2015 ኤፕሪል 22, ረቡዕ

ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት በሐዘንተኞቹ ቤት ተገኝተው በማጽናናት ላይ ይገኛሉ


ሚያዝያ 13 ቀን 2007 ዓ.ም.
001 papasat 002በዛሬው ዕለት ከቀኑ ዐሥር ሰዓት ጀምሮ ከስድስት በላይ ሊቃነ ጳጳሳት ሰማእቱ ቅዱስ ቂርቆስ ቤተ ክርስቲያን አካባቢ በሚገኘው በሊቢያ በግፍ በአሰቃቂ ሁኔታ የተገደሉትን ወጣቶች ቤተሰቦችን ለማጽናናት በመኖሪያ ቤታቸው ተገኝተዋል፡፡

ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳቱ በጥልቅ ሐዘን ላይ ለሚገኙት የሰማእታቱ ቤተሰቦችን፤ ዘመድ ወዳጆቻቸውን እንዲሁም ምእመናንን በቃለ እግዚአብሔር በማጽናናት ላይ ይገኛሉ፡፡

ብፁዕ አቡነ ሉቃስ፤ ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ፤ ብፁዕ አቡነ ማትያስ፤ ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ፤ ብፁዕ አቡነ እንጦንስ፤ ብፁዕ አቡነ ሔኖክ ተገኝተዋል፡፡

ብፁዕ አቡነ ሉቃስ በሰጡት የወንጌል ትምህርት €œልጆቻችን ብርሃን፤ መጻሕፍቶቻችንና ጀግኖቻችን፤ እንዲሁም የሃማኖትም የሀገርም አርበኞች ናቸው፡፡€ ብለዋል፡፡

ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ በበኩላቸው የሰማእቱ ቅዱስ ቂርቆስንና የእናቱን የቅድስት ኢየሉጣን ታሪክ መነሻ በማድረግ ሰፊ የማጽናኛ ትምህርት ሰጥተዋል፡፡

የማኅበረ ቅዱሳን ሚዲያ ክፍል አባላትም በቦታው ተገኝተዋል፡፡

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

                                   በአውሮጳ   የካህናት አንድነት ማኅበር ሊቋቋም መሆኑ ታወቀ በ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከመላዋ አውሮጳ   የተውጣጡ ካህናት፡” የ...