ሚያዝያ 12ቀን 2007ዓ.ም
የተለያዩ ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች አሸባሪ ቡድኑ ያሠራጨውን ቪዲዮ መነሻ በማድረግ ባሠራጩት ዘገባ የተገደሉት ክርስቲያኖች ኢትዮጵያውያን መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡
በዚህ ዘመን በአሸባሪ ቡድኑ የተፈጸመው አሰቃቂ ድርጊት የሚወገዝ ሲሆን፤ ድርጊቱን ለፈጸሙት አካላት እግዚአብሔር ልቡና እንዲሰጣቸው እንጸልያለን፡፡ ክርስቲያን ወንድሞቻችንም ስለ ሃይማኖታቸው ሲሉ ያሳዩት ምስክርነት፣ ስላሳዩት ጥብዓት /ስለ ሃይማኖት መከራን ለመቀበል ፈቃደኛ መሆን/ የወንጌልን ቃል መፈጸም በመሆኑ በእግዚአብሔር መንግሥት የከበሩና በቅዱሳኑ ዘንድ የተመሰገኑ ናቸው፡፡
ይህ በመሆኑም ድርጊቱ በዚህ ዓለም ላለነው ሰዎች እጅግ አሰቃቂ ቢሆንም በክርስቲያን ወንድሞቻችን ክርስቲያናዊ ተግባር እንኮራባቸዋለን፡፡ ጌታችን በደሙ የመሠረታትን፣ ቅዱሳን በደማቸው ያጸኑዋትን ቤተ ክርስቲያን እነሱም በደማቸው መሥክረዋልና፡፡
በመጨረሻም በክርስቲያን ወንድሞቻችን አሰቃቂ ሞት ምክንያት ለገጠማችሁ መሪር ሐዘን ለቤተሰቦቻቸውና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው እንዲሁም በድርጊቱ ላዘናችሁ በሙሉ መጽናናትን እንመኛለን፡፡
ይህን ጉዳይ እየተከታተልን የምንዘግብ መሆኑንም እንገልጻለን፡፡
ምንም አስተያየቶች የሉም:
አስተያየት ይለጥፉ