2013 ኦክቶበር 15, ማክሰኞ









 ሰበረ‹ዜና  ረጅም ዕድሜ ያስቆጠሩ ተላላቅ አሥር አቢያተ ክርስቲያናት ተቃጠሉ
32ኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አጠቃላይ ዓለማቀፍ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባዔ ከተጀመረ ዛሬ ሁለተኛ ቀን ሆኖታል ፡፡ በዚህ ተላቅ ጉባዔ ላይ እጅግ አሳዛኝ ሪፖርቶች ተሰምተዋል ጥቂቶቹ
1.     የደቡብ ጎንደር ሀገረ ስብከት ሪፖርት በጉባዔው ላይ እንዳስደመጠው  አምስት ታላላቅ አድባራት  ማንነታቸው ባልታወቀ አጽራረ ቤተክርስቲያን  መቃጠላቸውን  በሪፖርቱ አስደምጦአል አድባራቱ  ታሪካዊና ውድ የሆኑ ቅርሶች የሚገኙበት በመሆናቸው ቤተከርስቲያኒቱን አሳዝኖአል በተያያዘ የኮነኔል ማእረግ የተለጠፈላቸው ሁለት ግለሰቦች ቅርሶችን የመዝረፍ ሙከራ እያደረጉ እያሉ በሀገረ ስበከቱና በህዝበ ክርስቲያኑ ርብርብ የዳነ መሆኑንም ጨምሮ የገለጸው ሪፖርቱ ሀገረ ስብከቱ ረጅም ዕድሜ ያስቆጠሩ ቅርሶች ሚገኙበት በመሆኑ የቅረስ ዘረፋም ከመጠን በላይ መሆኑንም ቸምሮ ገልጦአል እንዲሁም የ15 አቢያተ ክርስቲናት ይዞታ ጉዳይም ከብዙ ክረክር በኋላ መፍትሔ እንዳገኙ ተገልጦአል ፡፡
2.    ምሥራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት  በዚህም ሀገረ ስብከትም አሥር አቢያተ ክርስቲያናት መቃጠላቸውን የሀገረ ስብከቱ ሪፖርት ገለጸ  በሪፖርቱ እንደተገለጸው አቢያተ ክርስቲያናቱ ታሪካዊና የብዙ ቅርስ ባለቤት ሆኑት ተመርጠው መቃጠላቸው ህዝበ ክርስቲያኑን አሳዝኖአል እነዚህ የሀገር ሀብት ቅርሶች ሲወድሙ ዝም ማለትና ወንጀለኞችን ለህግ አለማቅረብ  ጉባዔውን በጣም ያሳዘነ መሆኑን ሪፖርቱ ጨምሮ ገልጦአል የዞኑም አስተዳደር ጉዳዩን በአጽንኦት ተመልክቶ መፍትሔ ሊወስድ ይገባል ሲሉ የጉባኤው ታዳሚዎች አስተያየታቸውን ገልጠዋል ፡፡
3.    ምዕራብ ወለጋ ሀገረ ስብከት  ሕዝቡን በሚገባ ያስተዳድራሉ ይመራሉ ተብለው ሓላፊነት የተሰጣቸው  የዞኑ እና የወረዳው ባለሥልጣናት  የአቢያተ ክርስቲያናቱን ቦታ  በመቀማት፤ ካህናቱን በመደብደብ፤ በቅዳሴ ሰዓት ሕዝቡን ከቅዳሴ ላይ ሂዱ ወደ ስብሰባ በማለት በመረበሽ ፤ በዚሁ ምክንያት አንድ ሴትና አንድ ወንድ  በድብደባ ለሞት መዳረጋቸውን የሀገረ  ስብከቱ ሪፖርት ገልጦአል  ባለሥልጣናቱ በሣሪያ አፈሙዝ በማስፈራራት በይፋ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮችን  መደብደብና ማንገላታት የዘወትር ስራቸው በመሆኑ በዞኑ ለመኖር አለመቻላቸውን ሪፖርቱ ጨምሮ ገልጦአል  የጉባዔው ተሳታፊዎችም መንግስት እንዲህ ያሉትን የግል አጀንዳ ያላቸውን ባለሥልጣናት በመከታተል እርምጃ ሊወስድ ይገባል ብለዋል ይህ ካልሆነ በሕዝቡ መካከል ተከባብሮ የኖረውን ሕዝብ ለማጨት መሆኑ የአደባባ ምሥጢር ነው ብለዋል ተሳታፊዎቸሁ ፡፡ በየሀገረ ስብከቶቹ ሁሉ ተመሳሳይ ችግሮች እንዳሉ  ሀገረስብከቶቹ  በየሪፖርታቸው ገለጠዋል ፡፡
ይሁን እንጂ የደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀገረስብከት በሀገረ ስበከቱ በየደብሩ ላይ   የተፈጸመውን   ፍንዳታ፤ የአቢያተ ክርስቲያናት መዘጋትና ሌሎች ችግሮችን ጨርሶ አለማንሳቱ ከፍተኛ ጥርጣሬ አሳድሮአል ችግሮቹ በሕዝቡ ዘንድ የሚታወቅ ቢሆንም የሀገረ ስብከቱ ሪፖርት ችግሩን ለጉባዔው አለማቅረቡ የችግሩ ተበባሪ አስመስሎታል   የሀገረ ስብከቱ ሥራስኪያጁ  እንደሚያሳየው ከሆነ ከላይ የተጠቀሱት ችግሮች እተባባሱ መሄዳቸው የሚታወቅ ቢሆንም  የአድባራቱን በመናፍቃን መወረርና መቃጠል ችግሮቻውን ከመቅረፍ ይልቅ ማባበሱ ላይ ያቶከሩ ናቸው በማለት ተሳታፊዎች ገልጠዋል፡፡ አንባቢዎች የሀገረስብከቱ አጠቃላይ ችግሮች ስላልተነሱ በዝርዝር የምናቀርብ ይሆናል፡፡


