2015 ኤፕሪል 21, ማክሰኞ

ነፍስህን ይማር በሉኝ


 ሁለት የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮች በአንድ ላይ  ያገለግላሉ  ሰባክያነ ውንጌል ናቸው  አንደኛው ለአገልግሎት ውደ ክፍለ ሀገር ወጥተው  ሲመለሱ የመኪና አደጋ ደረሰና ወደ 35 ሰዎች ህይወታቸው  ሲያልፍ ሰባኬ ወንጌሉ ተረፉ  ይህንን የሰማ በልደረባቸው  የስራ አጋሮቹን ጠርቶ  ከፊታቸው ቁጭ ብሎ  ነፍስህን ይማረው  በሉኝ  እኔ እደሆን  ለአገልግሎት መንቀሳቀሴ አይቀርም  አደጋውም  አይቀርምና መሞቴ ሰለማይቀር  ከወዲሁ  አይኔ እያየ ጆሮየ እየሰማ  ነፍስህን  ይማረው በሉኝ  አለ ይባላል ፡፡
 በጆሮአችን ስንሰማ የነበረውን  በመጽሐፍ ስናነብ ነበረውን  ሰማእትነት  በዐይን አይተናል  ድሮውኑ ክርስቲያን መሆን ሰማእትነት የሚያጎናጽፍ ስለሆነ  ሁላችንም አንገታችንን እንደ ሰጠን ለጊዜው እየቆጠርን ተግባራዊ ለሚሆነው ሰማእትነት መታደል የሚጠይቅ ቢሆንም ሃይማኖታዊ ዝግጅት ማድረግ ያስፈልጋል፤፤

ለነገሩ በቸልተኝነት አልፈነው ነው እንጂ  1999 ዓ.ም በጅማ  የነበረው ሰማእትነት  ትኩረት ስላልተሰጠው አሁን  ገና ዋጋ ያስከፍላል፡፡  በተለይ የሃይማኖት መሪዎችን፡ በነገራችን ላይ እስካሁን የግብጾችንም ጨምሮ  የሃይማኖት መሪዎች  ለሰማእትነት  አልተመረጡም  ምሥጢሩ ምን ይሆን ?

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

                                   በአውሮጳ   የካህናት አንድነት ማኅበር ሊቋቋም መሆኑ ታወቀ በ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከመላዋ አውሮጳ   የተውጣጡ ካህናት፡” የ...