2015 ኤፕሪል 23, ሐሙስ

ተዋሕዶ-በደም

ሚያዝያ 14ቀን 2007ዓ.ም
መምህር ሳሙኤል ተስፋዬ
0000000000በደም ተመሥርተሽ
በደም ተገንብተሸ
በደም ተዋሕደሽ
በደም ተሰራጭተሸ
ደሙ ብርሃን ሆነን ከጨለማም ወጣን ፡፡
ተዋሕዶ
በደም አጥምቀሽን
በደም አጽንተሸን
ከጌታችን ጋራ አንድ አካል አረግሽን፡:
ተዋሕዶ
በደሙ አክብረሽን
በደሙ አስታርቀሽን
ደሙን ከካሰልን
የደሙን ማኅተም ኃይሉን ተጎናጸፍን፡፡

ተዋሕዶ
በደም ተገዝቼ
በደሙም ነጽቼ
በደሙ ጸንቼ
ኖርኩኝ ረክቼ ደሙን ጠጥቼ ፡፡

ተዋሕዶ
ለዓለም በፈሰሰው ደሙ
ምልክት ዓርማዬ ሲሆን ማኅተሙ
ነብር ዝንጉርጉርነቱን መለወጥ እንዳይችል መልኩን
እንዴት በመከራ አላውቀውም ልበል?

ተዋሕዶ
ደሙ ይጠራኛል ጽና በርታ እያለ
ምልከት በልቤ ታትሞ ስላለ፡፡
እንዴት ልበጥሰው አላውቅም ልበለው?
መንፈሱ አጽንቶ መንፈሱ ካገዘኝ፡፡
የቀድሞ ማንነት በደሌን ሳያየው
በማተቤ አጸናኝ ለመንግሥቱ አበቃኝ፡፡

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

                                   በአውሮጳ   የካህናት አንድነት ማኅበር ሊቋቋም መሆኑ ታወቀ በ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከመላዋ አውሮጳ   የተውጣጡ ካህናት፡” የ...