  • Participants of the 32nd SGGA03


   
 
ሰበር ዜና ጅም ዕድሜ ያስቆጠሩ ተላላቅ አሥር አቢያተ ክርስቲያናት ተቃጠሉ

32ኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አጠቃላይ ዓለማቀፍ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባዔ ከተጀመረ ዛሬ ሁለተኛ ቀን ሆኖታል ፡፡ በዚህ ተላቅ ጉባዔ ላይ እጅግ አሳዛኝ ሪፖርቶች ተሰምተዋል ጥቂቶቹ እነሆ!
1.     የደቡብ ጎንደር ሀገረ ስብከት ሪፖርት በጉባዔው ላይ እንዳስደመጠው  አምስት ታላላቅ አድባራት  ማንነታቸው ባልታወቀ አጽራረ ቤተክርስቲያን  መቃጠላቸውን  በሪፖርቱ አስደምጦአል አድባራቱ  ታሪካዊና ውድ የሆኑ ቅርሶች የሚገኙበት በመሆናቸው ቤተከርስቲያኒቱን አሳዝኖአል በተያያዘ የኮነኔል ማእረግ የተለተፈላቸው ሁለት ግለሰቦች ቅርሶችን የመዝረፍ ሙከራ እያደረጉ እያሉ በሀገረ ስበከቱና በህዝበ ክርስቲያኑ ርብርብ የዳነ መሆኑንም ጨምሮ የገለጸው ሪፖርቱ ሀገረ ስብከቱ ረጅም ዕድሜ ያስቆርጠሩ ቅርሶች ሚገኙበት በመሆኑ የቅረስ ዘረፋም ከመጠን በላይ መሆኑንም ቸምሮ ገልጦአል እንዲሁም የ15 አቢያተ ክርስቲናት ይዞታ ጉዳይም ከብዙ ክረክር በኋላ መፍትሔ እንዳገኙ ተገልጦአል ፡፡
2.    ምሥራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት  በዚህም ሀገረ ስብከትም አሥር አቢያተ ክርስቲያናት መቃጠላቸውን የሀገረ ስብከቱ ሪፖርት ገለጸ  በሪፖርቱ እንደተገለጸው አቢያተ ክርስቲያናቱ ታሪካዊና የብዙ ቅርስ ባለቤት ሆኑት ተመርጠው መቃጠላቸው ህዝበ ክርስቲያኑን አሳዝኖአል እነዚህ የሀገር ሀብት ቅርሶች ሲወድሙ ዝም ማለትና ወንጀለኞችን ለህግ አለማቅረብ  ጉባዔውን በጣም ያሳዘነ መሆኑን ሪፖርቱ ጨምሮ ገልጦአል የዞኑም አስተዳደር ጉዳዩን በአጽንኦት ተመልክቶ መፍትሔ ሊወስድ ይገባል ሲሉ የጉባኤው ታዳሚዎች አስተያየታቸውን ገልጠዋል ፡፡
3.    ምዕራብ ወለጋ ሀገረ ስብከት  ሕዝቡን በሚገባ ያስተዳድራሉ ይመራሉ ተብለው ሓላፊነት የተሰጣቸው  የዞኑ እነ የወረዳው ባለሥልጣናት  አቢያተ ክርስቲያናቱን ቦታ  በመቀማት፤ ካህናቱን በመደብደብ፤ በቅዳሴ ሰዓት ሕዝቡን ከቅዳሴ ላይ ሂዱ ወደ ስብሰባ በማለት በመረበሽ ፤ በዚሁ ምክንያት አንድ ሴትና አንድ ወንድ  በድብደባ ለሞት መዳረጋቸውን የሀገረ  ስብከቱ ሪፖርት ገልጦአል  ባለሥልጣናቱ በሣሪያ አፈሙዝ በማስፈራራት በይፋ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮችን  መደብደብና ማንገላታት የዘወትር ስራቸው በመሆኑ በዞኑ ለመኖር አለመቻላቸውን ሪፖርቱ ጨምሮ ገልጦአል  የጉባዔው ተሳታፊዎችም መንግስት እንዲህ ያሉትን የግል አጀንዳ ያላቸውን ባለሥልጣናት በመከታተል እርምጃ ሊወስድ ይገባል ብለዋል ይህ ካልሆነ በሕዝቡ መካከል ተከባብሮ የኖረውን ሕዝብ ለማጨት መሆኑ የአደባባ ምሥጢር ነው ብለዋል ተሳታፊዎቸሁ ፡፡ በየሀገረ ስብከቶቹ ሁሉ ተመሳሳይ ችግሮች እንዳሉ  ሀገረስብከቶቹ  በየሪፖርታቸው ገለጠዋል ፡፡
ይሁን እንጂ የደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀገረስብከት በሀገረ ስበከቱ በየደብሩ ላይ   የተፈጸመውን   ፍንዳታ፤ የአቢያተ ክርስቲያናት መዘጋትና ሌሎች ችግሮችን ጨርሶ አለማንሳቱ ከፍተኛ ጥርጣሬ አሳድሮአል ችግሮቹ በሕዝቡ ዘንድ የሚታወቅ ቢሆንም የሀገረ ስብከቱ ሪፖርት ችግሩን ለጉባዔው አለማቅረቡ የችግሩ ተበባሪ አስመስሎታል   የሀገረ ስብከቱ ሥራስኪያጁ  እንደሚያሳየው ከሆነ ከላይ የተጠቀሱት ችግሮች እተባባሱ መሄዳቸው የሚታወቅ ቢሆንም  የአድባራቱን በመናፍቃን መወረርና መቃጠል ችግሮቸሁን ከመቅረፍ ይልቅ ማባበሱ ላይ ያቶከሩ ናቸው በማለት ተሳታፊዎች ገልጠዋል፡፡ አንባቢዎች የሀገረስብከቱ አጠቃላይ ችግሮች ስላልተነሱ በዝርዝር የምናቀርብ ይሆናል፡፡

