ማክሰኞ 12 ኦገስት 2014

ዘመኑን የዋጁ በሥልጠና የታገዙ ካህናት እንደሚያስፈልጉ ሊቀጳጳሱ ገለጡ

 የደቡብ ትግራይ ማይጨው እና የደቡብ ምሥራቅ ትግራይ አህጉረ ስብከት ሊቀጳጳስ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ ሐምሌ 29 2006 ዓ.ም ከማይጨው ከተማ እና ዙሪያው  አድባራትና ገዳማት ለተውጣጡ ከ70 በላይ የሚሆኑ  ካህናትን ለ15 ቀናት ያህል ሰልጥነው በተመረቁ  ዕለት ሊቀጳጳሱ እንደተናገሩት ዘመኑ የተወሳሰበ ከመሆኑ የተነሳ  ዘመኑን የዋጁ በተለያዩ ጊዜያት በሥልጠና  የታገዙ ካህናት  ያስፈልጋሉ ሲሉ በምርቃቱ ላይ ተናገሩ፡፡ ስልጠናው የተዘጋጀው በነገረ መለኮት ምሩቃን መንፈሳዊ ማኅበር እና በደቡብ ትግራይ ማይጨው ሀገረ ስብከት ጋር በጋራ በመሆን ነው፡፡ ሥልጠናው ትምህርተ ኖሎት፤ ሥርዓተ ቤተክርስቲያን፤ የስብከት ዘዴ እና ሌሎችንም  ያካተተ መሆኑ ታውቆአል ፡፡ደፊትም በዚሁ ምልኩ ሥልጠናዎች ለካህናቱ እንደሚሰጥ ሊቀጳጳሱ አስታውሰዋል፡፡




ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

                                   በአውሮጳ   የካህናት አንድነት ማኅበር ሊቋቋም መሆኑ ታወቀ በ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከመላዋ አውሮጳ   የተውጣጡ ካህናት፡” የ...