ እንደ ዘገበው የከተማዋ ከንቲባ በተጋባዥነት በጉባዔው እንደ ሚገኙና የሀገረ ስብከቱ ሊቀጳጳስ የአቡነ ሙሴ መንበረ ጵጵስና ለአገልግሎት ምቹ ይሆን ዘንድ ጠቅሶ በከተማችን በንበረ ጵጵስና መኖሩ እድለኞች ያደርገናል ሲል ዘግቧ በመጨረሻም በሀገረ ስብከቱ ከፍተኛ የአገልግሎት አፈጻጸም ያገኙ አስተዳዳሪዎች በሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሙሴ ሽልማት እንደሚበረከትላቸው ለማወቅ ተችሏል በሊቀ ጳጳሱ አቡነ ሙሴ በማግባባት ላይ የተመሠረተ መንፈሳዊ የማስተዳደር ጥበብ የተነሳ ሀገረ ስብከቱ ሰላማዊና አድባራቱ የራሳቸው ቤተ ክርስቲያን እንዲኖራቸው የሚደረገው እንቅስቃሴ ምስክር ነው በቅርቡ የራሳቸው ቤተ ክርስቲያን ለመግዛት ዝግጅታቸውን ያጠናቀቁ የሙኒክ ደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤልን የሚጠቀሱ ሲሆን የበርሊን ደብረ ገነት አማኑኤል ቤተ ክርስቲያን ደግሞ የራሳቸውን ቤተ ክርስቲያን ገዝተዋል ሌሎቹም ከፍተኛ እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ እንደሚገኙ የሀገረ ስብከቱ ያመለክታል
ደንበኛ ይሁኑ ለ፡
ልጥፎች (Atom)
በአውሮጳ የካህናት አንድነት ማኅበር ሊቋቋም መሆኑ ታወቀ በ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከመላዋ አውሮጳ የተውጣጡ ካህናት፡” የ...
-
June 1, 2015 ከሐራ ዘተዋሕዶ በሐዋርያዊት፣ ጥንታዊት እና ብሔራዊት ቤተ ክርስቲያናችን ህልውና እና ዕድገት ፊት ከተጋረጡትና አፋጣኝ እልባት ከ...
-
‹‹…ወንድማችንን እናውቃቸዋለን፤ በእውነቱ ለፌ ወለፌ የማይሉ ደረቅ ሊቅ ናቸው፤ በሃይማኖቱ ዘርፍ ከሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን፣ ከቀኖና ቤተ ክርስቲያን አንዲቱም ነጥብ እንዳትዛባ...