2013 ኦክቶበር 14, ሰኞ


፴፪ኛው የመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ዓመታዊ ስብሰባ ተጀመረ

His Holiness Abune Mathias on the 32nd SGGA
ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ የአጠቃላይ ጉባኤው ርእሰ መንበር
  • የቃለ ዐዋዲው ድንጋጌ በፍርድ ቤቶች ያለው ተቀባይነት ማነስ ያስከተለው ችግር፣ ልዩ እምነት ያላቸው አንዳንድ የመንግሥት ባለሥልጣናት በቤተ ክርስቲያን ላይ የሚያደርሱት ሕገ መንግሥቱን የጣሰ ተጽዕኖ፣ ወደ ዐረብ አገሮች እየሔዱ እምነታቸውን ወደ እስልምና የሚለውጡ ኦርቶዶክሳውያን ቁጥር መበራከትና ከእኒህም የካህናት ሚስቶች መኖራቸው፤ የአብነት ት/ቤቶች ህልውና ቀጣይነትና በተለይም የመጻሕፍተ ሊቃውንት ጉባኤያት በብዛት መታጠፍ፤ የመንፈሳዊ ኮሌጆች አስተዳደር፣ የደቀ መዛሙርቱ ምልመላና ምደባ፤ በጠረፋማ አህጉረ ስብከት የአብያተ ክርስቲያን መራራቅ፣ በበጀትና በካህናት እጥረት ለችግራቸው ቶሎ መድረስ አለመቻልና የብዙዎቹ መዘጋት፣ በሰሜን ጎንደርና ቦረና አህጉረ ስብከት የአስተዳደር ችግራቸው ያልተፈታላቸው አጥቢያ አብያተ ክርስቲያን የአህጉረ ስብከቱን 20 በመቶ ፈሰስ አንከፍልም ማለታቸው፣ ባልታወቁ ሰዎች የአብያተ ክርስቲያን መቃጠል፣ የቤተ ክርስቲያን ይዞታዎች (ዐደባባዮች፣ መካነ መቃብሮች፣ የልማት ቦታዎች) መደፈርና ወደ ግል የማዞር ችግር ጉባኤውን እያወያየ ነ፡፡
  • ‹‹የቤተ ክርስቲያን ቀዳሚ ሀብቶች ምእመናን ናቸው፡፡ ብዙ ገቢ ማፍራታችን እሰየኹ ሊባል የሚገባው ቢኾንም ምእመናንን በማብዛት በኩል የተሠራው ሥራ አመርቂ አይደለም፤ የሰበካ ጉባኤያት ዋናው ትኩረት ከገንዘብ ይልቅ በገንዘብ ባለቤቶች ምእመናን ላይ መኾን ይኖርበታል፡፡›› /የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ መምሪያ/
Abune Mathewos presenting annual report
ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ አቡነ ማቴዎስ የ፳፻፭ በጀት ዓመት አጠቓላይ ሪፖርት ሲያቀርቡ
  • ኀምሳ አህጉረ ስብከት በ፳፻፭ ዓ.ም. ከገቢያቸው ለጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ፈሰስ ያደረጉት 35 በመቶ ከ89 ሚልዮን ብር በላይ ደርሷል፤ ከእዚህ ውስጥ 55‚256‚651 ብሩ የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ለመንበረ ፓትርያርኩ ያስገባው ነው፡፡ ኀምሳው አህጉረ ስብከት በበጀት ዘመኑ ለመንበረ ፓትርያርኩ ፈሰስ ያደረጉት የአጠቃላይ ገቢያቸው 35 በመቶ ፈሰስ ከ፳፻፬ ዓ.ም የፈሰስ መጠን ጋራ ሲነጻጸር የታየው ጭማሪ 27‚273‚309 ያህል ነው፡፡ የፈሰሱ መጨመር አጠቃላይ የገቢ ዕድገትን ቢያሳይም የመንበረ ፓትርያርኩ የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ መምሪያ የሒሳብ አሠራሩን ትክክለኛነት የሚያረጋግጥበት ስምሪትና በጀት የለውም
