2013 ኦክቶበር 31, ሐሙስ


የቤተ ክርስቲያን ተቋማዊ ለውጥ ጥናቶች የቅ/ሲኖዶሱን ሙሉ ድጋፍና ባለቤትነት አገኙ፤ በጥናቶቹ ቀጣይ አካሄድ ላይ ምልአተ ጉባኤው የአፈጻጸም አቅጣጫ ሰጥቷል፤ የምልአተ ጉባኤው ስብሰባ ዛሬ ያበቃል፤ መግለጫም ይኖራል

Holy SynodTikmit Meeting
  • በአገልግሎት ጥራት /በሰው ተኮር ነፍስ የማዳን አገልግሎት/ ምእመናንን ማብዛትና ማጽናት፣ ቤተ ክርስቲያንን ከባይተዋርነትና ጠባቂነት ወደነበራት ሚና መመለስ፣ አስተምህሮዋን ከማይቃረኑ ጋራ ዓለም አቀፍ አጋርነትን በማጠናከር የሰላምና አንድነት ተምሳሌት ማድረግ፣ ለሙስና ችግሮች በንስሐ መንገድ መፍትሔ ማበጀት የቤተ ክርስቲያናችን ስትራቴጂያዊ ዕቅድ ማሕቀፍና ቊልፍ ጉዳዮች ኾነዋል፡፡
  • በቡድን እየተደራጁ የመንግሥትን ወቅታዊ አጀንዳዎች በአሉታዊ መንገድ የሚጠቀሙ አሉባልተኞችና ሙሰኞች እንዲሁም በቤተ ክህነቱ ቢሮክራሲ ውስጥ የተሰገሰጉ የፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ አቀንቃኞች ዋነኛ የለውጡ ተግዳሮቶች እንደኾኑና እንደሚኾኑ ተጠቁሟል፡፡
  • የለውጥ አመራር መዋቅሩ፣ አደረጃጀቱና ዝርዝር አሠራሩ ሕገ ወጥ ጥቅምን የሚያስቀር ተገቢ ጥቅምን የሚያጎለብት፣ ማንኛውንም ሠራተኛና አገልጋይ ለለውጡ የሚያበቃ እንጂ የማያፈናቅል መኾኑ በቅ/ሲኖዶሱ ምልአተ ጉባኤ ታምኖበታል፡፡ ካህናት፣ ባለሞያ ሠራተኞች፣ የሰንበት ት/ቤት ወጣቶችና ምእመናን የለውጡ ግንባር ቀደም አራማጆች ይኾናሉ፡፡
  • ተቋማዊ ለውጡን ለመተግበር÷ ነባሩ የሰው ኃይል የሚበቃበት አዲስ የሰው ኃይል የሚወጣበት የሥራ አመራር ማሠልጠኛ አካዳሚ/የሥልጠና ማእከል/ለመገንባት ጥናቱ ተጠናቆ ዝግጅቱ ተጀምሯል፤ ማእከሉ የድኩማን/አረጋውያን መጦርያና የነዳያን መልሶ ማቋቋሚያም ያካተተ ነው፡፡
  • በአ/አበባ ሀ/ስብከት ለተቋማዊ ለውጥ አመራር ጥናቱ ምቹ ኹኔታ የፈጠሩትና ያስቻሉት የፓትርያርኩ ረዳት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ አለጊዜውና አላግባብ በተደረጉ የአድባራት አስተዳዳሪዎች፣ ጸሐፊዎችና ሌሎች ሠራተኞች ዝውውሮች ቢገመገሙም ከምደባቸው የመነሣታቸው ዜና ከእውነት የራቀ ነው፡፡
  • በሀ/ስብከቱ ጽ/ቤት አዲስ የሙስና ኔትወርክ ዘርግተው ሕገ ወጥ ሲያጋብሱ በቆዩ ሦስት ሓላፊዎች ላይ ርምጃ ይወሰዳል፤ ሓላፊነታቸው ለቀው ወደ አሜሪካ በሄዱት የሀ/ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ መጋቤ ሐዲስ ይልማ ቸርነት ምትክ አዲስ ዋና ሥራ አስኪያጅ ይሾማል፤ ገለልተኝነታቸው፣ የትምህርት ዝግጅታቸውና አገልግሎታቸው የሚጠቀስላቸው የአራዳና ጉለሌ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ሥራ አስኪያጅ ቀሲስ ታጋይ ታደለ ቀጣዩ ዋና ሥራ አስኪያጅ እንደሚኾኑ በስፋት እየተነገረ ነው፡፡
  • የገዳማት አጠቃላይ ወቅታዊ ይዞታና ሥርዐተ ምንኵስናው የሚገኝበትን ኹኔታ ተከታትሎ ለቋሚ ሲኖዶስ ሪፖርት የሚያቀርብ የሊቃነ ጳጳሳት ኮሚቴ በምልአተ ጉባኤው ተደራጀ፤ የዴር ሡልጣን ገዳምን ውዝግብ ለመፍታት ከኮፕት ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ጋራ የሚደራደር በኢየሩሳሌም የኢትዮጵያ ገዳማት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ዳንኤል የሚመራ ኮሚቴ እንዲቋቋም ምልአተ ጉባኤው መመሪያ ሰጥቷል፡፡
  • የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት መተዳደርያ ደንብ በቅዱስ ሲኖዶሱ ጸድቋል፡፡ ደንቡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕፃናትና ወጣቶች ጥራትና ወጥነት ባለው ሥርዐተ ትምህርት ተኮትኩተውና በሥነ ምግባር ታንጸው ተተኪዎች ለማድረግ የሚያስችል፣ ሁለገብ አገልግሎታቸውን ለማጠናከር የሚያግዝ እንደኾነ ተገልጧል፡፡ ሕገ ወጥ ሰባክያንን በመከላከል ስብከተ ወንጌልን በተለያዩ መንገዶች ለማስፋፋት ሰንበት ት/ቤቶችን በይበልጥ የማደራጀት ሥራ ትኩረት ይሰጠዋል
  • ብፁዕ አቡነ ጢሞቴዎስ በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ከነበራቸው የበላይ ሓላፊነት ተነሥተው በበላይ ጠባቂነት ተወስነው ይሠራሉ፤ በኮሌጁ አስተዳደራዊና የፋይናንስ እንቅስቀሴ ጉዳዮች ላይ የመወሰን ሥልጣን አይኖራቸውም፤ የኮሌጁ ዋና ዲን በግልጽ ማስታወቂያ በውድድር በሚካሄድ የቅጥር ሥርዐት ይመደባል፡፡
  • የካህናትና ምእመናን ምዝገባ/ቆጠራ/ ለማካሄድ የተያዘው ዕቅድ ተጨማሪ ዝርዝር ጥናት ያስፈልገዋል በሚል እንዲዘገይ ተደረገ፤ የመንግሥት ፈቃደኝነትና የበጀት አቅም እንደ ስጋት ቢጠቀስም የሊቃነ ጳጳሳት ደመወዝ በመቶ ፐርሰንት እንዲጨምር መወሰኑ አነጋጋሪ ኾኗል፡፡
About these ads

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

                                   በአውሮጳ   የካህናት አንድነት ማኅበር ሊቋቋም መሆኑ ታወቀ በ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከመላዋ አውሮጳ   የተውጣጡ ካህናት፡” የ...