ማክሰኞ 21 ኤፕሪል 2015

ነፍስህን ይማር በሉኝ


 ሁለት የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮች በአንድ ላይ  ያገለግላሉ  ሰባክያነ ውንጌል ናቸው  አንደኛው ለአገልግሎት ውደ ክፍለ ሀገር ወጥተው  ሲመለሱ የመኪና አደጋ ደረሰና ወደ 35 ሰዎች ህይወታቸው  ሲያልፍ ሰባኬ ወንጌሉ ተረፉ  ይህንን የሰማ በልደረባቸው  የስራ አጋሮቹን ጠርቶ  ከፊታቸው ቁጭ ብሎ  ነፍስህን ይማረው  በሉኝ  እኔ እደሆን  ለአገልግሎት መንቀሳቀሴ አይቀርም  አደጋውም  አይቀርምና መሞቴ ሰለማይቀር  ከወዲሁ  አይኔ እያየ ጆሮየ እየሰማ  ነፍስህን  ይማረው በሉኝ  አለ ይባላል ፡፡
 በጆሮአችን ስንሰማ የነበረውን  በመጽሐፍ ስናነብ ነበረውን  ሰማእትነት  በዐይን አይተናል  ድሮውኑ ክርስቲያን መሆን ሰማእትነት የሚያጎናጽፍ ስለሆነ  ሁላችንም አንገታችንን እንደ ሰጠን ለጊዜው እየቆጠርን ተግባራዊ ለሚሆነው ሰማእትነት መታደል የሚጠይቅ ቢሆንም ሃይማኖታዊ ዝግጅት ማድረግ ያስፈልጋል፤፤

ለነገሩ በቸልተኝነት አልፈነው ነው እንጂ  1999 ዓ.ም በጅማ  የነበረው ሰማእትነት  ትኩረት ስላልተሰጠው አሁን  ገና ዋጋ ያስከፍላል፡፡  በተለይ የሃይማኖት መሪዎችን፡ በነገራችን ላይ እስካሁን የግብጾችንም ጨምሮ  የሃይማኖት መሪዎች  ለሰማእትነት  አልተመረጡም  ምሥጢሩ ምን ይሆን ?

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

                                   በአውሮጳ   የካህናት አንድነት ማኅበር ሊቋቋም መሆኑ ታወቀ በ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከመላዋ አውሮጳ   የተውጣጡ ካህናት፡” የ...