  • ‹‹በደቡብ ሱዳን አምስት ያህል አብያተ ክርስቲያን ተተክለው አገልግሎት እየሰጡ ከጋምቤላ ሀ/ስብከት ጋራ እየተዳደሩ ነው›› በሚል በብፁዕ ዋና ሥራ አስኪያጁ ተካትቶ የቀረበው የሀ/ስብከቱ ሪፖርት ፍጹም ሐሰት ኾኖ መገኘቱ አንዳንድ አህጉረ ስብከት ረጃዎች በጥንቃቄ መታየት እንደሚገባው ያመላከተ ኾኗ
    Participants of the 32nd SGGA03
    የመ/ፓ/አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ፴፪ኛው ዓመታዊ ስብሰባ ተሳታፊዎች
  • ፴፪ው የመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ዓመታዊ ስብሰባ ተሳታፊዎች አቀባበል፣ በአዳራሽ ዝግጅትና መስተንግዶ፣ በጉባኤ ሰነዶች አደረጃጀትጥናታዊ ጽሑፎችና የቡድን ውይይቶች መርሐ ግብሮች ይዘቱ መሻሻል ታይቶበታል፤ ይኹንና ለአንገብጋቢ ጉዳዮች ትኩረትና ሰፊ ጊዜ ሰጥቶ ከመወያየት ይልቅ ሪፖርቶችን ለማዳመጥ የተመደበው ሰዓት የዓመታዊ ስብሰባውን አብዛኛውን ጊዜ የሚወስድ መኾኑ ይታያ፡፡ ለስብሰባው ብር 652‚000 ወጪ ይደረጋል፡፡
    Participating archbishops of the 32nd Sebeka Gubae General assembly
    የአጠቃላይ ጉባኤው ዓመታዊ ስብሰባ ተሳታፊ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት በከፊል
  • ሊቃነ ጳጳሳትን ጨምሮ የጠቅላይ ቤተ ክህነት የመምሪያዎችና ድርጅቶች ሓላፊዎች፣ ከኀምሳ በላይ የአህጉረ ስብከት ሥራ አስኪያጆች፣ የካህናት፣ ምእመናን፣ ሰንበት ት/ቤት ወጣቶችና የስብከተ ወንጌል ተወካዮች፣ የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት 160 ገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎችና የሰበካ ጉባኤ ምክትል ሊቃነ መናብርት በአጠቃላይ ከ900 በላይ ተሰብሳቢዎች ተሳታፊዎች ናቸው፡፡
የዜናው ዝርዝር ይቀጥላል

                                   በአውሮጳ   የካህናት አንድነት ማኅበር ሊቋቋም መሆኑ ታወቀ በ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከመላዋ አውሮጳ   የተውጣጡ ካህናት፡” የ...