2015 ኤፕሪል 20, ሰኞ

በሊቢያ የሚኖሩ 30 ኢትዮጵያውያን ክርስቲያኖች በአሰቃቂ ሁኔታ ተገደሉ


አትም ኢሜይል

ሚያዝያ 12ቀን 2007ዓ.ም
martyrበሊቢያ የሚኖሩ 30 ኢትዮጵያውያን ክርስቲያኖች ሚያዝያ 11 ቀን 2007 ዓ.ም አይ ኤስ አይ ኤስ በተባለው ዓለም አቀፍ አሸባሪ ቡድን ክርስቲያን በመሆናቸውና ሃይማኖታችንን አንቀይርም በማለታቸው በአሰቃቂ ሁኔታ ተገደሉ፡፡
አሸባሪ ቡድኑ ካሰሠራጨው ቪዲዮ ለመረዳት እንደተቻለው ኢትዮጵያውያን ክርስቲያኖቹ በአሰቃቂ ሁኔታ የተገደሉት በመታረድና ጭንቅለታቸው በጥይት ተፈርክሶ መሆኑን ለመረዳት ተችሏል፡፡

የተለያዩ ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች አሸባሪ ቡድኑ ያሠራጨውን ቪዲዮ መነሻ በማድረግ ባሠራጩት ዘገባ የተገደሉት ክርስቲያኖች ኢትዮጵያውያን መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

በዚህ ዘመን በአሸባሪ ቡድኑ የተፈጸመው አሰቃቂ ድርጊት የሚወገዝ ሲሆን፤ ድርጊቱን ለፈጸሙት አካላት እግዚአብሔር ልቡና እንዲሰጣቸው እንጸልያለን፡፡ ክርስቲያን ወንድሞቻችንም ስለ ሃይማኖታቸው ሲሉ ያሳዩት ምስክርነት፣ ስላሳዩት ጥብዓት /ስለ ሃይማኖት መከራን ለመቀበል ፈቃደኛ መሆን/ የወንጌልን ቃል መፈጸም በመሆኑ በእግዚአብሔር መንግሥት የከበሩና በቅዱሳኑ ዘንድ የተመሰገኑ ናቸው፡፡

ይህ በመሆኑም ድርጊቱ በዚህ ዓለም ላለነው ሰዎች እጅግ አሰቃቂ ቢሆንም በክርስቲያን ወንድሞቻችን ክርስቲያናዊ ተግባር እንኮራባቸዋለን፡፡ ጌታችን በደሙ የመሠረታትን፣ ቅዱሳን በደማቸው ያጸኑዋትን ቤተ ክርስቲያን እነሱም በደማቸው መሥክረዋልና፡፡

በመጨረሻም በክርስቲያን ወንድሞቻችን አሰቃቂ ሞት ምክንያት ለገጠማችሁ መሪር ሐዘን ለቤተሰቦቻቸውና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው እንዲሁም በድርጊቱ ላዘናችሁ በሙሉ መጽናናትን እንመኛለን፡፡

ይህን ጉዳይ እየተከታተልን የምንዘግብ መሆኑንም እንገልጻለን፡፡

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

                                   በአውሮጳ   የካህናት አንድነት ማኅበር ሊቋቋም መሆኑ ታወቀ በ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከመላዋ አውሮጳ   የተውጣጡ ካህናት፡” የ...