የደቡብ ትግራይ ማይጨው እና የደቡብ ምሥራቅ ትግራይ አህጉረ ስብከት ሊቀጳጳስ
ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ ሐምሌ 29 2006 ዓ.ም ከማይጨው ከተማ እና ዙሪያው አድባራትና ገዳማት ለተውጣጡ ከ70 በላይ የሚሆኑ ካህናትን ለ15 ቀናት ያህል ሰልጥነው በተመረቁ ዕለት ሊቀጳጳሱ እንደተናገሩት ዘመኑ የተወሳሰበ ከመሆኑ የተነሳ ዘመኑን የዋጁ በተለያዩ ጊዜያት በሥልጠና የታገዙ ካህናት ያስፈልጋሉ ሲሉ በምርቃቱ ላይ ተናገሩ፡፡ ስልጠናው የተዘጋጀው በነገረ መለኮት
ምሩቃን መንፈሳዊ ማኅበር እና በደቡብ ትግራይ ማይጨው ሀገረ ስብከት ጋር በጋራ በመሆን ነው፡፡ ሥልጠናው ትምህርተ ኖሎት፤ ሥርዓተ
ቤተክርስቲያን፤ የስብከት ዘዴ እና ሌሎችንም ያካተተ መሆኑ ታውቆአል
፡፡ደፊትም በዚሁ ምልኩ ሥልጠናዎች ለካህናቱ እንደሚሰጥ ሊቀጳጳሱ አስታውሰዋል፡፡


ምንም አስተያየቶች የሉም:
አስተያየት ይለጥፉ