2015 ጁላይ 9, ሐሙስ

ሕጻናት በስደት ሀገር .............



GA 15 5


የሰው ልጅ በተለያየ ምክንያት ከአንዱ ሀገር ወደ  አንዱ ሀገር ይዘዋወራል፡ ለትምህርት ፡ለኑሮ ለመሳሰሉት  ሁሉ ይሰደዳል ከዚሁ ጋር ትዳር መያዝ ልጅ መውለድ እይቀሬ ነው ይልቁንም ለሕጻናት መብት ፡ለልጆች ትምህርት ወዘተ የተሻለ ነውና / ተብሎ ስለሚታሰብ ቤተሰብእ፡ያለሐሳብ ልጅ ወልዶ ለመኖር ይወስናል፡፡ እንደ የሀገሩም ሕግ በተለይ የሕጻናት እንክብካቤ ቁጥጥርም በሉት ከባድ ነው ፡፡በየጊዜው ቁመታቸው፡ ክብደታቸው፡ የጭንቅላታቸሀው እድገት ፡ ጸጉራቸው ፡ጥርሳቸው ሁሉ ሳይቀር ሁል ጊዜ በህክምና ባለሙያ ይታያል ፡ዘጠና ዘጠኝ ፐርሰንት ቁጥጥሩ  የሀገሪቱ መንግስት ነው ወላጆች ስለ ልጆቻቸው መናግርና ውሳኔ ማሳለፍ አይችሉም በዚህ ምክንያት  ባህላቸው ሃይማኖታቸው ሥርዓተ ቤተክርስቲያናቸው ቛንቛቸው ሁሉ እየጠፋ ነው  ስለዚህ በስደት ሀገር ስለሕጻናት ጠበቅ ጠለቅ ያለ ሀሳብ ማሰብ ማቀድ ያስፈልጋል  በውጪ ሀገር ያለች ቤተ ክርስቲያን ዘመኑን በዋጀ መልኩ የሀገሪቱን የትምህርት ሥርዓት በመሰለ መልኩ መንፈሳዊ ሥርዓተ ትምህርት በፍጥነት ማዘጋጀት ያስፈልጋል ይህ ካልሆነ በስደት ያሉት ሕጻናት በቅርብ ጊዜ ውስጥ ሙሉ በሙሉ ሀገራቸውን ሃይማኖታቸውን….. ያጣሉ ለዚሁ ጥሩ ጅምር ማኅበረ ቅዱሳን የአሜሪካው ማዕከል የጀመረው አመርቂ ጅምር ይበል የሚያሰኝ ነው ፡፡ የማኅበረ ቅዱሳን አውሮፓው ማዕከልም በፍራንክፈርት ከተማ ጀርመን የ፲፭ኛው ዓመት ጠቅላላ ጉባዔውን ባደረገበት ውቅት በቀጣዩ ዓመት ከአጸደቀው እቅዶች መካከል አንዱ «በውጭው ዓለም የሚገኙ ሕጻናትን በቤተ ክርስቲያን በተቀናጀ መልኩ እንዴት እናስተምር?  በሚል ያቀደው እቅድ ሊበረታታና ሁሉም ሰው ሊረባረብበት ይገባል በተለይ በውጭ ሀገር ያሉ ነዋሪዎች ልጆቻቸው ራሳቸው ልጆች  ኢትዮጵያውያን ሆነው ሃይማኖታቸውን  በጎ ባህላቸውን ጠብቀው ይቀጥሉ ዘንድ መረባረብ ይገባል ያለበለዚያ ሕጻናት ከሃይማኖታቸው፡ ከመልካም ባህላቸው፡ ከሥርዓተ ቤተክርስቲያናቸው እንዳይሰደዱ ሊታሰብበት ይገባል።

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

                                   በአውሮጳ   የካህናት አንድነት ማኅበር ሊቋቋም መሆኑ ታወቀ በ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከመላዋ አውሮጳ   የተውጣጡ ካህናት፡” የ...